- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 4
- Всего постов
- 38
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 23
- 1/48двое суток
- 26
- 1/72трое суток
- 28
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
https://t.me/ALPHAMALE26
https://t.me/ALPHAMALE26
https://vt.tiktok.com/ZS4wJp4ge/ Video ተለቋል Like ,repost, copy link
ይሄን ቻናል ተቀላቀሉ ታተርፉበታላቹ 👇 https://t.me/Againsttheworld12
https://vt.tiktok.com/ZS4sMpNus/
አንተ የሕይወት ምንጭ ነህ። አንተ ለእኔ ሁሉም ነገሬ ነህ፤ አንተ ህልውና ራሱ ነህ። እጣ ፈንታዬ እና የእኔ ዘለዓለም ነህ። መጀመሪያዬ እና መጨረሻዬ ነህ። የእኔ አልፋ እና ኦሜጋ ነህ፤ የመጀመሪያና የመጨረሻ ነህ። አንተን ከተውኩህ የእኔ ፍጻሜ ነው፤ ጠፍቻለሁ። በእርግጥ አንተ እኔን ከተውከኝ ከአንተ በኋላ በመንገዶችና በአደባባዮች፣በከተማዎችና በመንደሮች እሮጣለሁ። ያለ አንተ ምንም ማድረግ አልችልምና አንተ ሁሉም ነገሬ ነህ።" "አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ" መልካም የጌታ ቀን ዕለተ ሰንበት "በቅዳሴ"❤
እንኳን ለፆመ ፍልሰታ በሰላም አደረሳችሁ!❤🙏
https://vt.tiktok.com/ZS4xDjHKo/
ኦርቶዶክሶችና ፕሮቴስታንቶች ከእስልምና እምነት ጋር በተያያዘ በንጽጽር (Comparative Religion) ላይ አብረው ይሰራሉ። መጨረሻ ላይ ግን ያ ሰው ወደ የትኛው ቤተ እምነት ነው የሚመጣው? እናንተ ለአንድ ሰው ወንጌልን ሰብካችሁ፣ በክርስቶስ እንዲያምን ወይም ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲቀበል ካደረጋችሁ በኋላ ያ ሙስሊም የነበረ ሰው የትኛውን ቤተ እምነት ነው የሚከተለው? ኦርቶዶክስ ነው ወይስ ፕሮቴስታንት? እስቲ በዚህ ጉዳይ ላይ ተወያዩበት፤ “በእስልምና እምነት ዙሪያ ፕሮቴስታንትም ሆነ ኦርቶዶክስ አብረን መስራታችን ነው ዋናው” የምትሉ ሰዎች፣ በመጨረሻ ግን ግለሰቡ ወደ የትኛው ቤተ እምነት ነው የሚመጣው?»
https://t.me/wendenet
ለመጀመሪያ ጊዜ ቸርች ስገባ
መዝሙረ ዳዊት ፩:፩-፮ --- ፩፤ ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። ፪፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። ፫፤ እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል። ፬፤ ክፉዎች እንዲህ አይደሉም፥ ነገር ግን ነፋስ ጠርጎ እንደሚወስደው ትቢያ ናቸው። ፭፤ ስለዚህ ክፉዎች በፍርድ፥ ኃጢአተኞችም በጻድቃን ማኅበር አይቆሙም። ፮፤ እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና፥ የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።አሜን/፫🙌 ያቆብ ለሊት❤🙏
አርመን ባለችው ቤተክርስቲያናችን የሚዘመር የንስሀ መዝሙር፣የመዝሙሩ ደራሲ ቅዱስ ሜስሮፕ ሲሆን፣ቅዱስ ሜስሮፕ በ5ኛው ክፍለዘመን የነበረ አባት ነው፣ የአርመንኛ ቋንቋ ፊደልን የሠራው ይህ አባት ሲሆን፣አንዳንድ ሊቃውንት የግእዝ ፊደል ተጽእኖ አሳድሮበት እንደነበረበት ይናገራሉ። በርካታ የሆኑ የስርአተ አምልኮ እና የሃይማኖት መጽሐፍትም በመጻፍ ለቤተክርስቲያን አበርክቷል። ስለዚህም በአርመን ያለችው ቤተክርስቲያን ስትዘክረው "Mashtots" መምህር ብላ ትጠራዋለች። በረከቱ ይደርብን። ይህን የንስሀ መዝሙር ወደ አማርኛ እንዲህ ተርጉሜዋለሁ፦ "የኔ ኃጢአት ከመጠን በላይ ነው፣ከባህር አሸዋዎች በላይ ይከብዳል፣ አንተን ብቻ በደልኹኽ፥እግዚአብሔር ሆይ ማረኝ። ጌታ ሆይ የምህረት በር የሆነችውን አንብዕን(ኃጢአትን እያሰቡ ማልቀስን) እንድትከፍትልኝ እጠራሀለሁ፣አንተንም ብቻ በደልኹኽ፥እግዚአብሔር ሆይ ማረኝ። ሰውን የምትወድ መሀሪ ሆይ ርህራሄህን በእኔ ላይ አፍስስ፣አንተንም ብቻ በደልኹኽ፥እግዚአብሔር ሆይ ማረኝ"
https://youtu.be/wi7ivZR7u7Y?si=qNmVbKZDztk999Gm
ኔቱ ሲስተካከልልኝ
"እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ" ሉቃ1 :19 ለመላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ታለቅ ክብረ በአል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። መልካም በአል 19 🙏 @ETHIO_CHELSEA @ETHIO_CHELSEA
³⁰,ለነገሠ ንጉሣቸውን እንዲህ አሉት የጌቶች ጌታ አንተ ነህና ካምላኮች በላይ ያለህ አምላክም አንተ ነህና ከነገሥታትም በላይ ያለህ ንጉሥ አንተ ነህና። ³¹,የጌትነትህም ዙፋን ለልጅ ልጅ ዘመን ጸንቶ ይኖራል ስምህም ለልጅ ልጅ ዘመን ለዘላለሙ የከበረ የተመሰገነ ነውና የከበርህ የተመሰገንህ ነህና ³²,ሁሉንም የፈጠርህ አንተ ፈጥረህ የሁሉም ሥልጣን ካንተ ጋራ ነውና በፊትህም ሁሉ የተገለጠ ነውና። ³³,አንተም ሁሉን መርምረህ ታውቃለህና ካንተም ሊሰወር የሚቻለው የለምና።"አሜን /፫ሀሌ ሉያ🙌❤ መፅሐፈ ሔኖክ,2
"ዲያብሎስ ልጅነታችንን እናቆሽሽ ዘንድ በእኛ ላይ የሚተናኰለው ተንኰል በጣም ተደጋጋሚና ኃይለኛ ነው፡፡ ስለዚህ ይህን መንቻካ የዲያብሎስን ደባ ድል እንነሣ ዘንድ ዘወትር ንቁዎችና ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናል፡፡ እኛ ይህን ማድረግ ሳንችል ቀርተን እጅግ #ጥቂት መግቢያ ቀዳዳ የምንተውለት ከኾነ ግን እርሱ #ጥቂቷን ቀዳዳ ሰፊ በር ያደርጋታል፡፡ እንዲህ አድርጎም ኃይሉን ኹሉ ተጠቅሞ ወደ እኛ ይገባል፡፡ ስለዚህ ስለ ድኅነታችን የሚገደን ከኾነ እንደዚህ #ጥቂትና ቀልድ በሚመስሉ ነገሮች እንኳን #አንዘናጋ፤ እርሱ የሚንቀውና #ጥቂት የሚለው ኃጢአት የለምና፡፡ እኛ #ጥቃቅን የምንላቸውን ነገሮች መነሻ አድርጎ ልጅነታችንን የምናቆሽሽበትን #ታላላቅ ኃጢአቶችን እንድንሠራ አድርጎ እጅግ ይተጋልና፡፡" #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
"አንተ ራስህ ለገዛ ወንድምህ ጨካኝና ይቅር የማትል ኾነህ ሳለስ እግዚአብሔር እንዲራራልህና እንዲምርህ እንዴት መለመን ይቻልሃል? "ባልንጀራህ ምናልባት ንቆህ ሊኾን ይችላል፡፡ አዎ! አንተ ግን እግዚአብሔርን ኹልጊዜ እንደናቅኸው ነው፡፡ በባልንጀራና በእግዚአብሔር መካከልስ ምን ንጽጽር አለ? ባልንጀራህ ምናልባት ጉዳት ሲደርስበት ሰድቦህ ይኾናል፤ አንተም በዚህ ተበሳጭተህ ይኾናል፡፡ አንተ ግን ምንም ሳይጎዳህና በአንተ ላይ ክፉ ሳያስብ ይልቁንም ዕለት ዕለት በረከቱን እየተቀበልክ እያለ እግዚአብሔርን ሰድበኸዋል፡፡ እንግዲህ ተመልከት! ነቢዩ፡- “እመሰ ኃጢአተኑ ትትዐቀብ እግዚኦ መኑ ይቀውም - አቤቱ ኃጢአትንስ ብትጠባበቅ ማን ይቆማል?” ብሎ እንደ ተናገረ እግዚአብሔር በእርሱ ላይ የምንፈጽመውን በደል ቢመረምር ኖሮ አንዲት ቀንስ እንኳን በሕይወት መቆየት አንችልም ነበር (መዝ.129፡3)፡፡ እያንዳንዱ በደለኛ ሰው ለራሱ የሚያውቀውንና ሌላ ሰው የማይመሰክርበትን እግዚአብሔር ብቻዉን ግን የሚያውቀውንስ ይቅርና የተገለጠውና ሰው ኹሉ የሚያውቀው ኃጢአታችንን እንኳን እግዚአብሔር ቢቈጣጠር ኖሮ ከእነዚህ ኃጢአቶች በኋላ የምንጠብቀው ምንድን ነው? እግዚአብሔር ንዝህላልነታችንንና ጸሎት ስናደርስ የምናሳየው ግድየለሽነታችንን፣ ሠራተኞች ለአሠሪዎቻቸው ወታደሮችም ለአለቆቻቸው ጓደኛሞች ለጓደኞቻቸው የሚያሳዩትን ፍርሐትና ክብር ያህልስ እንኳን ለጸሎትና ለልመና በፊቱ በቆምን ጊዜ አለማሳየታችንን ቢቈጣጠር ኖሮ ምን ነበር የምንኾነው? አንተ ከጓደኛህ ጋር ስትነጋገር ለምታደርገው ማንኛውም ነገር ትጠነቀቃለህ፡፡ ስለ በደሎችህ እግዚአብሔርን ስትጠብቀው፣ ለብዙ መተላለፎችህ ይቅርታን ስትጠይቀው፣ ሥርየትን ለማግኘት ስታሳስበው ግን [በፊቱ ላይ] ኹልጊዜ ግድየለሽ ትኾናለህ፡፡ ጉልበትህ በምድር ላይ ተንበርክኮ ሳለ ልቡናህ ግን እዚህም እዚያም፣ በገበያ ሥፍራም፣ በቤት ውስጥም ይዋልላል፤ ከንፈርህ በከንቱና እንዲሁ ያነበንባል፤ ይህን የምንፈጽመው ደግሞ አንዴ ወይም ኹለቴ ሳይኾን ኹልጊዜ ነው። እንግዲህ እግዚአብሔር ይህን ብቻ እንኳን ቢመረምር ይቅርታን ወይም ምሕረትን እንደምናገኝ ታስባለህን? በእውነት አይመስለኝም!" #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ #ትምህርት_በእንተ_ሐውልታት_መጽሐፍ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው
የምክር ቃል ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹህ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ ቃላቶችህ የተመጠኑ እና ጤናሞች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡ የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡ ወደ ጭቅጭቅ እና ንትርክ ከመግባት ራህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡ ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡ የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህ ኃጢአት አትግለጥ፡፡ የባልጀራህ ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡ ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱን ልክ በእሳት ፊት እንደወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡ ተፈጥሮ እንደ መጽሐፍ ፍጥረታት እንደ ጽላት ይሁኑህ፡፡ ከእነሱ ሕግጋትን ተማር፤ በተመስጦ ሆነህ በመጽሐፍ ያልሰፈሩትን ምስጢራት ተረዳ፡፡ እግዚአብሔርን ከሚፈራ በቀር ባለጸጋ የሆነ ሰው ማነው? የእውነት እውቀት ከጎደለው ሰው በላይ ፍጹም ደሃ የሆነ ማን ነው? ሁል ጊዜም እውነተኛ ፍቅራችን ጸንቶ ይቀጥል ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸልይ፡፡ እርሱን ለምነው፡፡ ስለ ቸርነቱ ምስጋና አቅርብ፤ ምክሬን ፈጽሞ ቸል አትበል፡፡ #ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ