tgindex
የህግ ጉዳዮች/Dhimma Seeraa

የህግ ጉዳዮች/Dhimma Seeraa

Статистика
@ethioseeraaанглийский

በፌዴራልና በኦሮሚያ ክልል በማናቸውም ፍ/ቤት ጠበቃና የህግ አማካሪ Abukaaattoo fi Gorsaa Seeraa Legal Consultant and Attorney JUSTICE should have to be Served Contact: solomonlawoffice08@gmail.com

Последний пост
17 авг.
Последнее чтение
14 авг.
Постов за неделю
3
Всего постов
22
Тип
открытый
Язык
английский
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
852
−1 за 5 дн.
Сутки
−1
−0,12%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
278
22 постов
Вовлечённость
32,6%
к подписчикам
Постов в день
0,4
всего 22
Упоминаний
0
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
132
1/48двое суток
151
1/72трое суток
163

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • የወጪ ማስረጃ ውድቅ ሲደረግ ተቀናሽ ስለሚደረግ ወጪ የሂሳብ መዝገብ የሚይዝ ማንኛውም ግብር ከፋይ ያቀረበው የወጪ ማስረጃ በታክስ ባለስልጣኑ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ምክንያት ውድቅ ሲደረግ የሚከተሉት ሁኔታዎች ከተሟሉ ወጪው በከፊል ይያዝለታል፡- 👉 ወጪው ገቢን ለማመንጨት የወጣ ከሆነ 👉 ወጪው የድርጅቱን የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ ለማስቀጠል ከሆነ 👉 ለድርጅቱ ህልውና ወይም ዋስትና ለመስጠት የወጣ ከሆነ የሚፈቀደው የወጪ መጠን (የመቶኛ ቀመር) ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የወጪ ማስረጃውን ውድቅ ቢያደርገውም፣ ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች ከተረጋገጡ በገበያ ዋጋ ተሰልቶ ከታች ባለው መጣኔ መሰረት ወጪው ይያዝለታል፡- 👉 ለቋሚ ንብረት የገበያ ዋጋው ——— 70% 👉 ለሌሎች ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶች የገበያ ዋጋው ——— 65% ወጪው ሙሉ በሙሉ ውድቅ የሚደረግባቸው ሁኔታዎች 👉ወጪው ለድርጅቱ ስራ አስፈላጊ መሆኑ ካልተረጋገጠ። 👉የሀሰት ደረሰኝ (Illegal Receipt)፤ ምንም አይነት የንግድ ልውውጥ ሳይኖር የተቆረጠ ደረሰኝ ከሆነ። 👉 ህገ-ወጥ ደረሰኝ፤ በህግ እውቅና ከሌለው አካል የተገኘ ወይም የተጭበረበረ ሰነድ ከሆነ። በታክስ ጉዳዮች ትምህርት ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ

  • без подписи

  • ይህ የአማራ ክልል የተፋጠነ ውሳኔ ህጋዊና አዋጁን መሠረት ያደረገ ነው። አሁንም ቢሆን ጥብቅና ንግድ አይደለም። ፈጽሞ እንደ ነጋዴም አይደለም። ዜጎችም ቢሆኑ ፍትህ የማግኘት መብት ያላቸው ቢሆንም አሁን ላይ ከተጫነባቸው የዳኝነት ክፍያ አልፎ ቫትም ክፈሉ መባሉ ህገወጥም፣ ኢሞራልም ኢአመክንአዊም ነው።

  • ባለፉት ስምንት ዓመታት የወጡ አብዛኛዎቹ አዋጆች በችኮላ የተዘጋጁ በመሆናቸው በተደጋጋሚ እንዲሻሻሉ መደረጋቸው በጥናት ተመላከተ #Ethiopia: የሥርዓት ለውጥ ከተደረገበት 2010 እስከ 2018 ዓ.ም. የወጡ አብዛኛዎቹ አዋጆች በችኮላና በይድረስ ይድረስ የተዘጋጁ በመሆናቸው፣ ለተደጋጋሚ ማሻሻያዎች መጋለጣቸውንና የአዋጁን ድንጋጌ የጣሱ ደንብና መመርያ እንዲወጡ ምክንያት መሆናቸውን የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከሌሎች ተቋማት ጋር በመተባበር ባጠናው ጥናት አስታወቀ፡፡ ኢንስቲትዩቱ ስለተደረገው ጥናት ያስታወቀው፣ የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር በ2018 ዓ.ም. ያከናወናቸውን አምስት ጥናቶች ማፀደቂያ ዓውደ ጥናት ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲካሄድ ነው፡፡ የሕግ አወጣጥ ሥርዓት መረጋጋት በኢትዮጵያ በሚል ኢንስቲትዩቱ ከባህር.... ሪፖርተር.. ..እናም ህግን.. .. በህግ የፍትህ አካል ነህና ንግድ ፍቃድ እንዳታወጣ፣ እንዳትሸጥ አትለውጥ የተባለው ጠበቃ ወዲ ተመልሶ እንደ ነጋዴ ቫት ተመዝገብ፣ ሂሳብ መዝገብ ያዝ፣ ሪፖርት አድርግ ... መባሉ ...ከእንደዚህ አይነት የችኮላና የይድረስ ሥራ በመሠራቱ የተፈጠረ ስህተት ነው። ይታረማልና ይታረም። እርግጠኛ ነን ይታረማል።

  • የመሬት እና የገቢዎች ተቋማትን ጨምሮ በበርካታ ተቋማት ውስጥ ሙስና አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሆነ አረጋግጫለሁ ሲል የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አሳውቋል። የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ባካሄደው የሙስና ግንዛቤ ዳሰሳ ጥናት፦ - በመሬት አስተዳደርና ይዞታ ምዝገባ፣ - በገቢዎችና ታክስ፣ - በኮንስትራክሽን ፈቃድና ቁጥጥር፣ - በንግድና ትራንስፖርት፣ - በወረዳና ቀበሌ አስተዳደሮች ሙስና አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆኑን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ለዳሰሳ ጥናት በተወሰደ ናሙና ከ6ዐ በላይ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን ሙስና በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ ተግባራት ከፍተኛ እንቅፋትና ችግር የፈጠረ አሳሳቢ ችግር መሆኑን እንደነገሩት ገልጿል፡፡ በአቋራጭ የመበልፀግ ፍላጎት፣ የሥነ ምግባር ጉድለት፣ ውስብስብና ግልጽ ያልሆኑ የአገልግሎት አሰጣጥ ሒደቶችና የሕግ ማስከበር ድክመቶች ለሙስና መስፋፋት ዋነኛውንና ቀዳሚውን ድርሻ እንደሚይዙ የኮሚሽኑ የጥናት ሪፖርት ያመለክታል፡፡ በጥናቱ ጉቦ ለመስጠት የሚገደዱ ሰዎች ለድርጊታቸው የሚያቀርቡት አንዱ ምክንያት አገልግሎቱን ለማግኘት ሌላ አማራጭ በማጣታቸው እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ግለሰቦች ጉቦ የሚሰጡት የሚፈልጉት አገልግሎት እንዲፈጸምላቸውና የሚጠበቅባቸውን ባለማድረጋቸው ሊደርስባቸው የሚችለውን እንግልት  ለማስቀረት እንዲሁም ጉዳያቸው በፍጥነት እንዲፈጸምላቸው መሆኑን ጥናቱ ያመለክታል፡፡ የሙስና ድርጊትን ለመጠቆም የሚፈልጉ ግለሰቦች ሊደርስባቸው የሚችል የበቀል ዕርምጃና የማስፈራራት ሥጋት በመኖሩ፣ አስተማማኝ የጠቋሚዎች ጥበቃ ሥርዓት ማነስ፣ እንዲሁም የጥቆማ አሰጣጥ ሒደቱ ረዥምና ውስብስብ መሆን ኅብረተሰቡ ሙስና ለመጠቆም ሥጋት እንዳለበት በጥናቱ ተገልጿል። ከጥናቱ ተሳታፊዎቹ 75 በመቶ የሚሆኑት በሙስና ጥፋተኞች ላይ ፈጣንና ጠንካራ የሕግ ቅጣት መውሰድ እና የተመዘበረ ሀብትን ማስመለስ ሙስናን ለመቀነስ ውጤታማ እርምጃዎች እንደሆኑ ገልጸዋል። ኮሚሽኑ የሙስና ወንጀል ሕግ ማስከበር ሂደትን በተመለከተም ተጨማሪ የአሠራር ማሻሻያ እንደሚያስፈልግ ገልጿል። በተለይም በተቋማት መካከል የመረጃ ልውውጥና የውሳኔ አፈጻጸም መዘግየት፣ የማስረጃ አሰባሰብ ውስንነት፣ የዲጂታልና ፎረንሲክ ምርመራ አቅም ማነስ እና የሠለጠነ የሰው ኃይል እጥረት በሙስና ምርመራና ክስ ሂደት ላይ እንቅፋት መሆናቸውን አመልክቷል። ኮሚሽኑ የሕግ ማስከበር ሂደቱ ግልጽ፣ ተጠያቂነት ያለው፣ ተገማችና ውጤታማ እንዲሆን ቀጣይነት ያለው የአሠራር ማሻሻያ እንደሚያስፈልግ ጠቁሟል። ሪፖርተር ጋዜጣ እንደዘገበው

  • በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1196(1) መሠረት በሕጋዊ መንገድ የተሰጠ የይዞታ ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ያለው ሰው የንብረቱ ባለቤት ለመሆኑ የሕግ ግምት የሚወሰድ በመሆኑ፣ ይህ ግምት ሊፈርስ የሚችለው ካርታው ከሕግ ውጪ መሰጠቱ ወይም ሰነዱን የመስጠት ሥልጣን በሌለው አካል የተሰጠ መሆኑ ሲረጋገጥ ብቻ ሲሆን፣ ከዚህ ውጪ በሰው ምስክርነት ወይም ገንዘብ አውጥቻለሁ በሚል ክርክር ብቻ ሊፈርስ አይችልም። ​በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40 (1 እና 2) መሠረትም የንብረት ባለቤትነት መብት የሚጠበቀው በሕጋዊ መንገድ በተያዘ ይዞታ ላይ ሲሆን ብቻ ነው። በመሆኑም በጋብቻ ውስጥ ባልና ሚስት በወላጅ ስም በተመዘገበ ይዞታ ላይ ገንዘብና ጉልበት በማፍሰስ ቤት ቢገነቡ እንኳ፣ ይዞታውም ሆነ በይዞታው ላይ የተገነባው ቤት የባልና ሚስት የጋራ ንብረት ሊሆን አይችልም። ​በቤቱ ግንባታ ላይ በትዳር ዘመን በባልና ሚስት የተደረገ የገንዘብ ወጪ ወይም አስተዋጽኦ ካለ፣ ግምቱን ከመጠየቅ ውጪ በሌላ ሰው ስም ባለው ይዞታ ላይ ያረፈውን ቤት የጋራ ንብረታችን ነው ብለው የክፍፍል ጥያቄ ማቅረብ አይችሉም። ​ስለሆነም፣ በጋብቻ ውስጥ በወላጆች ስም ባለው መሬት ላይ የሚገነባ ቤት የባልና ሚስት የጋራ ሀብት ሳይሆን የባለይዞታው ንብረት እንደሆነ የሚቆጠር ሲሆን፣ በፍቺ ጊዜ የትዳር አጋሮች መብት የሚጠበቀው ያወጡትን ገንዘብ በድርሻቸው ተመላሽ እንዲደረግላቸው በመጠየቅ እንጂ የንብረቱን/የቤቱን ክፍፍል በመጠየቅ አይደለም። ​የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ አቶ ብርሃኑ ከበደ እና ም/ኢ/ር ጥሩነሽ ዱባለ፣ መዝገብ ቁጥር 132 (ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም)

  • ድርጊቶችን በፈፀሙ ሰዎች ላይ ክስ ማቅረብ በይርጋ አይታገድም።                    ማጠቃለያ የወንጀል ክስ በአንድ በኩል ተጎጂዎች ፍትሕ የሚያገኙበት የሕግ ሂደት ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በወንጀል የተጠረጠሩ ወይንም የተከሰሱ ግለሰቦች ነፃነት በሕግ የሚገደብበት ነው። በዚሁ መሠረት የወንጀል ክስ መመስረቻ ጊዜ ገደብ በሕግ ወስኖ ማስቀመት በሁለቱ ተፃራሪ መብቶች መካከል ሚዛን ለመጠበቅ የሚያስችል ነው። ስለሆነም ማንኛውም ክስ በሕግ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ሊቀርብ ይገባል፡፡ ምንጭ ፍትሕ ሚኒስቴር  ገፅ

  • ጠበቃ Henok Taye/0916-79-85-85: የወንጀል ክስ ይርጋ በኢትዮጵያ **** ወንጀል ፈፃሚዎች ለፈፀሙት ጥፋት  በሕግ ፊት መጠየቃቸውና ተገቢውን ቅጣት መቀበላቸው  ተገቢና አስፈላጊም ነው፡፡ ይህም  በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ አንድ እንደተመለከተው በወንጀል ሕጉ መሰረት ወንጀል የተደረጉ ድርጊቶች እና የሚያስከትሉትን ቅጣት በመደንገግ ሰዎች ወንጀል ከመፈፀም እንዲቆጠቡ አሰቀድሞ ቅድመ-ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ ቢሆንም  ቅድመ-ማስጠንቀቂዎች በቂ ባልሆኑ ጊዜ ወንጀል ፈፃሚዎች ተቀጥተው ሌላ ወንጀል ከመፈፀም እንዲታቀቡና ለሌሎችም ማስተማሪያ እንዲሆኑ ማድረግን ግቡ ያደረገ ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ግን በወንጀል ሕጉ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ክስ ሊመሠረት እና አጥፊዎችን ለሕግ ማቅረብ የሚገባ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን ክሱ በይርጋ የሚታገድ ይሆናል፡፡ በዚህ አጭር ጽሑፍ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት፣ በሕግ የተመለከተውን የክስ ይርጋ ዘመን እናአቆጣጠር እንዲሁም የክስ ይርጋ ዘመን መቋረጥና መታገድ በአጭሩ እንመለከታለን፡፡                                 የወንጀል ክስ ይርጋ ምንነት የወንጀል ሕጉ የወንጀል ክስ ይርጋን ምንነት በተመለከተ ቀጥተኛ ትርጓሜ ባይሰጥም ከወንጀል ሕግ አንቀጽ 217 በመነሳት የወንጀል ክስ ይርጋ ማለት በማናቸውም ወንጀል ጉዳይ በግል አቤቱታ ወይም በወንጀል ክስ አቅራቢነት ጉዳዩ በዳኝነት ከመታየት የሚታገድበት በሕግ የተመለከተ ጊዜ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡                  የመደበኛ ክስ ይርጋ የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217 መደበኛ የክስ ማቅረቢያ ጊዜን የደነገገ ሲሆን •  የሞት ፍርድ ወይም የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አምስት ዓመት •  ከአስር ዓመት በላይ እስከ ሃያ አምስት ዓመት ለመድረስ የሚችሉ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በሃያ አመት •  ከአምስት ዓመት በላይ እስከ አስር ዓመት ለመድረስ የሚችል ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስራ አምስት አመት •  ከአምስት አመት በማይበልጥ ጽኑ እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአስር ዓመት •  ከአንድ ዓመት በላይ በቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወንጀል በአምስት ዓመት •   እስከ አንድ ዓመት ቀላል እስራት ለሚያስቀጣ ወይም በመቀጮ ብቻ ለሚያስቀጣ ወንጀል በሦስት ዓመት ውስጥ ክስ ካልቀረበ ክሱ በይርጋ ይታገዳል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ተደራራቢ ወንጀሎች ተፈጽመው ሲገኙ የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች ተመሳሳይ በሚሆኑበት ጊዜ የአንዱ ወንጀል የክስ ማቅረብያ የይርጋ ዘመን በሁለቱም ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆንና የወንጀሎቹ ከፍተኛ ቅጣቶች የተለያዩ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ከሁሉም ከባድ የሆነው ወንጀል የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን በሌሎች ወንጀሎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 217(2) ይደነግጋል፡፡                 በግል አቤቱታ አቅራቢነት የሚያስቀጡ ወንጀሎች ይርጋ በወንጀል ሕጉ ልዩ ክፍል ወይም በሌላ ማሟያ የወንጀል ሕግ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ  እንደሚያስቀጡ የተደነገጉ ወንጀሎች የግል ተበዳዩ ወይም ሕጋዊ ወኪሉ የግል አቤቱታ ካላቀረበ በስተቀር ክስ እንደማይመሰረት በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 212 ተደንግጓል ፡፡ ለአንብነትም በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 560 የእጅ እልፊት ወንጀል በግል አቤቱታ ሲቀርብ የሚስቀጣ ወንጀል መሆኑ ተደንግጓል፡፡ መሰል በግል አቤቱታ የሚቀርቡ ወንጀሎች የተፈፀመበት የግል ተበዳይ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 213 መሠረት አቤቱታውን ማቅረብ የሚጠበቅበት ሲሆን የእነዚህ በግል አቤቱታ አቅራቢነት ብቻ የሚያስቀጡ ወንጀሎች የክስ ይርጋ ዘመን ሁለት አመት እንደሆነ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 218 ተደንግጓል፡፡                 ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 222 ፍፁም የሆነ የይርጋ ዘመን የተደነገገ ሲሆን በማናቸውም ምክንያት ከላይ የተመለከትነው መደበኛ የክስ ማቅረቢያ የይርጋ ዘመን እጥፍ ጊዜ ካለፈ ወይም በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎች ሲሆኑ ደግሞ ከላይ ከተመለከትነው በግል አቤቱታ የሚያስቀጡ ወንጀሎችን የይርጋ ዘመን በግማሽ የሚበልጥ ጊዜ ካለፈ በወንጀሎቹ ላይ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ቀሪ ይሆናል፡፡                  የክስ ይርጋ አቆጣጠር በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 219 መሠረት የክስ የይርጋ ዘመን የሚታሰበው የቅጣት ማክበጃ ወይም ማቅለያ ሁኔታዎች ግምት ውስጥ ሳይገቡ በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ሲሆን የተፈፀመው ወንጀል በተለዋጭ ወይም በተደራራቢ ተፈፃሚነት በሚኖራቸውም ቅጣቶች የሚያስቀጣ ሲሆን የይርጋ ዘመኑ የሚታሰበው ከሁሉም ከባድ ለሆነው ወንጀል በወንጀል ሕግ ልዩ ክፍል የተደነገገውን ከፍተኛ ቅጣት መሠረት በማድረግ ይሆናል፡፡ የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረውም ጥፋተኛው የወንጀል ድርጊቱን ከፈጸመበት ቀን አንስቶ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱ እየተደጋገመ የተፈፀመ ከሆነም የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የመጨረሻው የወንጀል ድርጊት ከተፈፀመበት ቀን አንስቶ ነው፡፡ የወንጀል ድርጊቱ ለረጅም ጊዜ ሲፈፀም የቆየ ከሆነ ደግሞ የይርጋ ዘመኑ መቆጠር የሚጀምረው የወንጀል ድርጊቱ ካቆመበት ቀን ጀምሮ ይሆናል፡፡                   የክስ ይርጋ መታገድ የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 220 የወንጀል ክስ ይርጋ የሚታገድበትን ሁኔታ የደነገገ ሲሆን ይኸውም   በሕግ ወይም በፍሬ ነገር ክሱ እንዳይጀመር ወይም እንዳይቀጥል የሚያግድ መሰናክል ካለ መሰናክሉ እስካለ ድረስ   ክስ ቀርቦ ነገሩ በዳኝነት በመታየት ላይ ከሆነ ወይም በሌላ ችሎት የቀረበ ክስ ሳይፈፀም ተከሳሹ በተከሰሰበት የወንጀል ክስ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ የማይገባ በሆነ ጊዜ የይርጋ ዘመኑ ታግዶ ይቆያል፡፡ መታገዱን ያስከተለው መሰናክል ሲወገድ ግን የይርጋ ዘመኑ ወዲያውኑ መቆጠር ይጀምራል፡፡                   የይርጋ ዘመን መቋረጥ የወንጀል ሕጉ አንቀጽ 221 እንደሚያመለክተው ከወንጀሉ ወይም ከወንጀለኞቹ ጋር በተያያዘ ሁኔታ ምርመራ እንዲካሄድ፣ ብርበራ እንዲደረግ፣ መጥሪያ እንዲሰጥ ወይም ክስ እንዲቀርብ የሚሰጥ ትዕዛዝ፣ የሚፈፀም ድርጊት ወይም የሚሰጥ ውሳኔ የይርጋ ዘመኑን መቆጠር ያቋርጣል፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ የይርጋ ዘመን እንደገና እንደ አዲስ መቆጠር ይጀምራል፡፡ በድንጋጌው መሠረት የይርጋ ዘመኑ መቋረጥ ፍፁም የሆነ ውጤት የሚኖረው ሲሆን በወንጀሉ ተካፋይ መሆናቸው ለታወቀውም ሆነ ላልታወቀው ሁሉ መቋረጡ ይፀናባቸዋል፡፡ ይህ ማለት የወንጀል ተካፋይ መሆናቸው ወንጀሉ በተከሰተበት ጊዜ ያልታወቁ ሰዎች ያኔ ባለመታወቃቸው ምክንያት የይረጋ መቋረጥ አስመልክቶ ሊኖር የሚችል ልዩነት እንደሌለ መረዳት ይቻላል፡፡                   በይርጋ የማይታገዱ ጉዳዮች በመርህ ደረጃ የወንጀል ድርጊቶች ከተፈፀሙ በኋላ ክስ ለማቅረብ የሚቻልበት የጊዜ ገደብ በግልፅ ሰፍሮ ያለ ቢሆንም በልዩ ሁኔታ በሌላ ሕግ ከተደነገገ በይርጋ የማይታገዱ ወንጀሎች እንዳሉ ከወንጀል ሕጉ እንቀጽ 216(1) መገንዘብ ይቻላል፡፡ ከዚህ አንፃር የኢ.ፌ.ድ.ሪ ሕገ መንግሥት ቀዳሚው ሲሆን በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 28(1) መሠረት ኢትዮጵያ ባፀደቀቻቸው ዓለም ዓቀፍ ስምምነቶችና በሌሎች የአገራችን ሕጎች የሰው ልጅ ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች ተብለው የተወሰኑ ወንጀሎች፣ የሰው ዘር የማጥፋት፣ ያለፍርድ የሞት ቅጣት እርምጃ የመውሰድ፣ በአስገዳጅ ሰውን የመሰወር ወይም የኢሰብዓዊ ድብደባ

  • *አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ* ጠበቃ እንተነህ ውብአንተ የጥብቅና እና የህግ ማማከር አገልግሎት የሚሰጡ የማህበራችን አባል ሲሆኑ በደረሰባቸው ድንገተኛ የኩላሊት ህመም ምክንያት በአሁኑ ሰአት በሳምንት 2 ጊዜ ከ15,000 ብር በላይ በማውጣት የኩላሊት ዲያሌስስ እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን በዘላቂነት ደግሞ ወደ ውጭ ሃገር በመሄድ ከ3,000,000.00 (ሶስት ሚሊዮን ብር) በላይ በማውጣት የኩላሊት ንቅለ ተከላ ህክምና ማድረግ እንደሚገባቸው ክትትል ከሚያደርጉበት የህክምና ተቋም ተገልፆላቸዋል፤ ስለሆነም የፌደራል ጠበቆች ማህበር አባላት የማህበራችን አባል ለሆኑት #ጠበቃ እንተነህ ውብአንተ የተቻለውን የገንዘብ ድጋፍ እንድታደርጉላቸው እንጠይቃለን፡፡ አካውንት ቁጥር፡- ንግድ ባንክ 1000038889404 / ዳሽን ባንክ 5033169921011

  • በክረምት ለ2 ወራት በከፊል የሚዘጉና ፈጽሞ የማይዘጉ ፍ/ቤቶች ዝርዝር I) በከፊል የሚዘጉ:- 1. የፌደራል ፍ/ቤቶች:- -ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ:: [በፌደራል ፍ/ቤቶች ዐዋጅ ቁጥር 1234/2012 አንቀጽ 38(2) መሠረት] 2. የኦሮሚያ ክልል:- -ከሐምሌ 21/2018 ዓ.ም - መስከረም 20/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ:: [በክልሉ ፍ/ቤቶች ዐዋጅ ቁ.216/2011 አ. 44(1)+በደንብ ቁ.7/2012 አ. 80(1) መሠረት] 3. የአማራ ክልል:- -ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ:: [በክልሉ ፍ/ቤቶች ዐዋጅ ቁ. 282/2014 አ.41 መሠረት] 4. የትግራይ ክልል:- -ከሐምሌ 7/2018-መስከረም 7/2019 5. የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል:- -ከሐምሌ 21/2018 ዓ.ም - መስከረም 20/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ:: 6. የሲዳማ ክልል:- -ከሐምሌ 21/2018 ዓ.ም - መስከረም 21/2019 ኦዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ::] [በክልሉ ዐዋጅ ቁ.40/2016 አ.52(2)] 7. የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል:- -ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም -መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ:: [በዐዋጅ ቁ.6/2016 አ. 59] 8. የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል:- -ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ:: [በክልሉ የፍ/ቤቶች ዐዋጅ ቁ. 1/2016 አ. 59(2)] 9. የሸሪዓ ፍ/ቤቶች:- -ከነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም (የኒካ፣ “ጋብቻ” እና ቀለብ ጉዳዮችን ከማስተናገድ በስተቀር) ዝግ ናቸው:: 10. የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል:- -ነሐሴ 1/2018 ዓ.ም - መስከረም 30/2019 ዓ.ም በከፊል ዝግ ይሆናሉ:: Il) የማይዘጉ 1. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍ/ቤቶች:- -አይዘጉም—መደበኛ ሥራቸውን ይቀጥላሉ!😁 IIl) መረጃ ያልተገኘ 1. የአፋር ክልል :-NA 2. የሐረሪ ክልልል :-NA 3. የሱማሌ ክልል :-NA 4. የጋምቤላ ክልል:- NA 5. የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፍ/ቤት 6. የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን: NA 7. የንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ ይግባኝ ሰሚ አስተዳደራዊ ፍ/ቤት: NA ከምንጭ የተገኘ

  • የእኛ ትጋት፣ ድካምና ምኞት... እንዲህ አይነት የህግ ተርጓሚ ነፃ፣በእውቀት የሚመራና ሁሉንም በእኩል የሚያይና የሚዳኝ ግዙፍና የዝግባ ዛፍ የሆነ የፀና አቋም ያለው ፍ/ቤት መፍጠር ነው። ይሄ ደግሞ የፍትህ አብይታችን ጅምር ነው። በተለየ ሁኔታ .. ይሄንን ታሪካዊ ውሳኔ ለሰጡ ዳኞች ለእናንተ ያለኝ ክብር ባላቹበት ይድረስ.. .. እናንተ ዳኞች የፍትህዋርካ ናቹና ኩሩ ብሎሞ ድመቁ። ውሳኔው ዬሄው.. .. ትምህርት ሚኒስቴር የግል ት/ቤቶች "የክፍያ ማጣጣሚያ" በሚል የትምህርት ክፍያ እንዲጨምሩ ለመወሰን አሻሽሎ ያወጣው መመሪያ በፍ/ቤት ተሽሮአል:: በአመልካቾች እነ ወ/ሮ ዙሪያሽ ተክሌ ፈረደ (132 ሰዎች—በSanford Int’l School ልጆቻቸውን የሚያስተምሩ ወላጆች ናቸው ) እና በተጠሪ ትምህርት ሚ/ር መካከል በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ የፍ/ብሔር ምድብ 1ኛ የአስተዳደር ችሎት በፍ/መ/ቁ. 343621 አመልካቾች የመመሪያ ይከለስልን የሚል በ22/09/2017 ዓ.ም የተጻፈ አቤቱታ አቅርበው ነበር:: የአቤቱታው ይዘትም "ተጠሪ ያወጣው የአጠቃላይ የትምህርት ዘርፍ የት/ት ቤቶች ፈቃድ አሰጣጥ እና እድሳት ማሻሻያ መመሪያ (General Education Sector Schools Licensing & Renewal Amendment Directive) ቁ. 1037/2017 በክፍያ ማጣጣም (harmonization of school fees) በሚል ሳንፎርድ ኢንተርናሽናል ት/ቤት ያላግባብ ዋጋ እንዲጨመርብን አድርጎአል:: ትምህርት ሚ/ር መመሪያውን የማውጣት ሥልጣን በሕግ አልተሰጠውም፣ መመሪያው ከበላይ ሕግጋት ጋር ይጋጫል፣ እና መመሪያው አስገዳጅ የአስተዳፕር መመሪያ አወጣጥ ሥነ ሥርዓትን ተከትሎ የወጣ አይደለምና ተከልሶ ሊሻርልን ይገባል:" የሚል ነበር:: የተከበረው ፍ/ቤትም ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ መመሪያው በፌደራል የአስተዳደር ሥነ ሥርዓት ዐዋጅ ቁጥር 1183/2012 የተመለከተውን አስገዳጅ የመመሪያ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት ሳይከተል የወጣ ነው፤ ትምህርት ሚ/ር የትምህርት ክፍያ ጭማሪን በመመሪያ እንዲወስን የሚያስችል የውክልና ሥልጣን በፌደራል የአስፈጻሚ አካላት ሥልጣንና ተግባር ለመደንገግ በወጣው ዐዋጅ ቁ. 1263/2013 [አንቀጽ 19(4) እና 34(1)] አልተሰጠውም —ultra vires ነው:: እንዲሁም ትምህርት ሚ/ር በአጠቃላይ ትምህርት ዐዋጅ ቁ. 1368/2017 [አንቀጽ 75(4)] መሠረት ከተሰጠው 'የግል የትምህርት ቤቶች ሊያስከፍሉ የሚችሉትን የክፍያ ጣሪያ በየ3 ዓመቱ መመሪያ እያወጣ ማሻሻል እንደሚችል ሥልጣን የተሰጠው ቢሆንም ሚ/ሩ መመሪያ ቁ. 922/2016 ባወጣ አንድ በ1 ዓመት ውስጥ የማሻሻያ መመሪያ ቁ. 1037/2017 ማውጣቱ ሲታይ የማሻሻያ መመሪያው በዐዋጁ የተደነገገውን የጊዜ ገደብ የሚጥስ ነው:: እንዲሁም ትምህር ሚ/ር የግል ትምህርት ቤት ክፍያ ለማጣጣም በሚል መመሪያ እንዲያወጣ ሥልጣን አልተሰጠው:: በመሆኑም መመሪያ ቁ. 1037/2017 ከዐዋጅ ቁ. 1368/2017 ጋር ይጋጫል:: ስለሆነም መመሪያው ተፈጻሚነት ሊኖረው የማይገባ ነው በማለት የተከበረው ፍ/ቤት በሙሉ ድምፅ ሽሮታል:: ————————————

  • የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ሕጋዊ ውጤት እና የሰበር ውሳኔ ትንተና (የሰ/መ/ቁ 246474) የጉዳዩ ዋና ፍሬ ነገር እና መርህ በመከራከሪያ ይዞታ ላይ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ መገኘት ብቻውን ሕጋዊ ባለይዞታ ለማስባል በቂ አለመሆኑ ተረጋግጧል። ካርታው የተሰጠበት አግባብ ከሕጉ ጋር የተጣጣመ መሆኑ እና ባለይዞታው በእርግጥም ሕጋዊ መብት እንዳለው መረጋገጥ አለበት። ሕገ-መንግስታዊ እና የሕግ ማዕቀፎች የግል ንብረት ባለቤትነት መብት (ሕገ-መንግስት አንቀጽ 40(1))፦ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የግል ንብረት ባለቤት መሆን የሚችለበት መብት የተጠበቀ መሆኑ ይደነግጋል። ቋሚ ንብረት እና መሻሻል መብት (ሕገ-መንግስት አንቀጽ 40(7))፦ በጉልበት ወይም በገንዘብ በመሬት ላይ ለሚገነባ ቋሚ ንብረት ሙሉ መብት ይሰጣል፤ ይህም የመሸጥ፣ የመለወጥ፣ የማውረስ፣ የማንሳት፣ ባለቤትነት የማዛወር ወይም ካሳ የመጠየቅ መብቶችን ያካትታል። የሊዝ አዋጅ ቁጥር 721/2004፦ የከተማ መሬት በሊዝ ብቻ መያዝ ያለበት መሆኑን እና ከሊዝ ውጭ የከተማ ቦታ መያዝ ሕገወጥ መሆኑን ያመለክታል። የከተማ አስተዳደር ስልጣን እና የይዞታ ግምት የአስተዳደሩ ስልጣን፦የከተማ አስተዳደሮች ሕጎችን መሠረት በማድረግ ይዞታን የማስተዳደር፣ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ የመስጠትም ሆነ የመሰረዝ ሕጋዊ ስልጣን አላቸው። የባለቤትነት ግምት (ፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1195 እና 1196)፦ ሕጋዊነቱ ተረጋግጦ ካርታ የተሰጠው አካል የንብረቱ ባለቤት እንደሆነ በሕግ ግምት የሚወሰድ ቢሆንም፣ ይህ ግምት በቂ ተቃራኒ ማስረጃ በመቅረብ ሊሻር የሚችል ነው። 4. የሰበር ችሎት ሥልጣን እና የሕግ ትርጉም፣  ፍርድ ቤቶች የማስረጃ ይዘትን በአግባቡ ሳያገናዝቡ ውሳኔ ሲሰጡ ወይም በፍሬ ነገር የተረጋገጠውን ነጥብ ከሕጉ ጋር ሳያያይዙ ሲወስኑ መታረም አለበት። ይህ ጉድለት እንደ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የሚታይ እና በሰበር ሰሚ ችሎት ሥልጣን ማዕቀፍ ውስጥ ታይቶ ሊታረም የሚገባው መሆኑ ተወስኗል። (ተመሳሳይ የሰበር ውሳኔዎች፡ ሰ/መ/ቁጥር 44804፣ 211615 እና 229926) ከአለ ህግ

  • ሐምሌ 6 ቀን 2018 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ቁጥር 7 ስብሰባን ተከትሎ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ መሰረት ሌሎች ጉዳዮች እንደተጠበቁ ሆነው የብድር ጣራን ሙሉ ለሙሉ ማንሳቱንና የፖሊሲ ወለድ ምጣኔን ከ15% ወደ 16% ማሳደጉን ገልጿል። ብሔራዊ ባንክ ከዚህ ቀደም ሲል ያወጣው የብድር ጣራን የመገደብ ፖሊሲ በአንድ በኩል በአዲስ ብድር አማካኝነት የሚፈጠረውን የመገዛት አቅምና ፍላጎት እንዳይጎለበትና በብድር አማካኝነት የሚፈጠረውን ተጨማሪ ገንዘብ የመፍጠር አቅም፣ የገንዘብ እሽክርክሪትና ፍጥነትን (Money Velocity) በመገደብ ግሽበትን ለመቋቋም ተጠቅሞበታል። ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ባወጣው ፖሊሲ መሰረት ደግሞ የብድር ጣራ በመጣሉ ምክንያት ወደ ብድር መለወጥ ሲገባው እንቅስቃሴው የተገታውንና በንግድ ባንኮች ውስጥ የተከማቸውን ከፍተኛ መጠን ያለውን ገንዘብ በከፍተኛ ወለድና ወደ ዜሮ በቀረበ ስጋት (Risk) አሟጦ የመበደር እድል የሚፈጥርለትን ሁኔታ አመቻችቷል። ይህ ማለት ብሔራዊ ባንክ ዛሬ በአወጣው ፖሊሲ መሰረት በOvernight Deposit Facility ና በTreasury Bills (T-Bills) አማካኝነት ሲሸጥና ሲበደር የሚኖረውን ወደ ዜሮ የተጠጋ (Risk) ስጋት እንደ እድል (Advantage) በመጠቀምና ከፍተኛ ወለድ በመስጠት ቀድሞውኑም የግሉ ዘርፉ ሊበደረው ይገባው የነበረውን ገንዘብ እንዲከማች ያደረገውን ገንዘብ መንግስታዊ የተወዳዳሪነት አቅሙን በመጠቀም የግል ዘርፉን የመበደር አቅም ያራቁታል ማለት ነው። ( ወለዱን ለመክፈል ተጨማሪ ገቢ ስለሚጠይቅ ገቢውን የሚያመነጭበት መንገድ ምን ሊሆን እንደሚችል መመርመር የሚገባ ነው) የንግድ ባንኮችም በከፍተኛ ሪስክ ወይም ስጋት ለግል ዘርፉ ከማበደር ይልቅ በአንጻራዊ በከፍተኛ ወለድና ወደ ዜሮ በተጠጋ Risk (ስጋት) አብዛኛውን ብድራቸውን ለመንግስት በOvernight Deposit Facility ና በTreasury Bills (T-Bills) መልክ በብሔራዊ ባንክ ማስቀመጥና ማበደር የተሻለ አትራፊ ሰለሚያደርጋቸው አቅማቸውን በሙሉ አሟጠው ለብሔራዊ ባንክ ካበደሩ በኋላ የቀረውን የማበደር አቅማቸውን እስከ አሁን ተዘግቶ በቆየው ጣራ ምክንያት በግሉ ዘርፍ የተፈጠረውን የብድር ረሐብ አስታከው ለግል ተበዳሪው አዲስ የወለድ ተመን ጨምረው ማበደራቸው የሚጠበቅ ነው። የግል ዘርፉም የብድር ረሐብ ውስጥ የቆየ በመሆኑ ምክንያት ያለ ብድር መስራት የማይችልበት አጣብቂኝ ውስጥ ስለገባ ድርጅቱን ከመዝጋት ይልቅ የግል ባንኮች የሚጥሉትን ከፍተኛ ወለድ ያለማንገራገር ተቀብሎ የወለድ እዳውን ወደ ተጠቃሚው ማሸጋገር እንደሚችል በማሰብ የቀረችውን ብድር ተቀራምቶ መውሰዱ የሚጠበቅ ነው። ከላይ እንደተጠቀሰው በዚህ ፖሊሲ አማካኝነት የብድር ጣራው ለግል ባንኮች ሙሉ ለሙሉ የተነሳ ቢሆንም ብሔራዊ ባንክ የወለድ ክፍያ ምጣኔውን ወደ 16% ከፍ ስላሳደገው የብድር ፍሰት ወደ ብሔራዊ ባንክ ይጎርፋል እንጂ የግል ዘርፉ የብድር ረሐብን የሚቀረፍ አይሆንም። በድምር ውጤቱም የዚህ ፖሊሲ ሰለባ የሚሆነው ሸማቹ ነው። በአጭር ጊዜ (In the Short Run) ባንኮች ወደ ግል ዘርፉ ወጭ ማስተላለፍ (forward shifting) ምክንያት በሚከሰተው የዋጋ ንረት ሸማቹ ለተጨማሪ ግሽበት መጋለጡ፣ የዋጋ ንረትና የመግዛት አቅም መዳከሙና አዙሪቱ ተጠናክሮ መቀጠሉ የሚጠበቅ ነው። እዚህ ላይ ሊነሳ የሚገባው ሌላ ወሳኝ ጉዳይ ደግሞ ባንኮች ሳያበድሩት በመቆየታቸው ምክንያት ያከማቹትን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ብሔራዊ ባንክ ከግለ ዘርፉ ተሻምቶ በአንጻራዊ ከፍተኛ ወለድ (16%) በመበደር ምን ተግባር ላይ ያውለዋል የሚያውለው ጥያቄ ነው?! እሴት ለማይፈጥሩ ፕሮጀክቶች፣ ለጦርነት፣ ለድጎማ፣ ለደሞዝና መሰል ወቅታዊ ወጭዎች ወይስ ለእርዳታና ለገንዘብ ተቋማት ብድር ክፍያ ... ውጤቱ ወደፊት የምናየው ይሆናል ?!!?? በሙሴ ሸሙ

  • ይሄ ነው ማህበር ማለት ነው። ምን አልባት ለፌዴራሉ ማህበርም የማንቂያ ደውል ነው። ከነቁ ማለት ነው። የማህበር አባል ሆኖ ማህበሩ መብቱን ሳያስጠብቅለት ከ250 ጠበቃ በላይ በግሉ ለመብቱ እየታገለ ነው። ማህበሩም ቁጭ ብሎ በማን አለብኝነት ይመስል እያያቸው ነው።

  • без подписи

  • ​ቀደም ብለው ቢያውቋቸው ኖሮ የሚያስመኙዎት ነገር ግን እንዳሉዎት የማያውቋቸው 10 መብቶች https://t.me/ethioseeraa 5ቱን እናስቀድም አይደል ​አብዛኞቹ ሰዎች ችግር ውስጥ የሚወድቁት ስህተት ስለሰሩ ብቻ አይደለም። ይልቁንም በህግ የተረጋገጠላቸውን መብቶቻቸውን ስለማያውቁ ወይም ስለማያስተውሉ ወይም ልብ ስለማይሏቸው እንጂ። በዚህ ርዕስ ብዙ መዘርዘር ብንችልም እስቲ ​ብዙ ሰዎች አቅልለው የሚመለከቷቸው አንዳንድ መብቶች እንመልከት። ጠቃሚ ነው ካሉ ለወዳጆ ይደርስ ዘንዘዳ ያጋሯቸው። ​I. በቁጥጥር ስር በሚውሉበት (በሚታሰሩበት) ጊዜ ያሉዎት መብቶች ​በቁጥጥር ስር መዋል ማለት መብቶችዎን ሁሉ አጥተዋል ማለት አይደለም። በአጠቃላይ የሚከተሉት መብቶች አሉዎት፦ 👉 ለምን በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የማወቅ። 👉 ዝም የማለት። 👉 ጠበቃ የማማከር ወይም የህግ ውክልና የማግኘት። 👉 በሰብአዊነት እና በክብር የመያዝ። በቁጥጥር ስር መዋል ማለት ጥፋተኛ መባል ማለት አይደለም። ​ll. የኪራይ ቤት ተከራይ መብቶች ​ቤት ተከራይተው መክፈልዎ ክብርዎን አሳልፈው ሰጥተዋል ማለት አይደለም። እንደ ተከራይ የሚከተሉት መብቶች ሊኖሩዎት ይችላሉ፦ 👉 በቤቱ ውስጥ በሰላም የመኖር። 👉 ከቤት ከመውጣትዎ በፊት ተገቢውን ቅድመ-ማስጠንቀቂያ የማግኘት። 👉 በኪራይ ውሉ ላይ የተስማሙባቸው ውሎች እንዲከበሩ የመጠየቅ። 👉 መብትዎ በሚጣስበት ጊዜ ህጋዊ መፍትሄዎችን የመፈለግ። አከራይዎ የቤቱ ባለቤት እንጂ የእርስዎ ህይወት ባለቤት አይደለም። ​III. የሰራተኛ መብቶች ​ብዙ ሰራተኞች ሊያስተናግዱት የማይገባቸውን በደል በዝምታ ያስተናግዳሉ። ሰራተኞች ብዙውን ጊዜ ከሚከተሉት ጋር የተያያዙ መብቶች አሏቸው፦ 👉 ለተሰራው ስራ ተመጣጣኝ (ፍትሃዊ) ደመወዝ የማግኘት። 👉 አስተማማኝ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የስራ አካባቢ የማግኘት። 👉 ካልተገባ አድልዎ የመጠበቅ። 👉 ስለ ስራው ቅጥር ሁኔታዎች እና ግዴታዎች አስቀድሞ የመረጃ የማግኘት። ደመወዝ ማግኘት ብቻ በስራ ቦታ ያለዎት ብቸኛ መብት አይደለም። ​IV. የደንበኛ (ሸማች) መብቶች ​የንግድ ድርጅቶችም ግዴታዎች አለባቸው። እንደ ደንበኛ የሚከተሉት መብቶች ሊኖሩዎት ይችላሉ፦ 👉 ቃል የተገባላቸውን አይነት እቃዎች እና አገልግሎቶች የማግኘት። 👉 ስለ ምርቶች ትክክለኛ መረጃ የማግኘት። 👉 ፍትሃዊ ያልሆነ አያያዝ ሲገጥምዎ ቅሬታ የማቅረብ። 👉 ጉድለት ያለባቸው ምርቶች ጉዳት ወይም ኪሳራ ሲያደርሱ ካሳ የመጠየቅ። "የተሸጠ እቃ አይመለስም" የሚሉ ምልክቶች የደንበኛን መብት በራሳቸው ሙሉ በሙሉ አያሽሩም። ​V. ውል ከመፈረምዎ በፊት ያሉዎት መብቶች ​ማንም ሰው እንዲቸኩሉ እና በፍጥነት እንዲፈርሙ እንዲያደርግዎ አይፍቀዱ። በአጠቃላይ የሚከተሉት መብቶች አሉዎት፦ 👉 ስምምነቱን በደንብ የማንበብ። 👉 ጥያቄዎችን የመጠየቅ። 👉 ማብራሪያ ወይም የህግ ምክር የመጠየቅ። 👉 ባልተስማሙባቸው ውሎች ላይ የመቃወም (ያለመቀበል)። ፊርማዎ ህይወትዎን ሊለውጥ ይችላል። በጥንቃቄ ይጠቀሙበት። ሰለሞን ነኝ። https://t.me/ethioseeraa

  • በወንጀል የተከሰሰ ሰው የግል ተበዳይን በመከላከያ ምስክርነት ያቀረበና የግል ተበዳይም ድርጊቱ ያለመፈጸሙን በመግለጽ የምስክርነት ቃል የሰጠ ከሆነ ዓ/ህግ የግል ተበዳይ የምስክርነት ቃል በደላላ ወይም በጥቅም የተገኘ መሆኑን ለማረጋገጥ እስከ አልቻለ ድረስ ተከሳሽ ክሱን አልተከላከለም ሊባል የማይገባ ስለመሆኑ፡፡ ሰ.መ.ቁ 137545 ቅፅ  22

  • የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሳባ የሕገ መንግሥት ትርጉም አያስፈልጋቸውም በማለት የወሰናቸው መዝገቦች ዝርዝር ተ.ቁ መ. ቁጥር 1. 5477/13 2. 7565/15 3. 7756/15 4. 7761/15 5. 7899/15 6. 7972/15 7. 7975/15 8. 7978/15 9. 7991/15 10. 7999/15 11. 8009/15 12. 8010/15 13. 8012/15 14. 8013/15 15. 8014/15 16. 8016/15 17. 8017/15 18. 8020/15 19. 8032/15 20. 8037/15 21. 8041/15 22. 8054/15 23. 8072/15 24. 8078/15 25. 8083/15 26. 8086/15 27. 8095/15 28. 8110/15 29. 8114/15 30. 8102/15 31. 8201/16 32. 8210/16 33. 8212/16 34. 8222/16 35. 8229/16 36. 8422/16 37. 8430/16 38. 8431/16 39. 8437/16 40. 8438/16 41. 8440/16 42. 8448/16 43. 8510/16 44. 8512/16 45. 8518/16 46. 8525/16 47. 8535/16 48. 8552/16 49. 8568/16 50. 8589/16 51. 8598/16 52. 8615/16 53. 8626/16 54. 8663/16 55. 8683/16 56. 8703/16 57. 8730/16 58. 8735/16 59. 8750/16 60. 8794/16 61. 8800/16 62. 8892/16 63. 8895/16 64. 8907/16 65. 9136/17 66. 9424/17 67. 9544/17 68. 9551/17 69. 9744/17 70. 9750/17 71. 9837/17 72. 10052/17 73. 10226/18 74. 10452/18 75. 10737/18 76. 10740/18 77. 10748/18 78. 10881/18 79. 10924/18 80. 11149/18 81. 11426/18 82. 11087/18           ማስፈቀጃ 83. 10803/18  ፈቃድ አላገኘም *ማስታወሻ* 1. ቁጥራቸው የቅርብ ጊዜ የሆኑት ጉዳዮች ቀድመው የታዩበት ምክንያት በጉባዔው መመሪያ መሰረት ቅድሚያ አግኝተው ምርመራቸው የተጠናቀቀ (የወንጀል፣ የአካል ጉዳተኞች፣ የአሰሪና ሰራተኛ፣  ከፍ/ቤት ሪፈራል የተላኩ፣ የታገዱ መዝገቦች መሆናቸውን እየገለፅን ከዚያ ውጭ ያሉት ግን እንደ አመጣጥ ቅደም ተከተላቸው የተስተናገዱ ናቸው፡፡ 2. ከላይ የተዘረዘሩትን ውሳኔዎች  የውሳኔ ግልባጭ ከሁለት ሳምንት በኋላ በጉባዔው ፅ/ቤት በመቅረብ ማግኘት የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን፡፡ መረጃው የሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ጽ/ቤት ነው

  • አንድ ህግ ተፈፃሚና ተጌባራዋ የሚሆነው በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ሲወጣ ነው..ከዚህ የተለየ የለም።

  • без подписи