አል-ኢማሙ ነወዊይ መድረሳ የወጣቶች ጀማዓ
Статистика☞አላማችን በሸሪዐዊ እውቀት የነቃ እና የበቃ ትውልድ መፍጠር ነው፡፡ ✌ኢኽላስ መነሻችን ተቅዋ መንገዳችን ሰብር ምርኩዛችን ነው! 📡ሸሪዐዊ እውቀትን እና ወቅታዊ መረጃዎችን በቻናላችን ያገኛሉ። እኛን ብላችሁ ስለምትከታተሉን እናመሰግናለን።
- Последний пост
- 12 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 1
- Всего постов
- 28
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 38
- 1/48двое суток
- 43
- 1/72трое суток
- 46
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
በአንድ ወቅት በአንድ ትንሽ መንደር ውስጥ የሚኖር አንድ ታዳጊ ልጅ አያቱ በትልቅ ጠረጴዛ ላይ ተቀምጠው ሲጽፉ በትኩረት ይመለከታቸዋል። ልጁም ወደ አያቱ ቀረብ አለና፦ አያቴ፣ የምትጽፈው ታሪክ ስለ እኔ ነው? ወይንስ ስለ አንተ? ብሎ ጠየቃቸው። አያቱ ጽሕፈታቸውን አቆሙና ፈገግ ብለው እንዲህ አሉት፦ የምጽፈው ስለ አንተ ነው ልጄ፤ ነገር ግን ከምጽፋቸው ቃላት በላይ አሁን በእጄ የያዝኳት እርሳስ እጅግ ትልቅ ትርጉም አላት። ስታድግ ልክ እንደዚች እርሳስ እንድትሆን እመኛለሁ። ልጁም ግራ ተጋብቶ እርሳሷን ተመለከታት። ነገር ግን በየቀኑ ከሚያያቸው ተራ እርሳሶች የተለየ ምንም ነገር አላየባትም። አያቴ፣ ይህች እኮ ተራ እርሳስ ናት! ምን የተለየ ነገር አላት? አላቸው። አያቱም እጁን እየዳሰሱ እንዲህ አሉት፦ ልጄ፣ ነገሮችን በደንብ ካስተዋልክ፣ ይህች እርሳስ በሕይወትህ ውስጥ ሙሉ ደስተኛና ስኬታማ ሰው እንድትሆን የሚያደርጉህ አምስት ታላላቅ ምስጢሮች አሏት አሉት። 1. የመሪው እጅ (የመጀመሪያው ምስጢር)፦ ይህች እርሳስ ታላላቅና ውብ ቃላትን መጻፍ የምትችለው በአንድ ሰው እጅ ውስጥ ስትሆን ብቻ ነው። አንተም እንዲሁ በሕይወትህ ትልቅ ታሪክ መስራት የምትችለው ራስህን ለፈጣሪ መሪነትና ለመልካም አስተማሪዎች ምክር ስትሰጥ ብቻ ነው። 2. የመቅረጫው ሕመም (ሁለተኛው ምስጢር)፦ እርሳሷ መፃፍ ስታቆም ምን እንደምናደርጋት ታውቃለህ? በመቅረጫ እንቀርጻታለን። ይህ መለል እና መቅረጽ ለእርሳሷ ከባድ ሕመም አለው። ነገር ግን ከተቀረጸች በኋላ ይበልጥ ሹልና በጥራት የምትጽፍ ትሆናለች። አንተም በሕይወትህ የሚገጥሙህ ፈተናዎች፣ ትችቶችና ስቃዮች ዛሬ ቢያምሙህም፣ ነገ ካንተ የተሻለና ጠንካራ ሰው ለመገንባት የመጡ መቅረጫዎች መሆናቸውን እወቅ። 3. የላጲሱ ዕድል (ሦስተኛው ምስጢር)፦ እርሳሷ ስትሳሳት ከበስተጀርባዋ ያለውን ላጲስ በመጠቀም ስህተቷን ማረም ትችላለች። ይህ የሚያስተምረን በሕይወት ውስጥ መሳሳት ጥፋት እንዳልሆነ ነው። ዋናው ቁምነገር ስህተትን አምኖ የመቀበልና የመታረም ብልህነት ካለን፣ ያ ስህተት ወደ መልካም መስመር ይመራናል። 4. የውስጡ ከሰል (አራተኛው ምስጢር)፦ ለእርሳሷ ዋናው ነገር የውጭው ውብ እንጨት ወይም ቀለሟ ሳይሆን፣ በውስጧ ያለው ጥቁር የከሰል እርሳስ ነው። አንተም ለሰዎች የምታሳየው የውጭ ውበትህ፣ የሀብትህ ወይም የልብስህ ጥራት ሳይሆን፣ እውነተኛው ታላቅነትህ በውስጥህ ያለው መልካም ስብዕናህ፣ አስተሳሰብህና ንጹሕ ልብህ ነው። 5. የአሻራው መቅረት (አምስተኛው ምስጢር)፦ እርሳሷ ባለፈችበት ወረቀት ላይ ሁሉ የራሷን መስመርና ምልክት ጥላ ያልፋል። አንተም በዚህ ምድር ላይ ስትኖር በየቀኑ የምታደርጋቸው ነገሮች ሁሉ በሰዎች ሕይወት ላይ የራሳቸውን ምልክት ይተዋሉ። ስለዚህ በሄድክበት ቦታ ሁሉ መልካም አሻራ ጥለህ ለማለፍ በጥንቃቄ ኑር! ውጫዊው ዓለም ምንም ያህል ቢጫንህ፣ በውስጥህ ያለውን የጥራት መስመር ካላጠፋህ ታሪክህን በራስህ እጅ መጻፍ ትችላለህ። Copied
без подписи
«መጤው እስልምና እንጅ እኛ አይደለንም!» «እናንት ሙስሊሞች መጤ ናችሁ» ለሚሉ ክርስቲያኖች በመልስነት የሚሰጥ ንግግር ከሆነ ሰነበተ።መጤነት የሚለው ፅንሰ ሀሳብ መነሻው ድንበር ነው ። የቦታ ባለቤት አለመሆንን የሚገልፅ መሆኑ ነው ።ይህ የመሬትና የቦታ ክለላ የመጣው የሰው ልጆች በምናባቸው ባሰመሩት ወሰን እንጅ አላህ ማስረጃ ያወረደበት ክፍፍል ሆኖ አይደለም። መጤ መባል የሚያሸማቅቅህ ከሆነ አንተ በሰው ሰራሽ ድንበር ታምናለህ ማለት ነው ።አላህ ምድርን ሰፊ አድርጎ የፈጠራት በየትኛውም አቅጣጫዋ ተንቀሳቅሰህ እንድታመልከው ነበር።በክቡር ቃሉ እንዳለው :- يَا عِبَادِيَ الَّذِينَ آمَنُوا إِنَّ أَرْضِي وَاسِعَةٌ فَإِيَّايَ فَاعْبُدُونِ «እናንተ ያመናችሁ ወይ! ምድሬ ስፊ ነችና እኔንም ብቻ አምልኩ» (አል ዐንከቡት 56) እዚህ ምድር ላይ አላህ ድንበር አስቀምጦ ይህ የእገሌ ያ የእገሌ ነው ብሎ ያከፋፈለው መሬት የለም ፤ ነገር ግን ሰዎች ራሳቸው ድንበር አበጁና ለነዚሁ ድንበሮች ራሳቸውን ባሪያ አደረጉ። አላህ የሰጣቸውን የመንቀሳቀስ ነፃነት በራሳቸው ወይም በጠላ ቶቻቸው እጅ ገደቡ። ከዚያም አልፎ የኔ ያንተ የሚል ምናባዊ ወሰን አስቀምጠው እርስ በርስ ይተላለቃሉ። «የሀገራችን» ኩፋ••ሮች መጤ ሲሉ እንዳልሆነ ለማሳመን የሚጥር ሰው በድንበር ያምናል ማለት ነው።ይህም ድንበር ኢትዮጲያዊነት መሆኑ ነው።በተቃራኒው መጤነት ወንጀል መሆኑን እያፀደቀላቸው መሆኑን ግን አይረዳም። በዚህ እሳቤ መሰረት ረሱል ﷺ ወደ መዲና «መጤ» ሆነው ነው የገቡት።ነገር ግን መዲና ላይ «በጥገኝነት» ከመኖር አልፈው «በሰው ሀገር ላይ» ኢስላማዊ መንግስት መሰረቱ። ቋሚ ነዋሪ ሆነው እዚያው ሞተው ተቀበሩ። ዛሬ ላይ ረሱል ﷺ ሲነሱ በማንም ሰው አእምሮ ቀድሞ የሚመጣው መዲና እንጅ መካ እስከማይሆን ድረስ! ረሱል ﷺ ከዚህም አልፈው የተሰደዱበት ሀገር ሰዎችን ይዘው የትውልድ ሀገራቸው «ዜጎች » ላይ ጦርነት ከፍተው ድል አድርገው ገብተዋል። በዘመኑ እስቤ ይህ «ባንዳነት» ይባላል! «እኛ ሳንሆን መጤው እስልምና ነው» ብለው ምላሽ የሚሰጡ ሰዎች ረሱልም ﷺእምነታቸውም መዲና ላይ መጤ ናቸው ማለት ነው ! ስለዚህ መጤነት ነውር ከሆነ ዲነል ኢስላም ለመዲና ሰዎች ነውር ነበር። ወይም ረሱል ﷺ ሰው ሀገር ላይ መጤና እምነታቸውም መጤ ነበር ማለት ነው ! የመዲና ሰዎች መጤ ስለሆናችሁ ሀገራችንን ልቀቁ ወይም መብታችሁን አናከብርም ቢሉ በነዚህ ሰዎች አስተሳሰብ ትክክል ነው ማለት ነው ! ከጅምሩ የአደም ልጆች ሁሉ የተፈጠሩበትን ዲን «መጤው እሱ ነው » ማለት በራሱ የዲናዊ እውቀት ሸፋፋነት እንጅ ሌላ አይደለም ! አላህ ምድርና ሰማያትን የፈጠረበትን እምነት መጤ ማለት በራሱ የዐቂዳ ፈሳድ እንጅ ሌላ አይደለም! ኢስላም በድንበርና በድንበር ላይ በተመሰረቱ ማንነቶች ሁሉ አያምንም ። ያ ባይሆን •ሙዐዊያ ከመካ ሻም ሄዶ አስተዳዳሪ አይሆንም ነበር! •ዐሊይ ኩፋ ላይ •ዐምር ኢብኑል ዐስ ግብፅ ላይ •አቡ ሙሳ አልአሽዐሪይ ዒራቅ ላይ •አቡ ሁረይራ በህረይን ላይ •አቡ ዑበይዳህ ፍልስጤም ላይ •አመውያ ኸሊፋዎች ቱርክና ስፔን ድረስ ሄደው አያስተዳድሩም ነበር። አይ መጤ እንዳንባል አርፈን መካችን ላይ እንኑር ብለው ይቀመጡ ነበር። እሽ ሰሃቦች ይህን ያደረጉት በዚህ ዘመን ቢሆን «ሰው ሀገር ሄደው እምነታቸውን ማስፋፋታቸው » አግባብ አይደለም ልንል ነው ? ወይስ መጤ ስለሆኑ ሀገራት ወደ ቦታቸው ይመልሷቸው ልንል? እኛ ኢትዮጲያውን ነን «ብለን» ለማሳመን የምንጥረው የሀገር ባለቤትነታችን እንዲታመንልን ነው አ ? ስለዚህ ሰሃቦች ከመካ ተነስተው ኢራቃዊ ፣ ሻማዊ ወይም ግብፃዊ ሳይሆኑ ሰው ሀገር ላይ መኖራቸው ጥፋት ነበር ማለት ነው ? ኢትዮጲያዊ ነን «ስንላቸው » የማይቀበሉን ከሆነ የሰው ልጆች ሁሉ የተፈጠሩበትን እምነት መጤው እሱ ነው እንድንል የፈቀደልንስ ማን ነው ? ኢማሙ አህመድ (ግራኝ) በኢስላማው ወንድማማችነት ትስስር ድንበር ተሻግሮ ሄዶ በቱርኮች ትብብር የሀገሩን አፄዎች መፋለሙስ ባንዳነት ነበር? ኢማሙ አህመድስ መጤ ነበር? ኢስላም ለምድር ሁሉ የወረደ ዲን ነው። እስልምናን በድንበርና በሐገርተኝነት ጠባብ አስተሳሰብ ጠርንፈን ከመረዳት እንውጣ ! ቴሌግራም :- t.me/ismaiilnuru
без подписи
ይመልሱ ይሸለሙ😀
без подписи
እውቀት የተጠማው የጠሮ መስጂድ ማህበረሰብ‼ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ላለፋት 5 አመታት ጠሮ ኡስማን ኢብኑ አፋን መስጂድን እያወኩ የነበሩ ጥቂት ግለሰቦች አየር ጤና እና ቤተል መስጂድ ሄዳቹ መቅራት ትችላላቹ እያሉ መሲጂዱ ላይ ቂርአት እንዳይቀራ (ትምህርት እንዳይሰጥ)፣ ማህበረሰቡ በሰራው መስጂድ አገልግሎት እንዳያገኝ አልፎም ገብቶ እንዳይሰግድ ሁሉ እንቅፋት ሲሆኑ ቆይተዋል። በምን አግባብ ነው ማህበረሰቡ ካለው ነገር ቀንሶ፣ እናቶች ወርቃቸውን ሽጠው፣ አባቶች እና ወጣቶች ስራቸውን ፈተው በስንት መስዋትነት የገነባውን መስጂድ ለጥቂቶች ትቶን አየር ጤና እና ቤተል ሄዶ ሚሰግደው እና ሚቀራው‼ ላለፋት 5 አመታት የአከባቢው ማህበረሰብ ትግስት አድርጎ ለመስጂዱ እና ለአከባቢው ሰላም ሲል በብዙ መስዋትነት ከገነባው መስጂድ ርቆ ሰላማዊ ትግል እያደረገ የቆየ ሲሆን አሁን ላይ ትግስቱ ፍሬ አፍርቶ በመጅሊስ አማካኝነት ህዝባዊ ኮሜቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ የገባ ሲሆን በሂደት እና በብስለት መስጂዱ ወደ ነበረበት የመመለስ ስራ እየሰሩ ይገኛሉ። የተሰጣቹን ሀላፊነት ተቀብላቹ ጊዜያቹን እና እውቀታቹን ሰውታቹ ማህበረሰቡን በቅንነት እያገለገላቹ ያላቹ ኮሜቴዎቻችንን ከልብ እያመሰገንን እውቀት የተጠማውን የመስጂዱን ጀመዓ ባጭር ጊዜ ወደ መማር ማስተማር የሚመለስበት ሁኔታ እንድታመቻቸው አደራ እንላለን። __________ የኡስማን ኢብኑ አፋን ጠሮ መስጂድ ወጣት ጀመዓ
የጠላቶቻን ብዛት፤ የኛ መዘናጋት!! ====================== አሁን ያሉት የመብታችን ጠበቆች ይህን ሁሉ ውርጅብኝ ችለው ሰው ሆነንና አንደ ሰው እየታየን በሃገሪቱ መብታችን ተከብሮ እንድንኖር አቅጣጫ እየሰጡ ደህና እየመሩን ነው። እኔ የማዝነው ለመጪው ትውልድ ነው። ይህን ሁሉ ሊውጠውና ሊሰለቅጠው የቋመጠ እንደ getachew shiferaw ያለ የቀን ጅብ እንዴት አድርጎ ይሆን የሚቋቋመውና አንድነቱን ጠብቆ የሚቆየው? በዚህ በኩል የኛዎቹ ሥልጣን ተነጠቅን በማለት ከሁሉም ብሰው ሰድበው ለሰዳቢ እየሰጡ ትንሽ ስንጥቅ በተፈጠረ ቁጥር በድዳቸው ይስቃሉ። ከመሃላችን ደሞ ቀርቷል፣ ያገናዝባል የምትለው በየጊዜው ፋዎል እየሠራ፤ ሌሎችን ለማስደሰት ፈውቀል ሃድ ተናዙል እያደረገና እየቃዠ ስንጥቃቱን ከፍ ወዳለ ንቃቃትና ሸለቆ ይቀይራል። alas! 🤔🤔🤔
• አትጨነቅ፤ መከራዎች ምንም ያህል ቢከብዱና ቢበዙ ዘላለም አይቆዩም ። የአላህ እዝነት ከሁሉም የላቀ ነው፣ እፎይታውም ቅርብ ነው። ስለዚህ ተስፋ አትቁረጥ፣አትጨነቅ፤ እንዲህም በል፦ " وقل ﻳﺎ ﺣﻲ ﻳﺎ قيوم ﺑﺮﺣﻤﺘﻚ أستغيث ! Copied
🎉✨ ታላቅ የምርቃትና የዳዕዋ ፕሮግራም✨ 🎓 ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ወሎ ቅርንጫፍ፣ደሴ ላለፉት 2 አመታት በዲፕሎማና በሰርተፍኬት መርኋግብር ሲያስተምራቸው የቆዩ ተማሪዎችን ለማስመረቅ የፊታችን ቅዳሜ ነሀሴ 2/2018 በወሎ ባህል አምባ አዳራሽ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ በደማቅ ሁኔታ ያስመርቃል። 🌹የፕሮግራሙ ተጋባዥ እንግዶቻችን ✅ ሸይኽ ኢልያስ አህመድ ✅ ሸይኽ ሙሀመድ ኢድሪስ ✅ ኡስታዝ አዩብ ደርባቸው እና ሌሎችም ታላላቅ መሻይኾችና ኡስታዞች ተጋብዘዋል። በዕለቱ በተመራቂ ተማሪዎች የሚቀርቡ አስደማሚና ምርጥ ምርጥ ፕሮግራሞች ተሰናድተዋል። 🌸 ለሴቶች በቂ ቦታ አለ! 📌 አይደለም መቅረት ማርፈድ ያስቆጫል‼️ 🕌 ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ወሎ ቅንርጫፍ፣ ደሴ ☘️ https://t.me/merkezunadessie
በልብ ህመም እየተሰቃዬ የሚገኘው አሳዛኝ ህፃን‼ ============================= (የቻለ አላህ ከሰጠው ላይ በመስጠት፣ ለሌሎች በመጠቆም፣ በመልካም ዱዓችሁና ሼር በማድረግ ለተጨነቀች ነፍስ ሰበብ እንሁን!) || ✍️ ከታች በፎቶው ላይ የምትመለከቱት የሚያሳሳ ህፃን ገና የ7 ወር ጨቅላ ነው። በዚህ እድሜው በከባድ የልብ ህመም (Tetralogy of Fallot) እየተሰቃየ ይገኛል። በምስሉ ላይ እንደምታዩት የአፍንጫ የኦክስጅን ቱቦ ተገጥሞለት በሆስፒታል አልጋ ላይ ነው። የተደረገለት የኢኮካርዲዮግራፊ (Echocardiography) ምርመራ ውጤት እንደሚያሳየው ህፃኑ የሚከተሉት ከባድ የልብ ችግሮች አሉበት፡ 1⃣ Tetralogy of Fallot (TOF): በልብ ላይ የሚከሰቱ አራት አይነት ተያያዥ ጉድለቶች ያሉት ውስብስብ የልብ ህመም አይነት ነው። 2⃣ VSD (በልብ ግድግዳ ላይ ቀዳዳ): ከልብ ክፍሎች መካከል ባለው ግድግዳ ላይ ቀዳዳ አለ። 3⃣ RV Hypertrophy (የቀኝ የልብ ክፍል ጡንቻ ውፍረት): ከልብ ፓምፕ የማድረግ ሂደት ጋር በተያያዘ የቀኝ የልብ ventricle ጡንቻ ወፍሯል። 4⃣ Severe RVOTO / Hypoplastic pulmonary valve: የሳንባ ቫልቭ በጣም ጠባብ በመሆኑ ደም ወደ ሳንባ መሄድ በጣም ተቸግሯል። 5⃣ Aorta overrides the VSD 50%: ዋናው የደም ቧንቧ (Aorta) በተሳሳተ ቦታ በመውጣቱ ከ VSD ቀዳዳ 50% በላይ ደም ይወስዳል። ይህ ሁሉ በዚህ በሚያሳሳ የ7 ወር ጨቅላ ላይ የተከሰተ ነው። 🎀 የሕክምና ባለሙያዎች እንዳረጋገጡት ይህ ህመም በአስቸኳይ በልብ ቀዶ ህክምና ( surgery) መታከም አለበት። አለበለዚያ ለህይወቱ አስጊ ነው። ቤተሰቦቹ የህክምና ወጪውን ለመሸፈን አቅም የላቸውም። ስለሆነም እናንተ ደጋግ ኸይር ፈላጊዎች፣ ወላጅ አባትና እናት ልጃቸውን በሞት እንዳያጡ እባካችሁን እጃችሁን ዘርጋላቸው። አቅማችሁ የፈቀደውን ያህል በማበርከት የዚህን ጨቅላ ህይወት እንታደግ። የወለደ ልብ ይረዳዋልና፣ የልጅ ስቃይ ያማልና እባካችሁን እንደ አቅማችሁ ተባበሯቸው። ✅ ለድጋፍ የሚሆን የባንክ አካውንት፡ ✅ንግድ ባንክ (Commercial Bank of Ethiopia - CBE) ✅ የአካውንት ስም፡ Mudin Awol Hassen ✅ የአካውንት ቁጥር፡ 1000649713522 ✅ ቴሌ ብር: 0910489484 ሁላችሁም በምትችሉት መልኩ ተባበሩት። የተጠየቁት 3.5 ሚሊዮን ነው። እስካሁን ያሰባሰቡት ገና 500 ሺህ ብር ብቻ ነው። ለአላህ ብለን እንተባበራቸው። ለኸይር ማነሳሻ እንድጠቀመው የምትሰድቁበትን ደረሰኝ በውስጥ መስመር @MuradTadesseBot ላይ ላኩልኝ። || t.me/MuradTadesse
በመጨረሻም መጅሊሱ ከ 4 ወራት በላይ የፈጀ ውይይት በማድረግ ከመስጂዱ ማህበረሰብ በመስጂዱ ምስረታ እና ግንባታ ንቁ ተሳትፎ የነበራቸውን ግለሰቦች፣ ምሁራን፣ወጣቶችን እና በአከባቢው ማህበረሰብ ትልቅ ቦታ ያላቸውን አባቶችን በማዋቀር አዲስ ኮሜቴ ሰይሞ ወደ ስራ አስገብቷል። የተመረጣቹ አስተዳደሮች መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቹ እየተመኘን ማህበረሰቡ እና መጅሊሱ የጣለባቹን ሀላፊነት በአግባቡ እንድትወጡ አደራ እያልን አላህ ኸይሩን ሁሉ እንዲወፍቃቹ ዱኣችን ነው። ማህበረሰቡ ድምፁን ሰጥቶ የመረጣቸው የመጅሊስ አመራሮች እና የፀጥታ ክፍል ሀላፊዎች ለመስጂዱ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የመስጂዳችን ችግሮች በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት እና መስጂዱ ወደነበረበት ለመመለስ ላደረጉት ያላሰለሰ ጥረት ጀመዓችን ላቅ ያለ ምስጋና ያቀርባል። __________ የኡስማን ኢብኑ አፋን ጠሮ መስጂድ ወጣት ጀመዓ
без подписи
без подписи
без подписи
🎉 እንኳን ደስ አላቹ 🎉 ጠሮ ኡስማን ኢብኑ አፋን መስጂድ የአህባሽ ቡድን በፈጠረው ግር ግር ያለ ህጋዊ አስተዳደር ኮሜቴ ከአራት አመታት በላይ በጥቂት ጉልበተኛች እጅ ወድቆ ማህበረሰቡ ከገነባው መስጂዱ ተገሎ የመስጂዱ ኢማም ከሚናው ተገለው፣ ማህበረሰቡ ለዓመታት ይከታተለው የነበረው የዒልም ትምህርት በኃይል ቆሞ፣ ልጆች ከመድረሳ ተባረው በጥቅሉ መስጂዱ የጥቂት ስግብግቦች ሀብት ማካበቻ ሆኖ ቆይቷል። ማህበረሰቡ በዱላ የተነጠቀውን መብት በዱላ ማስመለስ እየቻለ ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ህግ እና ስርአት ተከትሎ መብቱን ለማስከበር እና የገነባውን መስጂዱን ወደነበረበት ለመመለስ ፅኑ ትግል ሲያደርግ ቆይቷል። በየ እርከኑ ያሉ የመጅሊስ አመራሮች ሆደ ሰፊ ሆነው እነዚህን ፅንፈኛች አቅርቦ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ሙከራ ያደረጉ ቢሆንም እንቢተኛ ሆነው ስብሰባዎችን ሁሉ ረግጠው በመውጣት ለመጅሊሱ ያላቸውን ንቀት ሲያንፀባርቁ ቆይተዋል። ከዚህም አልፎ እነሱ ሰብሳቢ ያደረጉዋቸውን አቶ አብዱልሀዲን ዋና ሰብሳቢ በማደረግ ሁሉንም ያካተተ ህዝባዊ ኮሜቴ አዋቅሮ ያወረደ ቢሆንም እነዚህ አንባገነኖች ከኛ አስተሳሰብ ውጭ ያለ አንድም ሰው ቢሆን ኮሜቴ ላይ እንዲቀላቀልብን አንፈቅድም በማለት የሀይማኖት ፅንፈኝነታቸውን እና ለመጅሊሱ ያላቸውን እንቢተኝነታቸውን ዳግም አረጋግጠዋል።
ሰበር ዜና‼ የጠሮ መስጂድ ማህበረሰብ የ 5 አመታት የፅናት እና የሰላማዊ ትግል ልፋት በዛሬው እለት ፍሬ አፍርቶ መስጂዱን የሚያስተዳድር ህዝባዊ ኮሜቴ በመጅሊስ አማካኝነት ተዋቅሮ ወደ ስራ ገብቷል። እንኳን ደስ አላቹ‼ አንኳን ደስ አለን‼
⚠️ ለሰለፊይ ወንድሞች የቀረበ የትዳር ማሳሰቢያ ⚠️ 🥀 ስንትና ስንት የሱና (ሰለፊይ) እህቶች አሉ፤ በትክክለኛው መንገድ ላይ ያለን ሰለፊይ ወንድ በትዕግስት በመጠበቅ እድሜያቸው 30 ዓመትና ከዚያም በላይ የዘለለ? ነገር ግን ሰለፊይ የሆነው ወንድ ጋብቻን ፈልጎ በሚመጣበት ጊዜ፣ የእነዚህን እህቶች ጽናትና ዲን ከማየት ይልቅ እድሜዋ ገና ለጋ የሆነችን (ትንሽ) ብቻ ይመርጣል። 💎 አንተ ሰለፊይ ወንድ ሆይ! ከማንኛውም ሰው ይበልጥ የአላህን መልክተኛ (صلى الله عليه وسلم) ትእዛዝ በተግባር ልትተገብር የሚገባህ አንተ ነህ። በትዳር ምርጫ ውስጥ ትልቁ መስፈርት ዲን መሆኑን ልትዘነጋ አይገባም። 📜 የአላህ መልክተኛ (صلى الله عليه وسلم) እንዲህ ብለዋል፦ «ባለ ዲኗን (ሃይማኖተኛዋን) ምረጥ ካልሆነ ግን፤ (እጅህ በአፈር ትለቅለቅ/አመድ አፋሽ ትሁን)»ብለዋልና። ስለዚህ እንደ በኒ እስራኤል ላም መስፈርት በማብዛትና እድሜ ላይ ብቻ በማተኮር በሐቅ ላይ የጸኑ እህቶችን አታሳቅቅ ። አላህ (سبحانه وتعالى) ለወጣቶቻችን በሙሉ ሷሊህ (ደግ) የትዳር አጋርን ይወፍቃቸው። ማንኛውንም ሰው ከጋብቻ ጸጋና እንዲሁም ከመልካም 'ተዓዱድ' (ከአንድ በላይ ከማግባት) በረካ አይከልክለው ። Copied from Abu_hibetillah_Asselfiy
без подписи
ዑዝር ስጡት የሚባልለት ኡማ ☛እግር ኳስ ስንት ሰአት እንደሚጀመር ያውቃል ☞ማን ከማን እንደሚጋጠም ያውቃል ☛በሁለቱ ቡድኖች ማን ኮከብ ተጫዋች እንዳለ ☞የፍልሚያ ሰአቱ በኛ ሰአት አቆጣጠር ሲቀየር ☛ስንተኛው ደቂቃ ላይ እንዳስገባ ☞የእግር ኳስ ተጫዋች ሚስቶችን ስም ☛የሚነዱትን መኪና ☞የሚወዱትን ምግብ ☛የሃብት መጠናቸውን ☞ስንት ዋንጫ እንደተሸለመ ☛የቀድሞ «ፍቅረኛውን» ስም ☞የደመወዙን መጠን ☛የሚያዘወትረውን ጫማ ☞የሚጠቀመውን ብራንድ በዱንያ ላይ የተገኘበትን ትልቁን የህይወት ግብ ተውሂድን ግን ባለማወቁ ዑዝር እንዲሰጠው ይፈልጋል! ምክንያቱም በእግር ኳስ ቢዚ ስለሆነ ተውሒድንና ነዋቂዶቹን የሚማርበት ሰአት ሰለሌለው ..