EthiopikaLink/ኢትዮጲካሊንክ
СтатистикаOne of the best Radio shows in Ethiopia...And we are on air every Tuesday, Thursday and Saturday from 3pm - 5pm on Arada FM 95.1 Dm- @EthiopikaLink1
- Последний пост
- 15 авг.
- Последнее чтение
- 14 авг.
- Постов за неделю
- 1
- Всего постов
- 21
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 282
- 1/48двое суток
- 323
- 1/72трое суток
- 348
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ምን ተሻለ?
ምን ተሻለ?
ምን ተሻለ?
ምን ተሻለ?
ምን ተሻለ?
ምን ተሻለ?
ምን ተሻለ?
በሕይወታችን ውስጥ ውሳኔ ለመወሰን የሚያስቸግሩ፣ በሃሳብ ተወጥረን “ምን ይሻላል?” የምንልባቸው ብዙ ሁኔታዎች ያጋጥሙናል። በፍቅር፣ በቤተሰብ፣ በሥራ፣ በጓደኝነት ወይም በማንኛውም የሕይወት ምርጫ ላይ ግራ ተጋብተዋል? እርስዎን ውሳኔ ለመወሰን ያስቸገረዎትን እና ግራ ያጋባዎትን ማንኛውንም ታሪክ በፌስቡክ መልዕክት ሳጥናችን (Facebook DM) ላይ “ምን ተሻለ” ብለው ይላኩልን። ከምትልኩልን ታሪኮች ውስጥ የተመረጡትን በፌስቡክ ገፃችን ላይ እናጋራለን። ተከታዮቻችን በኮሜንት ላይ የራሳቸውን ሃሳብና ምክር ያካፍሉዎታል፤ እኛም በሬዲዮ ላይ በማቅረብ የራሳችንን እይታ እና ምክር የምናካፍል ይሆናል። እናመሰግናለን! https://www.facebook.com/share/1DRtspndUt/
ድምፃዊ አሕመድ ማንጁስ የገንዘብ ቅጣት ተወሰነበት በሰው ላይ ጥቃት በማድረስ የተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ማንጁስ የ300 ብር ቅጣት እንዲከፍል ተፈረደበት፡፡ በሴት ልጅ ላይ አካላዊ ጥቃት በማድረስ ወንጀል በተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ሁሴን (ማንጁስ) ላይ የገንዘብ ቅጣቱን ያስተላለፈው ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ነው። ድምፃዊው ለዚህ ቅጣት የተዳረገው የካቲት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከንጋቱ 12: 10 ሰአት ላይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ስታር በተባለ ሆቴል ውስጥ የግል ተበዳይ የሆነችው መድሃኒት ይልማ ላይ ጥቃት ፈፅሞ ጥፋተኛ በመባሉ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ አብራርቷል። ፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔውን ከመስጠቱ በፊት የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት የመረመረ ሲሆን አቃቤ ህግ ወንጀሉ የተፈፀመው በሴት ላይ በመሆኑና ተከሳሽ ድርጊቱን የፈፀመው በምሽት በመሆኑ ቅጣቱ ሊከብድበት ይገባል ሲል አመልክቷል። ተከሳሽ በበኩሉ ቀደም ሲል የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑ፣ ድርጊቱን መፈፀሙን አምኖ በመፀፀቱ እንዲሁም የሁለት ልጆች አባትና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆኑን በመጥቀስ የሚጣልበት ቅጣት እንዲቀልልት ጠይቋል። ፍርድ ቤቱ በውሳኔው የአቃቤ ህግን የቅጣት ማክበጃ በመተው ተከሳሹ ያቀረባቸውን የቅጣት ማቅለያዎች ተቀብሎ የእስር ቅጣቱን ወደ ገንዘብ ቅጣት ቀይሮለታል። በዚህም መሰረት ተከሳሹ 300 ብር (ሦስት መቶ ብር) የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል እንደተወሰነበት ፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ ተመልክተናል። ተከሳሹ የገንዘብ ቅጣቱን እንደከፈለ የዋስትና ገንዘቡ ተመላሽ ተደርጎለት ከእስር እንዲፈታም ታዟል። (ኢትዮጲካሊንክ)
የኢትዮጲካሊንክ ዜና በፊንቴክ ማጭበርበር የተጠረጠሩት ክስ ተመሰረተባቸው አቃቤ ህግ ከመንሱር ጀማል ውጭ ሌሎቹ በዋስ ቢለቀቁ እንደማይቃወም ገልጿል በፊንቴክ ኢንቨስትመንት የመኪና ግዢ ማጭበርበር የተጠረጠሩ ስድስት ታዋቂ አርቲስቶችና ቲክቶከሮች ዛሬ በከፍተኛው ፍርድ ቤት አራተኛ ልዩ ልዩ ችሎት ክስ ቀረበባቸው። አቃቤ ህግ በተከሳሾቹ ላይ የሶሻል ሚዲያን ታዋቂነትን በመጠቀም፣ በሚዲያ እንዲታዩ በማድረግና የሰው እምነት በመገንባት ህዝብን የማሳሳት ወንጀል ፈጽመዋል በሚል ክስ መስርቶባቸዋል። የቀረበባቸው ክስ የአምስት ዓመት እስርና የ50 ሺህ ብር መቀጮ ድረስ የሚያስቀጣ መሆኑም በክሱ ላይ ተጠቅሷል። ዛሬ ረቡዕ ሚያዚያ 28 ከቀኑ 9 ሰዓት በተሰየመው ችሎት ክሱ ከተነበበ በኋላ አስተያየት የሰጡት የተከሳሽ ጠበቆች የቀረበባቸውን ክስ እንደማይቃወሙ ጠቅሰው ዋስትና እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። አቃቤ ህግ በበኩሉ ከአምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል ውጪ በሌሎች ተከሳሾች ላይ የዋስትና ተቃውሞ እንደሌለው ምላሽ ሰጥቷል፡፡ በክስ ዝርዝሩ ላይ እንደተመለከተው አምስቱ ተከሳሾች ከላይ የተጠቀሰው አንድ ክስ የቀረበባቸው ሲሆን በአቶ መንሱር ጀማል ግን አምስት የተለያዩ ክሶች ተዘርዝረዋል፡፡ አቃቤ ህግ የአቶ መንሱርን ዋስትና የተቃወመው "ግለሰቡ በድርጅቱ ውስጥ በዋነኛነት ዋና ተግባር ነበረው፤ ፌንቴክ ኢንቨስትመንት 1.9 ቢሊየን ብር በማጭበርበሩ ላይ ዋና ተዋናይ ነበር። በዋስ ከወጣ ምስክሮችን ያባብልብናል፤ ሌላ ወንጀል ሊፈጽም ይችላል፤ ስንይዘውም በከባድ ሁኔታና በመከራ ነበር የተያዘው፤ ገንዘብ አስይዞ በዋስ ወጥቶ ሊጠፋ ይችላል" የሚሉ ምክንያቶች በመጥቀስ ነው። አቃቤ ህግ በሌሎቹ ተከሳሾች ላይ በተሰጠው አስተያየት “የተጭበረበረው 1.9 ቢሊየን ብር እንደመሆኑ ያንን መጠን ግምት ውስጥ ያስገባ የገንዘብ ዋስ አስይዘው ቢወጡ አልቃወምም፤ ነገር ግን ከሀገር እንዳይወጡ እግድ ይሰጥልኝ” ሲል ጠይቋል። ለዚሁ የአቃቤ ህግ ሃሳብ የተከሳሽ ጠበቆች ተቃውሞ አቅርበዋል፡፡ “ተከሳሾች ከሃገር አይውጡ የሚለውን አንደገፍም፤ በሥራ ምክንያት በተደጋጋሚ ወደ ውጭ ሃገራት ስለሚጓዙ የሥራቸው ሁኔታ ታሳቢ ሊደረግ ይገባል፡፡ እንዲሁም ገቢያቸው አነስተኛ ስለሆነ የዋስትና ገንዘቡ መጠን ላይ አስተያየት ሊደረግ ይገባል” ሲሉ አብራርተዋል፡፡ በዚህ መሰረት ፍርድ ቤቱ አምስቱ ተከሳሾች ሊያስይዙት የሚገባ የዋስ ገንዘብ መጠንና የጉዞ እገዳ ጉዳይ ላይ ለመወሰን እንዲሁም አቃቤ ህግ በፅሁፍ እንዲያቀርብ የተጠየቀውን የአቶ መንሱር ጀማልን ዋስትና የተቃወመበትን ምክንያት ሰምቶ ውሳኔ ለመስጠት ለመጪው ሰኞ ግንቦት 3 ረፋድ አምስት ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቶ የዛሬው ችሎት ተጠናቋል።
በአሁኑ ወቅት የፍቺ ቁጥር እንዲጨምር ያደረገው ዋናው ምክንያት ምንድን ነው ብለው ያስባሉ?🤔
በአሁኑ ወቅት ስለ ትምህርት አስፈላጊነት ያለዎት አመለካከት የትኛው ነው?🤔
በአብዛኛው የትኛው የተለመደ ይመስላችኋል?
በአብዛኛው በትዳር ተጠቃሚና ደስተኛ የሚሆነው ማን ይመስላችኅል?🤔
በፍቅር ግንኙነት ላይ የጥንዶቹ ተመሳሳይ ዝንባሌ (hobby) መኖር ምን ያህል አስፈላጊ ነው ብለው ያስባሉ?🤔
ታዋቂ መሆን ሕይወትን ያቀላል ብለው ያስባሉ?
የሚፈልጉት ቢሟላልዎት የት መኖር ይመርጣሉ?🤔
ከስራ ባልደረቦች ጋር ጓደኛ መሆን አስፈላጊ ነው?🤔
ስለ የርቀት የፍቅር ግንኙነት ምን ያስባሉ?🤔
አይ ሾው ስፒድ በኢትዮጵያ ስለነበረው ቆይታ ምን ያስባሉ?🤔