SOS HGS & KG, Harar Learning Center since 2020
СтатистикаThis is Official SOS HGS & KG ,Harar Telegram Channel. *Designd for Students at any class level in order to address such * Short Notes * Exams * Supplementary Materials like Videos, voices, Photos Cont: 0932301038/0910669638/ 0912691010
- Последний пост
- 16 июл.
- Последнее чтение
- 14 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 23
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- В каталоге с
- 14 авг.
- 1/24сутки в ленте
- —
- 1/48двое суток
- —
- 1/72трое суток
- —
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
የ2019 የትምህርት ዘመን የትምህርት ክፍያ 1. ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ = 2550 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር= 3050 2. ከ3ኛ-8ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ = 2220 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 2720 3. 2ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ = 2400 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 2900 4. 1ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ = 2550 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 3050 5. ኬጂ 3 ወርሃዊ ክፍያ = 2550 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 3050 6. ኬጂ 2 ወርሃዊ ክፍያ = 2600 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 3100 7. ኬጂ 1 ወርሃዊ ክፍያ = 2800 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 3300 ፨ከ1ኛ -12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የጽዳትና የመጽሐፍ ኪራይ ክፍያ ት/ቤት የሚከፈል ይሆናል። ልጅዎን ሲያስመዘግቡ የመስከረም ወርና መመዝገቢያ በተማሪው/ዋ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥር 1000203028869 ገቢ ማድረግ ይኖርብዎታል። የነባር ተማሪዎች የመመዝገቢያ ጊዜ ከሐምሌ 8 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ብቻ መሆኑን እያሳወቅን በተሰጠው ጊዜ ባልተመዘገበ ተማሪ ቦታ አዲስ ተማሪ የምንቀበል መሆኑን እንገልጻለን። ትምህርት ቤቱ
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
ለኤስ ኦ ኤስ ሔርማን ግማይነር ት/ቤት ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ፡ የሐረር ኤስ ኦ ኤስ ሄርማን ግማይነር ት/ቤት የ2018 ዓ.ም የወላጆች በዓል እንዲሁም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የምረቃ መርሃ ግብር ቅዳሜ ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ስለሆነም በዕለቱ ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ ውድ ተመራቂ ተማሪዎቻችንና የተመራቂ ተማሪ ወላጆች ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ እንድትገኙ ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን ። ትምህርት ቤቱ
Dear all, Both grade 6 & 8 Students scored a remarkable result. To our Amazing Students especially Grade 6: Congratulations on your exceptional performance! Your discipline, perseverance, and determination have truly paid off. You have made our school incredibly proud, and these outstanding regional scores are a testament to your bright futures. Keep reaching for the stars! To our Dedicated Teaching Staff: Thank you for your tireless efforts, patience, and passion. Your commitment to nurturing these young minds and providing high-quality guidance has been the driving force behind these brilliant results. You have empowered our students to reach their full potential. Once again, congratulations to our entire school community! Let this milestone be just the beginning of many great accomplishments to come. Note: All Our Grade 6 students promoted.(100% passed), And, 97% of Grade 8 students scored a remarkable result.
የሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤትን ዛሬ ይፋ ተደረጉዋል። 👉 ውጤታችሁን እንዴት ማየት ትችላላችሁ? የተማሪዎችን ውጤት ለማየትና ለማረጋገጥ ቢሮው ባዘጋጀው ይፋዊ የኦንላይን ፖርታል (ሊንክ) በመግባት የፈተና መለያ ቁጥራችሁን (Registration Number) በማስገባት በቀላሉ መመልከት ትችላላችሁ። 👇የውጤት ማያ ገጽ ሊንክ፦ ለ6ኛ ክፍል https://harari6.ministry.et/#/ ለ8ኛ ክፍል https://harari.ministry.et/login#/ 👉 ተማሪዎቻችን በሙሉ መልካም ውጤት እንዲሆንላችሁ ከልብ እንመኛለን!
መልዕክት ለተማሪ ወላጆች በሙሉ አንዳንድ ተማሪዎች ዝግጅት አለን በማለት ከወላጅ ገንዘብ እየጠየቁ እንደሆነ ከአንዳንድ ወላጆች ለመገንዘብ ችለናል። ይሁን እንጅ ምንም አይነት የተፈቀደ ዝግጅትም ሆነ ጉዞ የሌለ መሆኑን እናሳውቃለን ። ትምህርት ቤቱ
ለ 8ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች ጠቃሚ ማሳሰቢያ ✅ የፈተና መታወቂያ ካርድ ይያዙ። ✅ ከፈተናው 30 ደቂቃ በፊት በፈተና ጣቢያ ይገኙ። ✅ HB 2 እርሳስ፣ ማጥፊያ እና መቅረጫ ብቻ ይያዙ። ✅ የተማሪ መለያ ቁጥርና የትምህርት መለያ ቁጥርን በትክክል ይሙሉ። ✅ መልሶችን በተሰጠው ክብ ውስጥ ብቻ በጥንቃቄ ያጥቁሩ። ✅ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም ነገር አይፃፉ። ❌ ሞባይል፣ ስማርት ሰዓት እና ሌሎች ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች አይፈቀዱም። ❌ ኩረጃ፣ ያልተፈቀዱ ወረቀቶች እና ያለ ፈቃድ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው። 🎯 መመሪያዎቹን በአግባቡ በመከተል የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ እንመኛለን!
видео или голосовое, без подписи
08/10/2018 ለት/ቤቱ ተማሪዎችና ወላጆች ት/ቤቱ የአመቱን የትምህርት ሂደት እያጠናቀቀ በመሆኑ ተማሪዎች የተዋሷቸውን የት/ቤት መጽሐፍት እየመለሱና ያለባቸውን ወርሃዊ ክፍያ በጊዜ እያጠናቀቁ ክሊራንስ ወረቀት እየተሰጣቸው መሆኑ ይታወቃል። ይሁንና አንዳንድ ተማሪዎች የተሰጣቸውን የክሊራንስ ወረቀት አስፈርመው ያልጨረሱ በመሆኑ ወደ ፈተና የመግቢያ ክሊራንስ ወረቀት እንዳያጡ ወላጆች ከወዲሁ እንድታግዟቸውና ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ ት/ቤቱ በጥብቅ ያሳስባል። የተ/ቤቱ አስተዳደር
видео или голосовое, без подписи
01/10/2018 ለ 8ኛ ክፍል ተማሪዎችና ወላጆች የአንደኛ ደረጃ ት/ቤቱ የክልላዊ ሚኒስትሪ ፈተና መፈተኛ ጣቢያ በመሆኑ ከሰኔ 1-5 እንዲሁም 11-12 /2018 ዓም ድረስ ከ1ኛ-5ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች ዝግ መሆኑ ይታወቃል። ይሁንና ለ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ባለው ቦታና የዝግ ጊዜ የትምህርት ይዘት ማጠናቂያና ማጠናከሪያ ትምህርት መስጠት ስለሚገባ ከነገ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓም ጀምሮ ተማሪዎች በተሻለ ሁኔታ ለመማር ተዘጋጅተው እንዲመጡ እየገለፅን ፣ ወላጆችም ለተግባራዊነቱ ክትትል እንድታደርጉ በቅድሚያ እናሳስባለን። የት/ቤቱ አስተዳደር
⏩ ለማስታወስ ያህል ወላጆች እና ተማሪዎች ስለ 6ተኛ ክፍል ፈተና ማወቅ ያለባቸው ተግባራት ⏩የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ ስር የሚሰጠውን የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በሚወስዱበት ወቅት የፈተናውን ጥራት ለመጠበቅና የተሳካ የፈተና ሂደት እንዲኖር ከተማሪዎች የሚጠብቃቸው ዝርዝር ተግባራት በሚከተሉት ዋና ዋና ተግባራትና ስነ-ምግባራት: 👉 ከፈተናው በፊት የሚጠበቁ ተግባራት ⏩መታወቂያ (Admission Card) መያዝ፦ ተማሪዎች ወደ ፈተና ጣቢያ ሲመጡ በፎቶግራፍ የተረጋገጠውንና የፈተና ቁጥራቸውን የያዘውን መታወቂያ ካርድ መያዝ ይኖርባቸዋል። ⏩በሰዓቱ መገኘት፦ ፈተናው ከመጀመሩ ቢያንስ ከ30 ደቂቃ በፊት በፈተና ጣቢያውና በተመደበው ክፍል ውስጥ ተገኝቶ ቦታን መያዝ ያስፈልጋል። ⏩የመፈተኛ ቁሳቁሶችን ማዘጋጀት፦ ለፈተናው የሚያስፈልጉ እንደ እርሳስ (HB 2 Pencil)፣ ላጲስ እና መቅረጫ የመሳሰሉ ህጋዊ ቁሳቁሶችን ብቻ ይዞ መገኘት። 👉 በፈተና ወቅት የሚጠበቁ ተግባራት ⏩የፈታኞችን መመሪያ መስማት፦ የክፍሉ ፈታኝ መምህራን የሚሰጡትን የቃልም ሆነ የጽሑፍ መመሪያዎችን በትዕግስት ማዳመጥና መተግበር። ⏩የግል መረጃን በትክክል መሙላት፦ በፈተናው ወረቀት ወይም የመልስ መስጫ ካርድ (Answer Sheet) ላይ ስም፣ የፈተና ቁጥር (Registration Number) እና ሌሎች መረጃዎችን በጥንቃቄና በትክክል መጻፍ። ⏩ኩረጃን በፍፁም መራቅ፦ የትምህርት ቢሮው "ኩረጃን የሚፀየፍ ትውልድ" ለመፍጠር በትኩረት እየሰራ በመሆኑ፣ ከሌላ ተማሪ ለመቅዳት መሞከር፣ የራስን መልስ ለማሳየት መሞከር ወይም መቅዳት የተከለከለ ነው። ⏩በራስ መተማመንና ፀጥታን መጠበቅ፦ በፈተና ክፍሉ ውስጥ ሙሉ ፀጥታን በመጠበቅ፣ በስነ-ልቦና ተዘጋጅቶ ፈተናውን በግል ጥረት ብቻ መስራት። 👉 በፈተና ክፍል ውስጥ የተከለከሉ ተግባራት ⏩ሞባይልና ኤሌክትሮኒክስ መያዝ የተከለከለ ነው፦ ማንኛውንም አይነት ተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ወይም ሌላ የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ መሳሪያ ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በፍፁም አይፈቀድም። ⏩ያልተፈቀዱ ወረቀቶችን አለመያዝ፦ ከፈተናው ጋር ንክኪ ያላቸውን ማስታወሻዎች፣ መጽሐፍት ወይም የተጻፉ ወረቀቶች ይዞ መገኘት ከፈተና ያሳግዳል። ⏩ያለፈታኝ ፈቃድ አለመንቀሳቀስ፦ ፈተናው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ ያለ ፈታኝ መምህሩ እውቅና እና ፈቃድ ከወንበር መነሳትም ሆነ መውጣት አይቻልም። ⏩ተማሪዎች እነዚህን ደንቦች በአግባቡ በመተግበር ክልላዊ ፈተናቸውን በሰላም አጠናቀው የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ ያሳስባል።
በሀረሪ ክልል የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናዎች ከሰኔ 02-12/2018 ዓ.ም ይሰጣሉ። - የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ6ኛ ክፍል ፈተና ➫ ከሰኔ 02 እስከ 04/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ የ8ኛ ክፍል ፈተና ➫ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ በክልሉ 6,418 የ6ኛ ክፍል እና 4,624 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በተገለፁት ቀናት ፈተናቸውን እንደሚወስዱ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አርሰላን አብዲ ተናግረዋል፡፡ @tikvahuniversity
ለኤስ ኦ ኤስ ት/ቤት ተማሪዎችና ወላጆች ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም መደበኛ የትምህርት ስራ የሚቀጥል መሆኑን እናሳውቃለን ። ትምህርት ቤቱ
ለኤስ ኦ ኤስ ት/ቤት ተማሪዎች በሙሉ ሰኞ ግንቦት 17 2018 ዓ/ም በሐረር ከተማ በሚደረግ ሰልፍ ምክንያት ትምህር የማይኖር መሆኑን እያሳወቅን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የሰልፉ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል ። ት/ቤቱ
видео или голосовое, без подписи
#ጥቆማ " ለስልጠናው ከ11 ዓመት ጀምሮ ያሉ ታዳጊዎች፣ ወጣቶች መመዝገብ ይችላሉ " - INSA የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) 5ኛውን የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ በስድስት ዩኒቨርሲቲዎች ሊሰጥ መሆኑን ገልጿል። የአስተዳደሩ የሳይበር ልህቀት ማዕከል ዳይሬክተር አቶ ቢሻው በየነ እንደገለጹት፤ ካምፑን በክልል ዩኒቨርሲቲዎች ለማካሄድ የታቀደው የ«ዲጂታል አካታችነት» (Digital Inclusion) መርህን በመከተል ሰልጣኞች ባሉበት አካባቢ የሥልጠና ዕድሉን እንዲያገኙ ለማስቻል ነው። እስካሁን ባለው ሂደት ከ4 ሺ 551 በላይ ክህሎት ያላቸው ወጣቶች ለሥልጠናው መመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። ለአንድ ወር በሚቆየው ስልጠና የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ተከታታይ የሆኑ ስልጠናዎችን የሚሰጡ ሲሆን የስልጠናው ማብቂያ ላይም ፕሮጀክቶችን የሚሰሩ ይሆናል። ስልጠናው :- • ሳይበር ደህንነት (Cyber Security) • ሶፍትዌር ዴቨሎፕመንት(Software Developmet) • ኤምቤድድ ሲስተም (Embedded System) • ኤሮስፔስ (Aerospace) • ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ (Emerging Technology) ዘርፎችን ያካተተ ነው። ለስልጠናው ከ11 ዓመት ጀምሮ ያሉ ታዳጊዎች ፣ ወጣቶች መመዝገብ ይችላሉ የተባለ ሲሆን ነገር ግን ከዛ በታችም ሆነው ተቋሙ የሚፈልጋቸው ልዩ ክህሎቶችን ይዘው ቢገኙ ተቀባይነት የሚያገኙበት እድል ይኖራል ተብሏል። የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ ቴክኖሎጂን መግዛት ብቻ በቂ እንዳልሆነ የገለጹት አቶ ቢሻው፤ በሀገር በቀል እውቀት የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ለሀገራዊ ደህንነት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። ይህ መርሃ ግብርም «ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030» ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግና ብቁ የሳይበር ሠራዊት ለመገንባት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተጠቁሟል። የዘንድሮው የሰመር ካምፕ ስልጠና የሚሰጥባቸው ማዕከላት ፦ * አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ * ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ * ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ * ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ * ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እና * ጅማ ዩኒቨርሲቲ ናቸው። ለሥልጠናው ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች እስከ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በድረ-ገጽ https://ctc.insa.gov.et/registration መመዝገብ የሚችሉ ሲሆን፤ ወላጆችም ልጆቻቸውን በማስመዝገብ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи