- Последний пост
- 16 июл.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 20
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- В каталоге с
- 15 авг.
- 1/24сутки в ленте
- —
- 1/48двое суток
- —
- 1/72трое суток
- —
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
የ2019 የትምህርት ዘመን የትምህርት ክፍያ 1. ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ = 2550 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር= 3050 2. ከ3ኛ-8ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ = 2220 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 2720 3. 2ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ = 2400 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 2900 4. 1ኛ ክፍል ወርሃዊ ክፍያ = 2550 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 3050 5. ኬጂ 3 ወርሃዊ ክፍያ = 2550 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 3050 6. ኬጂ 2 ወርሃዊ ክፍያ = 2600 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 3100 7. ኬጂ 1 ወርሃዊ ክፍያ = 2800 ፤ መመዝገቢያ = 500 ድምር = 3300 ፨ከ1ኛ -12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች የጽዳትና የመጽሐፍ ኪራይ ክፍያ ት/ቤት የሚከፈል ይሆናል። ልጅዎን ሲያስመዘግቡ የመስከረም ወርና መመዝገቢያ በተማሪው/ዋ ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቁጥር 1000203028869 ገቢ ማድረግ ይኖርብዎታል። የነባር ተማሪዎች የመመዝገቢያ ጊዜ ከሐምሌ 8 እስከ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ብቻ መሆኑን እያሳወቅን በተሰጠው ጊዜ ባልተመዘገበ ተማሪ ቦታ አዲስ ተማሪ የምንቀበል መሆኑን እንገልጻለን። ትምህርት ቤቱ
ለ2019 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ፡ ከነገ ረቡዕ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ልዩ የክረምት ትምህርት የሚጀመር መሆኑ ይታወቃል። ስለሆነም ሁሉም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በት/ቤት ዩኒፎርም ከጠዋቱ 2:20 ጀምሮ በጥናት መርሃ ግብሩ መሳተፍ ግዴታ መሆኑን እያሳወቅን ወላጅ አስፈላጊውን ክትትል እንዲያደርግ እናሳስባለን ። ትምህርት ቤቱ
መልዕክት ለ2019 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን በሙሉ ከሐምሌ 6-7 ቀን 2018 ዓ.ም ለክረምት ትምህርት በመመዝገብ ረቡዕ ሐምሌ 8 ቀን ትምህርት የሚጀመር መሆኑን እናሳውቃለን ። ትምህርቱ ዘወትር ከሰኞ እስከ ዓርብ ከጠዋቱ 2:15 እስከ 6:00 ይሰጣል ። ማሳሰቢያ: የክረምት ትምህርት ያልተከታተለ ተማሪ ለሚቀጥለው የትምህርት ዘመን የማይመዘገብ መሆኑን እንገልጻለን። መልካም ጊዜ
ለኤስ ኦ ኤስ ሔርማን ግማይነር ት/ቤት ተማሪዎችና ወላጆች በሙሉ፡ የሐረር ኤስ ኦ ኤስ ሄርማን ግማይነር ት/ቤት የ2018 ዓ.ም የወላጆች በዓል እንዲሁም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የምረቃ መርሃ ግብር ቅዳሜ ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል። ስለሆነም በዕለቱ ተማሪዎች፣ ወላጆች፣ ውድ ተመራቂ ተማሪዎቻችንና የተመራቂ ተማሪ ወላጆች ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በትምህርት ቤቱ ቅጥር ግቢ እንድትገኙ ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን ። ትምህርት ቤቱ
Dear all, Both grade 6 & 8 Students scored a remarkable result. To our Amazing Students especially Grade 6: Congratulations on your exceptional performance! Your discipline, perseverance, and determination have truly paid off. You have made our school incredibly proud, and these outstanding regional scores are a testament to your bright futures. Keep reaching for the stars! To our Dedicated Teaching Staff: Thank you for your tireless efforts, patience, and passion. Your commitment to nurturing these young minds and providing high-quality guidance has been the driving force behind these brilliant results. You have empowered our students to reach their full potential. Once again, congratulations to our entire school community! Let this milestone be just the beginning of many great accomplishments to come. Note: All Our Grade 6 students promoted.(100% passed), And, 97% of Grade 8 students scored a remarkable result.
без подписи
መልዕክት ለተማሪ ወላጆች በሙሉ አንዳንድ ተማሪዎች ዝግጅት አለን በማለት ከወላጅ ገንዘብ እየጠየቁ እንደሆነ ከአንዳንድ ወላጆች ለመገንዘብ ችለናል። ይሁን እንጅ ምንም አይነት የተፈቀደ ዝግጅትም ሆነ ጉዞ የሌለ መሆኑን እናሳውቃለን ። ትምህርት ቤቱ
Physics
Notice Dear G-11 Students, There will be Web & IT Final Exam on tomorrow June 11, 2026. Stay informed.
без подписи
без подписи
ለኤስ ኦ ኤስ ት/ቤት ተማሪዎችና ወላጆች ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም መደበኛ የትምህርት ስራ የሚቀጥል መሆኑን እናሳውቃለን ። ትምህርት ቤቱ
ለኤስ ኦ ኤስ ት/ቤት ተማሪዎች በሙሉ ሰኞ ግንቦት 17 2018 ዓ/ም በሐረር ከተማ በሚደረግ ሰልፍ ምክንያት ትምህር የማይኖር መሆኑን እያሳወቅን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የሰልፉ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል ። ት/ቤቱ
https://www.premedprojects.co.uk/online-portal/future-doctors-weekend
без подписи
#ጥቆማ " ለስልጠናው ከ11 ዓመት ጀምሮ ያሉ ታዳጊዎች፣ ወጣቶች መመዝገብ ይችላሉ " - INSA የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (INSA) 5ኛውን የሳይበር ታለንት ሰመር ካምፕ በስድስት ዩኒቨርሲቲዎች ሊሰጥ መሆኑን ገልጿል። የአስተዳደሩ የሳይበር ልህቀት ማዕከል ዳይሬክተር አቶ ቢሻው በየነ እንደገለጹት፤ ካምፑን በክልል ዩኒቨርሲቲዎች ለማካሄድ የታቀደው የ«ዲጂታል አካታችነት» (Digital Inclusion) መርህን በመከተል ሰልጣኞች ባሉበት አካባቢ የሥልጠና ዕድሉን እንዲያገኙ ለማስቻል ነው። እስካሁን ባለው ሂደት ከ4 ሺ 551 በላይ ክህሎት ያላቸው ወጣቶች ለሥልጠናው መመዝገባቸውን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። ለአንድ ወር በሚቆየው ስልጠና የአካል ብቃት እንቅስቃሴን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ተከታታይ የሆኑ ስልጠናዎችን የሚሰጡ ሲሆን የስልጠናው ማብቂያ ላይም ፕሮጀክቶችን የሚሰሩ ይሆናል። ስልጠናው :- • ሳይበር ደህንነት (Cyber Security) • ሶፍትዌር ዴቨሎፕመንት(Software Developmet) • ኤምቤድድ ሲስተም (Embedded System) • ኤሮስፔስ (Aerospace) • ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ (Emerging Technology) ዘርፎችን ያካተተ ነው። ለስልጠናው ከ11 ዓመት ጀምሮ ያሉ ታዳጊዎች ፣ ወጣቶች መመዝገብ ይችላሉ የተባለ ሲሆን ነገር ግን ከዛ በታችም ሆነው ተቋሙ የሚፈልጋቸው ልዩ ክህሎቶችን ይዘው ቢገኙ ተቀባይነት የሚያገኙበት እድል ይኖራል ተብሏል። የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ ቴክኖሎጂን መግዛት ብቻ በቂ እንዳልሆነ የገለጹት አቶ ቢሻው፤ በሀገር በቀል እውቀት የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ለሀገራዊ ደህንነት ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። ይህ መርሃ ግብርም «ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030» ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግና ብቁ የሳይበር ሠራዊት ለመገንባት ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ተጠቁሟል። የዘንድሮው የሰመር ካምፕ ስልጠና የሚሰጥባቸው ማዕከላት ፦ * አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ * ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ * ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ * ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ * ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እና * ጅማ ዩኒቨርሲቲ ናቸው። ለሥልጠናው ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች እስከ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በድረ-ገጽ https://ctc.insa.gov.et/registration መመዝገብ የሚችሉ ሲሆን፤ ወላጆችም ልጆቻቸውን በማስመዝገብ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia
ማስታወቂያ የትምህርት ቤት ክፍያ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ላላጠናቀቃችሁ ወላጆች በሙሉ ፡ የ2018 የትምህርት ዘመን የመጨረሻ ዙር የትምህርት ክፍያ መክፈያ ጊዜ እስከ ሚያዚያ 21, 2018 ዓ/ም መሆኑን በደብዳቤ ያሳወቅን መሆኑ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም አብዛኛው ወላጅ በተሰጠው ጊዜ የ2018 የትምህርት ክፍያ በማጠናቀቃችሁ ት/ቤቱ ከፍ ያለ ምስጋና ያቀርባል። ነገር ግን ጥቂት ወላጆች እስከ ግንቦት 11 ቀን ድረስ የዓመቱን የትምህርት ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ መሆኑን አረጋግጠናል። ስለሆነም በተሰጠው ጊዜ ያላጠናቀቃችሁ ወላጆች ቀሪ የትምህርት ክፍያ በማጠናቀቅ ረቡዕ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ. ም ክፍያ የፈጸማችሁበትን የባንክ ሰነድ ፋይናንስ ክፍል እንድታቀርቡ በአክብሮት እንጠይቃለን ፡፡ ማሳሰቢያ: ከሐሙስ ግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ. ም ጀምሮ ክፍያ ያላጠናቀቀ ተማሪ ክፍል የማይገባ መሆኑን በጥብቅ እናሳሰባለን:: የት/ቤቱ አስተዳደር
без подписи
መልዕክት ለት/ቤታችን ሴት ተማሪዎችና መምህራን ቅዳሜ 08/09/2018 ዓ.ም በክልል ደረጃ የሴቶች ንቅናቄ በደማቅ ሁኔታ ስለሚከበር ከ8ኛ-12ኛ ክፍል ያላችሁ ሴት ተማሪዎችና ሴት መምህራን የባህል ልብስ በመልበስ በእለቱ ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ በአሚር አብዱላሂ አዳራሽ እንድትገኙ ከሴቶች፣ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት መልዕክት ተላልፏል፡፡ ማሳሰቢያ በዝግጅቱ ላይ ተማሪዎች የት/ቤት የደንብ ልብስ መልበስ የማይፈቀድ መሆኑን እያሳሰብን የባህል ልብስ መልበስ የማይችሉ ተማሪዎች በማንኛው የዘወትር ልብስ መገኘት የሚቻል መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ መልካም ጊዜ
без подписи