tgindex
የአዳማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት

የአዳማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት

Статистика

ይሄ የቴሌግራም ገፅ በምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነተ በሰ/ት/ቤቶች አንድነት የተከፈተ ሲሆን በዚህ ቻናል መንፈሳዊ ትምህርቶችን፣ ዜና ቤተክርስቲያንና ወቅታዊ ጉዳይ የምንዘግብበት ነው። እርሶም ለኦርትዶክሳውያን ሁሉ ቻናሉን በማጋራት ለቅድስት ቤተክርስቲያን ድምጽ ይሁኑ። ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን!

Последний пост
8 авг.
Последнее чтение
15 авг.
Постов за неделю
0
Всего постов
31
Тип
открытый
Язык
ti
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
1 282
0 за 2 дн.
Сутки
+1
+0,08%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
499
31 постов
Вовлечённость
38,9%
к подписчикам
Постов в день
0,0
всего 31
Упоминаний
1
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
403
1/48двое суток
461
1/72трое суток
498

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • ሥርዓተ ትምህርቱ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ምን ያስተምሩ? ተማሪዎች እን ዴት ይማሩ?  ማን ምንም መማር አለበት? ማን ያስተምር? ትምህርት ቤቶች እንዴት ይደራጁ? ተማሪዎች እንዴት ይለዩ? የሚሉ ጥያቄዎችን እንዲመልስ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ሥርዓተ ትምህርት ማለት ዓላማ  የተነደፈላቸው፣ ይዘት የተቀረጸላቸው ትምህርቶችን እንዲሁም አጠቃላይ መርሖዎችን፣ ቅደም ተከተሎችንና የአተገባበር አቅጣጫዎችን በሚያሳይ መልኩ የተደራጁ ትምህርቶችን በመያዝ በመማር ማስተማር ሒደት ውስጥ የተማሪዎችን እና የመምህራንን ተግባራት የሚያመ ላክት ሰነድ(Document)እንደ መሆኑ መጠን ይህም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መርሑን ተከትሎ የተዘጋጀ ነው። በዚህም መሰረት አጠቃላይ ማዕቀፍ (framework) ለየትምህርት ዓይነቱ መርሐ ትምህርት (Syllabus) በማዘጋጀት  የመማርያ መጻሕፍቱ ተዘጋጅተዋል።የተዘጋጂጁት መጻሕፍት  በቅድመ መደበኛ (KG) “ሀ” እና “ለ’ እንዲሁም በመደበኛ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ተዘጋጅተዋል። በቋንቋ ረገድም በአማረኛ የቅድመ መደበኛ (KG) “ሀ” እና “ለ” እንዲሁም የመደበኛ ከ 1ኛ እስከ 10ኛ ክፍል የአርትኦት ሥራውን ተጠናቆ የታተመ ሲሆን በአፋን ኦሮሞም ከ 1ኛ እስከ 4ኛ ታትሞ በሥርጭት ላይ ይገኛል። በቀጣይም በትግርኛ፣በኢንጊሊዝኛ እና በአፍሪካ ብዙ ተናጋሪዎች ባሉ በስዋሂሊ (Swahili / Kiswahili ) ቋንቋዎች ለማሳተም የትርጉም ሥራዎች ተጀምረዋል። ይህ ሥርዓተ ትምህርት በሰንበት ት/ቤቶች ይታይ የነበረ መዝሙር ላይ ብቻ ያተኮረ አግልግሎት በዕውቀት የተደገፈ እንዲሆን የሰንበት ተማሪዎችም ለተጠየቁት ሁሉ ምላሽ መስጠት የሚችሉ ብቻም ሳይሆኑ የጠፉትን አስተምረው መመለስ የሚችሉ እንዲሆኑ በእጅጉ ያግዛል። ከዚህ በተጨማሪ ይህንን ተምረው ወደመንፈሳዊ ኮሌጆችም ሆነ ወደ አብነት ት/ቤቶች ቢገቡ  መሠረታዊውን የቤተ ክርስቲያን እውቀት አስቀድመው ጨብጠው ስለሚገቡ ብቁ እና ለቤተ ክርስቲያን  እጅግ ጠቃሚ አገልጋዮች ሆነው ይወጣሉ። በ  ፲፱፻፹፮ ዓ.ም በተሻሻለው ቃለ ዐዋዲ አንቀጽ ፳፩  የሰንበት ትምህርት ቤት ሕጻናት፣ወጣቶች እና ጎልማሶች በቤት ክርስቲያን ተገኝተው የቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት ሥርዓት እና ትውፊት እንዲሁም ክርስትያማዊ ስነ ምግባር እንዲማሩ በተደነገገው መሠረት ሥርዓተ ትምህርቱ በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ በየደረጃው ባለው የቤተ ክርስቲያን መዋቅር ተግባራዊ ማድረግ ለነገ የሚባል ተግባር አይደለም። ስለሆነም መጽሐፍ ቅዱስን በአግባቡ የተረዳ የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤትክርስትያን ዶግማ ቀኖና እንዲሁም ትውፋት እና ሥርዓት የሚያውቅ ብቁ ምእመንና አገልጋይ መፍጠር ይቻል ዘንድ ሥርዓተ ትምህርቱን ተግባራዊ እናድርግ እላለሁ።                                                          ወስብሐት ለእግዚአብሔር  ወስብሐ አባ ቀሌሚንጦስ በ/ኢ/ኦ/ተ/ቤ/በ/ፓ/ጠ/ጽ/ቤት  የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

  • የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ሰንበት ትምህርት ቤት በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን መዋቅር መሠረት ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የጾታ ልዩነት ሳይደረግ የቤተ ክርስቲያን ተተኪ ትውልድ ማለትም መንፈሳዊያን ሕፃናት፣ ወጣቶች እና ጎልማሶች በቤተ ክርስቲያን እየተገኙ የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ቀኖና፣ ትውፊት ሥርዐት እና ትውፊት የሚማሩበት ትምህርት ቤት እና የአገልግሎት ሥፍራ ነው። ቤተ ክርስቲያን ተተኪውን ትውልድ ለማስተማር እና ለማሳደግ ያስችላት ዘንድ ሰንበት ትምህርት ቤቶች  ላይ በተደራጀ መልኩ ሰንበት ት/ቤቶች ከተመሠረቱ ጀምሮ አባላትን የማስተማር እና በአገልግሎት የማሰማራት ሥራዎች  እንደእየ አጥብያው ተጨባጭ ሁኔታ ሲከናወን የቆየ ሲሆን ከትምህርት አሰጣጥ ሂደት ጋር ተያይዞ ወጥ ባልሆነ መንገድ የተለያዩ ሥራዎች ሲሠሩ ቆይቷል።  ለምሳሌ ፲፱፻፰ ዓ.ም መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ድርሰት ክፍል የተዘጋጀ የመጽሐፍ ቅዱስ መማርያ  በሚል ከ ፩ እስከ ፫ኛ  ክፍል ያለው ሆኖ በየትምህርት ቤቶች እና በሰንበት ትምህርት ቤቶች ለማስተማርያ እንዲውል ተዘጋጅቶ ቀርቦ ነበር ። ቀጥሎም በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ለሰንበት ት/ቤት አባላት እና መምህራን ማስተማርያ ጽሑፎችን በማዘጋጀት ከ ፲፱፻፸ ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ ልዩ ልዩ ሥራዎችን ሲከናወን ቆይቷል። ይህ ወጥ ያልነበረው እና ያልተናበበ ለሁሉም አብያተ ክርስትያናት ሰንበት ት/ቤቶች ያልተዳርሰ አሠራርን አስቀርቶ ሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤቶች ወጥ በሆነ እና ሥርዓት ባለው መልኩ ለማስተማር ይቻል ዘንድ የሰንበት  ትምህርት ቤቶች ወጥ ሥርዓተ ትምህርት ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።

  • የ2019 ዓ.ም የሥርዓተ ትምህርት ማስተግበሪያ የጊዜ ሰሌዳ በተመለከተ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ከቅዱስ ሲኖዶስ በተሰጠው ተልዕኮ በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጭ የሚገኙ ሕፃናት፣ ወጣቶች እና ጎልማሶችን በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖት የጸኑ፣ ሥነ ምግባራቸው ያማረ፣ ቀደምት አባቶቻቸውን በመምሰል ቤተ ክርስቲያንን የሚረከቡ እና ሀገርን የሚጠብቁ ትውልድን የማፍራት ሥራውን በመሥራት ላይ ይገኛል። ይህንንም ከተዥጎረጎረ እና ወጥነት ከጎደለው፣ ለአንድ ዓላማና ግብ የተናጠል ሩጫ ከበዛበት አሠራር ሰንበት ትምህርት ቤቶቻችን ተላቀው በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በአንድ ሐሳብና በአንድ ቃል እንዲጓዙ የሚያስችል ሥራን በመሥራት ላይ ይገኛል። ከነዚህም አንዱና ዋነኛው የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ነው። ይህም ሥርዓተ ትምህርት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ባሉ አህጉረ ስብከት በትግበራ ላይ ይገኛል። ሰንበት ትምህርት ቤቶችም ለአተገባበር ያመቻቸው ዘንድ ዓመታዊ የትምህርት መርሐ ግብር የሚያስፈልግ በመሆኑ በሀገር ዐቀፍ ደረጃ ይህን ማስተገበሪያ ሰነድ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኗል። ይህም ዓመታዊ የትምህርት ማስተግበርያ ሰነድ ለ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን እንዲሆን ተደርጎ ተዘጋጅቷል። በዚህ ማስተግበርያ ሰነድ ውስጥ የዓመቱን የትምህርት መርሐ ግብር መጀመርያ እና መጨረሻ ጊዜ፣ የፈተና መርሐ ግብራት፣ የሴሚስተር የሪፖርት ጊዜያትን፣ የመርጃ መሣርያ ዝግጅትን ወዘተ በዝርዝር የያዘ ነው። ለዚህም የትምህርት መርሐ ግብር የየአህጉረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እንዲሁም አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሓላፊነታቸውን በአግባቡ በመወጣት ሰፊውን ድርሻ መያዝ ይጠበቅባቸዋል። ይህ የትግበራ ሰነድ ወይም የትምህርት መርሐ ግብር በተቀመጠለት ጊዜና ሰዓት ተፈጻሚ መደረግ ይኖርበታል። ሰነዱንም በአንድነቱ የዌብሳይት ገጽ ላይ  ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማግኘት ይችላሉ። https://eotc-gssu.org/a/የ2019-ዓ-ም-የሥርዓተ-ትምህርት-ማስተግበሪያ/ መንበረ ፓትርያርክ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሀገር አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሐምሌ 2018 ዓ.ም የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok 👉  Website

  • видео или голосовое, без подписи

  • “መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ" በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ፣ አሜን ! በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ! የሰውን ወገን ለማዳን የልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ ድንግል ማርያምን የመረጠ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ማርያም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ! “ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ፡- ከወደዳችሁኝስ ትእዛዜን ጠብቁ" (ዮሐ.14፥15)፤ ፍቅር የሕያዋን ኣካላት ረቂቅ መገናኛ ነው፣ ሕያዋን ኣካላት በውጫዊው ግዙፍ ኣካላቸው በተወሰኑ ጊዜያትና ቦታ ይገናኛሉ ፤ ስለ ጋራ ጉዳያቸውም በጋራ ይመክራሉ፤ ይበልጥም ይቀራረባሉ፡፡ ይሁንና የሕያዋን ኣካላት ግንኙነት በኣካል በጊዜና በቦታ ብቻ የተወሰነ ኣይደለም፣ በፍቅረ መንፈስ ተገናኝተውም ይግባባሉ፣ ከኣካላዊ ግንኙነት በላይ የበለጠም ይኸው ፍቅረ መንፈስ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር እግዚአብሔርንም ማግኘት የምንችለው በዚሁ ፍቅረ መንፈስ ሆነን በእምነት ዓይን ነው! ይህም በመሆኑ ሓዋርያው ቅዱስ ዮሓንስ በመልእክቱ “በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔርይኖራል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል" በማለት ያስተምረናል፣ (1ዮሐ. 4፥16) ይህም ማለት ከሱ ጋር በፍቅር ስንገናኝ፤ እሱም በኛ፣ እኛም በእሱ የመኖሩ ኩነት ይፈጠራል ማለት ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ጌታችን “አፍቅሮ ለእግዚአብሔር ኣምላክከ፤- አምላክህን እግዚአብሔርን ውደደው" በማለት በፍጹም ልባችን እንድንወደው፣ እንደዚሁም ራሳችንን በምንወድበት መጠን እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ማዘዙን እናውቃለን፤ የመውደዳችን መለኪያ ሚዛንና መገለጫ ምልክትም ትእዛዙን ማክበርና መጠበቅ እንደሆነ “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” በማለት ኣስተምሮናል ከዚህ ኣኳያ ጌታን መውደድ ማለት ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ግዙፍ ነገር እንጂ ምናባዊና የማይታይ ድብብቆሽ ነገር ኣይደለም ማለት ነው፣ ጌታችንን የመውደድ ነገር ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ከሆነ ትእዛዙ ምንድን ነው? የሚለውን ማየት ኣስፈላጊ ይሆናል፤ ትእዛዙን በጥቅል ስናይ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን በመውደድ እንደሚጠቃለል ራሱ ጌታችን ኣስገንዝቦናል፣ በተለይም በባልንጀራችን ላይ የምንከተለው መውደድ ከላይ እንደተገለጸው “እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ" ተብለ በግልጽ ተቀምጦኣል፤ የሰው ባልንጀራ እነማን ናቸው? በሕይወት ያሉት ናቸው? ወይስ የሞቱት? ወገን ዘመድ? ወይስ የሰው ወገን በሙሉ የሚለውንም ማወቅ ኣስፈላጊ ነው፡፡ ጌታችን ነገሩን በዚህ ደረጃ ለያይቶ ኣላስቀመጠም፣ ለምን? ቢባል ባልንጀራ ማለት የተወሰነን የማኅበረ ሰብ ወገን የሚያሳይ ሳይሆን መላውን የሰው ወገን የሚገልጽ በመሆኑ፤ እንደዚሁም የሞቱም ሆኑ ያለነው ሁላችን በእሱ ፊት ሕያዋንና እርስ በእርሳችን ባልንጀሮች በመሆናችን ነው፤ በመሆኑም መዋደዳችንም ሆነ መከባበራችን በሕይወተ ሥጋ ሳለን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ በሌለው ዕድሜ በመሆኑ ጌታችን በጊዜ በቦታና በከፊል ለይቶ ኣላስቀመጠም፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት ! ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ለ፲፭ ቀናት የምንጾመው የጾመ ማርያም መነሻ ምክንያቱ የእግዚአብሔርትእዛዝና ፍቅር ነው፣ እግዚአብሔር ሰውን በኣጠቃላይ በተለይም ደግሞ እንደፈቃዱ የኖሩ ቅዱሳንን እንድናከብርኣዞናል ክቅዱሳን ፍጥረታት መካክል ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያውን ደረጃ ትይዛለች፤ ይህም በመሆኑ ከፍጥረት ወገን ከሏ ክብር የሚደርስ ባለመኖሩ ከሁሉም ኣብልጠን እናክብራታለን፤ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ደረጃ የድንግል ማርያምን ክብር ስትገልጽ ክእግዚአብሔርና ለባስያነ እግዚአብሔር ክሆኑ ቀደምት ኣበው ተምራ ነው! በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ዕውቁ ቅዱስና ዓለም ዓቀፋዊው አባት ቅዱስ ኤፍሬም የድንግል ማርያምን ክብር! ቅድስና እና ልዕልና ሲናገር “ይእቲ ተዓቢ እምኪሩቤል፡ ወትፈደፍድ እምሱራፌል፣ እስመ ኮነት ታቦተ ለአሓዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ- እሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች! ከሱራፌልም ትልቃለች፣ ከቅድስት ሥላሴ ኣንዱ ለሆነው ታቦት ወይም ማደሪያ ሆናለችና" በማለት አስተምሮናል፡፡ በመሆኑም ለስሟ መታሰቢያ በሆነው በዚህ ጾም ድንግል ማርያምን በዚህ ደረጃ ስናክብርትእዛዙን እንጠብቃለን፤ ትእዛዙን በመጠበቃችን ደግሞ እሱን መውደዳችንን እናረጋግጣለን ! እኛ ድንግል ማርያምን እንድንወዳት "እናታችሁ'' ብሎ እንዳዘዘ፣ እሷም ልትወደን “ልጆችዅ ተብላ ታዛለችና ስለኛ ትጸልያለች፡፡ በጸሎቷም ከመከራ ትታደገናለች፤ በኣጠቃላይ በእግዚአብሔር' በቅዱሳንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት በዚህ ትእዛዝና ፍቅር በትዕይንተ ዓለም ባለች ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የተሳሰረ ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሱባዔ የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሎትን በማስታረቅ፤ የታመሙትንና የታስሩትን በመጠየቅ፤ ቅዱስ ቍርባንን በመቀበልና ለኃጢኣታችን የንሥሐ ሥርየትን በመለመን ሱባዔውን ልናሳልፍ ይገባል፡፡ በመጨረሻም በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከባድ ስጋት የሆነው የፍጥረት ኣውዳሚ ጦርነትን በመለኮታዊ ጥበቡና ሥልጣኑ እንዲያስቆምልን በቅን ልቡና፤ በትሑት ሰብእና ሆነን እግዚአብሔርን በዚህ ሱባዔ እንድንጠይቀው ኣደራ ጭምር ኣባታዊ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤ የተባረከና የተቀደስ ጾም ያድርግልን፤ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ አሜን! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

  • “ይህን ነገር ወላጆች ሁሉ ማወቅ አለባቸው!” — ከመድኃኔዓለም ገዳም የተላለፈው አባታዊ ጥሪ የመድኃኔዓለም ወራዊ መታሰቢያ በዓል በአዳማ ቦሌ መድኃኔዓለም ገዳምና ካቴድራል በክብርና በመንፈሳዊ ድባብ ተከብሯል።የበዓሉ ሥርዓት በማኅሌትና በሥርዓተ  ቅዳሴ የተጀመረ ሲሆን፣ በመቀጠልም የአውደ ምሕረት ትምህርተ ወንጌልና ለምዕመናን የተሰጡ መንፈሳዊ ምክሮች ተላልፈዋል።በዚህ መንፈሳዊ መድረክ የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ ጳውሎስ ምንዳ ለምዕመናን ሰፊ የወንጌል ትምህርትና አባታዊ ምክር ሰጥተዋል። 📖 “ልጆቻችሁን ቅዳሜና እሁድ ወደ ቤተክርስቲያን ላኩ”በዚህም መሠረት የገዳሙ ፈለገ ጥበብ ሰንበት ት/ቤት 32ኛ የምስረታ በዓሉን እያከበረ መሆኑን ገልጸው፣ ለዚህም እንኳን  አደረሳችሁ በማለት  ለምዕመናንና ለቤተሰቦች ደስ የሚያሰኝ መልዕክት አስተላልፈዋል።በአዲሱ የትምህርት ሥርዓት ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚደርስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የተዘጋጀ ጥራት ያለው የመንፈሳዊ ትምህርት ሥርዓት መኖሩንም አባታችን ገልጸዋል። 👉 “ዓለማዊው ትምህርት በክፍያ ነው፤ ይህ መንፈሳዊ ትምህርት ግን በነጻ የሚሰጥ የልጆቻችን የነፍስ ሀብት ነው” የሚል ሀሳብ በማንሳት፣ ወላጆች ልጆቻቸውን በሰንበት ት/ቤት እንዲያስመዘግቡ ጥሪ አቅርበዋል። 🏫 የገዳሙ ትምህርት ቤት — ዓለማዊ ትምህርትን ከመንፈሳዊ እሴት ጋርየገዳሙ ትምህርት ቤት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቦርድ አመራር መመራቱ ለትምህርት ቤቱ እድገት እና ለሥራ አፈጻጸሙ ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉንም ገልጸዋል።ትምህርት ቤቱም ከሌሎች ተርታ የሚያሰልፈው ልዩ ገጽታ ያለው ሲሆን፣ ዓለማዊ ትምህርትን ብቻ ሳይሆን ከመንፈሳዊ ትምህርትና ከሥነ ምግባር ጋር በማጣመር ትውልድን ለማነጽ እየሰራ መሆኑን አባታችን አስረድተዋል።የገዳሙ የልማት ሥራዎችበገዳሙ በአሁኑ ወቅት በርካታ ዘርፈ ብዙ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውንም አስተዳዳሪው ገልጸዋል።እነዚህ ሥራዎችም እስከሚመጣው አዲስ ዓመት እና በጥቅምት የሚከበረው የመድኃኔዓለም ዓመታዊ የንግሥ በዓል ድረስ በተቻለ መጠን ተጠናቀው ለምዕመናን እንዲደርሱ እየተሰራ መሆኑን ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። 🙏 የመጨረሻ ጥሪ የትውልድ ነገር ዛሬ እንጀምረው! ወላጆች ሆይ፣ ልጆቻችሁን ቅዳሜና እሁድ ወደ ቤተክርስቲያን ላኩ፤ በሰንበት ት/ቤትም አስመዝግቡ። የዛሬ መንፈሳዊ ትምህርት የነገ ትውልድ መሠረት ነው። መረጃው:- Felege Medhanit Media

  • видео или голосовое, без подписи

  • видео или голосовое, без подписи

  • видео или голосовое, без подписи

  • видео или голосовое, без подписи

  • видео или голосовое, без подписи

  • видео или голосовое, без подписи

  • видео или голосовое, без подписи

  • видео или голосовое, без подписи

  • የምሥራቅ ሸዋ ሀገረስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በተጠናቀቀው የ2018 ዓ.ም የአገልግሎት አፈፃፀም ዙሪያ ለብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅ/ገብርኤል ገዳም የካህናት ማሰልጠኛ እና መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ ጋር  በ27/11/2018 ዓ.ም ውይይት አደረገ ። የአንድነቱ ሥራ አመራር በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተሰሩ  ዋና ዋና ስራዎችን እና ያገጠሙ ተግዳሮቶች የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች እንዲሁም የ2019 ዓ.ም ዋና ዋና እቅድ  ለብፁነታቸው የቀረበ ሲሆን ፤ አንድነቱ ከሀገረ ስብከቱ ከብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ ጀምሮ በክቡር ሥራ አሰኪያጅ እና በክቡር ም/ሥራ አስኪያጅ እየተደረገ ያለውን ድጋፍ ምስጋና አቅርቧል። ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስም የተሰሩ ስራዎችን መልካም እና ተስፋ ሰጪ ናቸው ነገር ግን ብዙ ስራ ከአንድነቱ ይጠበቃል ሲሉ አሳስበው አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል። በመርሐግብሩ ላይ የሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሣሕል ቀሲስ ነጋሽ ሀብተ ወልድ የሀገረ ስብከቱ ም/ስራ አስኪያጅ መጋቢ ጥበባት ቀሲስ ጌቱ ሞቲ የሀገረ ስብከቱ የሰ/ት/ቤቶች ማደረጃ መምሪያ ሀላፊ ሊቀ ካህናት ቀሲስ ሻውል ታዬ ተገኝተዋል። **** መረጃው ፡-የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው።

  • видео или голосовое, без подписи

  • видео или голосовое, без подписи

  • видео или голосовое, без подписи

  • በባቱ (ዝዋይ) ከተማና አዳሚ ቱሉ ጂዶ ወረዳ ቤተ ክህነት የሰንበት/ት/ቤቶች አንድነት የ2018ዓ/ም የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና በትላንትናው እለት ማለትም ሐምሌ 26/2018 መሰጠቱን አስታወቀ። መረጃው:- በባቱ (ዝዋይ) ከተማና አዳሚ ቱሉ ጂዶ ወረዳ ቤተ ክህነት የሰንበት/ት/ቤቶች አንድነት

  • видео или голосовое, без подписи

የአዳማ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት — tgindex