ASIF RAMI
Статистикаወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል ረሱል (ﷺ) 👳♀️ @file_openn Group 👇 https://t.me/asif_rami11
- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 2
- Всего постов
- 22
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 734
- 1/48двое суток
- 841
- 1/72трое суток
- 907
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ነብያችን ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል በኔ ላይ አንድ ሰለዋት ያወረደ አላህ በሱ ላይ 10 ሰለዋት ያወርድለታል ። በጁመዐ ቀን ሱረቱል ካህፍን የቀራ ሰው በሁለቱ ጁመዓዎች መካከል ብርሀን ይበራለታል ። ረሱል (ﷺ)
ሶስት ጁመዐ በቸልተኝነት የተወ ሰው አላህ ቀልቡን ያሽግበታል ። ረሱል (ﷺ)
без подписи
ለዱንያውም ሆነ ለአኺራው የማይጠቅመውንና የማይመለከተውን ነገር መተው ለአንድ ሰው የመልካም ሙስሊምነቱ አንድ መገለጫ ነው።” ነብዩ ሙሃመድ(ሰ.ዐ.ወ) (ትርሚዚና ሌሎችም የዘገቡት ሃዲስ)
አላህ (ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፡- "ዛሬ ሃይማኖታችሁን ለእናንተ ሞላሁላችሁ። ጸጋዬንም በእናንተ ላይ ፈጸምኩ..." (ሱረቱ አል-ማኢዳህ፡ 3) ይህ አንቀጽ የወረደው በሐጅ ወቅት፣ በዓረፋ ቀን፣ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ዓረፋ ተራራ ላይ ቆመው ሳለ እንደሆነ በቡኻሪና ሙስሊም ተዘግቧል። "ኢድ ሙባረክ"
አረፋ ላይ መቆም ላልቻለ ◾️ፋደይል ቢን ኢያድ "አላህ ይዘንላቸው" እንዲህ ይላሉ- ⭕️👉በዚህ አመት (አላህ ወፍቆት) አረፋ ተራራ ላይ መቆምን ያልቻለና ያመለጠው ሰው፦ ያወቀው በሆነው በአላህ ሀቅ (ኢባዳ) ላይ ቀጥ ብሎ ይቁም። ⭕️👉(አላህ ወፍቆት) ሙዝደሊፋ ላይ ማደር ያልቻለ ሰው፦ አላህን በመታዘዝ ላይ ቆራጥነቱን ያሳድር። ⭕️👉በኸይፍ መስጅድ ዙሪያ መቆም ያልቻለ ሰው፦ በትክክል ለጌታው ትእዛዛ በፍራቻና በተስፋ ይቁም። ⭕️👉ሀድዩን (እርዱን) ሚና ወስዶ ማረድ ያልቻለ ሰው፦ ባለበት ሆኖ "መጥፎ" ዝንባሌው (ስሜቱ) ይረድ። ⭕️👉እሩቅ ሆኖበት የአላህን ቤት መድረስ (መዘየር) ያልቻለ፦ ባለበት ሆኖ የቤቱ (የመስጅደል ሀረም) ባለቤት የሆነውን አላህ ይሰብ። ምክንያቱም አላህ ለለመነውና ተስፋ ላደረገው ከደም ጋን ጅማቱ የበለጠ የቀረበ ነው። 📕 لطائف المعارف لابن رجب | 287 |
የአላህንም (የማመን) ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡[ሱረቱል አል-ኢምራን : 103]
የዙል ሂጃ ቀን ነገ ሰኞ ይጀምራል💫 🌸ዙል ሂጃ 10ሩ ቀናት ብዙ የሆኑ ትሩፋቶች አሏቸው 🌷ከነዚህ ቀናቶች ብልጫ እና ትሩፋት🌷 💐① አላህ በእነዚህ አስር ቀናቶች ላይ ምሏል እንደ ሚተቀው ደሞ አላህ የሚምለው ትልቅ እና ቦታ ባለው ነገር ነው አላህ እንዲህ ይላል{ وليال عشر} ሙፈሲሮች እነዚህ አስርት ቀናት አላህ የማለበት የዙል ሒጃ አስሩ ቀናቶች ናቸው ብለዋል 🌸②ታላቁ ሰሓቢይ ኢብኑ አባስ አላህ መልካም ስራውን ይውደድለት እና የአላህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላል [ በነዚህ አስርት ቀናቶች ላይ የሚሰሩ ስራዎች ከሁሉም ይበልጣሉ ሰሃባዎች ከጂሃድ ይበልጣሉደ ሲሉ ነብዩም ከጂሃድም ይበልጣሉ አንድ ሰው ሲቀር እንጂ ወደ አላህ መንገድ ወደ ጂሃድ ሲወጣ ንብረቱን ነፍሱን ይዞ ወቶ ከዛ ካልተመለሰ ] አሉ { رواه البخاري} 🌺③ እንዲሁም ታላቁ ሶሃቢይ ኢብኑ ኡመር በዘገቡት ሀዲስ የአላህ መልክተኛ እንዲህ ብለዋል [የትኛውም ቀን የለም አላህ ዘንድ ትልቅ የሆነ እንዲሁም ስራ ተወዳጅ የሚሆንበት ከነዚህ አስርቱ ቀን በላይ ] 🌺★ ከነዚህ ሀዲሶች የምንረዳው እነዚህ ቀናቶች ታላቅ እና የተከበሩ መሆናቸውን ነው★ 🌷በእነዚህ ቀናቶች የሚሰሩ መልካም ስራዎች 🌸①🕌ግዴታ የሆኑ ሰላቶችን በጊዜው መስገድ ለወንዶች በጀመአ መስገድ 🌷②🕋ረዋቲቦች ላይ መጠባበቅ እንዲሁም የተለያዩ ሱና ሰላቶችን ማብዛት 💐③ፆምን ማብዛት 🌸④ቁርአን መቅራት 💐⑤ተሀህሊል ተክቢር ተህሚድ ማብዛት ⑥🪴ሶደቃን ማብዛት 🔶እንዲሁም የተለያዩ የኸይር ስራዎችን በማብዛት ወደ አላህ መቃረብ🔶 🌷🌷ለየት ባለ መልኩ ዘጠነኛውን ቀን መፆም ምክንያቱም ስለ ዘጠነኛው ቀን መፆም ነብያችን ሲጠየቁ የሁለት አመት ወንጀል ያሳብሳል ብለዋል☀️ 🤲አላህ ሁላችንም ለኸይር ነገር ይወፍቀን እነዚህንም እድሎችን እና አጋጣሚዎች ከሚጠቀሙት ያድርገን 🤲 ❗️❗️❗️ አደራ አደራ አደራ በነዚህ ታላቅ እና ክቡር ቀናቶች ለአኼራችን ኸይር ነገር ሳንሰንቅ እንዳያመልጠን ❗️❗️❗️
በመታገስና በሶላትም ተረዱ፡፡ እርሷም (ሶላት) በፈሪዎች ላይ እንጅ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት፡፡ሱረቱል አል-በቀራህ [45]
ልጄ ሆይ! ሶላትን አስተካክለህ ስገድ፡፡ በበጎ ነገርም እዘዝ፡፡ ከሚጠላም ሁሉ ከልክል፡፡ በሚያገኝህም መከራ ላይ ታገስ፡፡ ይህ በምር ከሚያዙ ነገሮች ነው፡፡ሱረቱል አል ሉቅማን ምዕራፍ 17 መልካም ጁመዐ ❤
እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
без подписи
ረሱል (ﷺ ሠ ዐ ወ) እንዲህ ብለዋል፦ ዘካተል ፊጥርን ከ ኢድ ሰላት በፊት የሰጠ ተቀባይነት ያለው ዛካ ይሆንለታል።ከ ኢድ ሰላት በኃላ የሰጠ ግን እንደማንኛውም ተራ ሰደቃ ነው።"
без подписи
без подписи
አንድ ሰው የማይመለከተው ነገር መተው ከእስልምና ውበት የሚመደብ ነው!! ረሱል ﷺ
ዛሬ ቀኑ 26 ለይሉ ደሞ 27 ነው በኢባዳ ሱረቱን ኢኽላስ መቅራት ታላቅ ምንዳ በረካ አለው። የረመዷን 27ኛው ሌሊት በብዙ የኢስላም ሊቃውንት ዘንድ ለይለተል ቀድር የመሆን እድሉ ከፍተኛ እንደሆነ ይታመናል። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ይህን ታላቅ ሌሊት አስመልክተው ያስተማሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦ የረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ትምህርቶች እና ተግባራት መፈለግ (ቲላዋ): ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) "ለይለተል ቀድርን በረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ውስጥ ባሉ ኦድ (ኢ-ጥንድ) ቀናት ፈልጓት" ብለዋል። ከእነዚህም መካከል 27ኛው ሌሊት በብዙ ሰሐቦች (እንደ ኡበይ ኢብኑ ካዕብ) ዘንድ ትልቅ ግምት ይሰጠዋል። ኢባዳን ማብዛት: ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ሲገቡ ትጥቃቸውን አጥብቀው፣ ሌሊቱን በሙሉ በሶላት፣ በዚክርና በዱዓ ያሳልፉ ነበር፤ ቤተሰቦቻቸውንም ለኢባዳ ያነቁ ነበር። የሚቀራ ዱዓ: እናታችን ዓኢሻ (ረ.ዐ) "የቀድርን ሌሊት ካገኘሁ ምን ልበል?" ብለው ሲጠይቋቸው ረሱል (ሰ.ዐ.ወ) ይህን ዱዓ እንዲሉ አስተምረዋቸዋል፦ የሌሊቱ ትሩፋት ይህ ሌሊት ከአንድ ሺህ ወራት (83 ዓመት ከ4 ወር) በላይ በላጭ ነው። በዚህ ሌሊት በኢማንና አጅርን ከአላህ በመፈለግ የቆመ ሰው ያለፈው ወንጀሉ እንደሚማርለት ተነግሯል። በዚህ በረከቱ በበዛበት ሌሊት በሶላት፣ በቁርአን ንባብ እና በዱዓ በመበርታት የአላህን እዝነት እንዲያገኙ ይመከራል። ስለ ለይለተል ቀድር ምልክቶች ወይስ ስለ ዱዓው አቀራረብ በዝርዝር ማወቅ ይፈልጋሉ
ለይለተል ቀድርን በመጨረሻ አስር የረመዳን ቀናቶች ውስጥ ፈልጉት::
ረሱል (ﷺ ሠ ዐ ወ) እንዲህ ብለዋል፦ ዘካተል ፊጥርን ከ ኢድ ሰላት በፊት የሰጠ ተቀባይነት ያለው ዛካ ይሆንለታል።ከ ኢድ ሰላት በኃላ የሰጠ ግን እንደማንኛውም ተራ ሰደቃ ነው።"
#ረመዷን_24 . ሱረቱል ካህፍ . “በጁምዓ ቀን ሱረቱል ካህፍን ላነበበ ሰው በሁለቱ ጁምዓዎች መሀል ያለውን ያህል ከብርሃን ያበራለታል።” . #መልካም ጁመዓ