- Последний пост
- 12 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 1
- Всего постов
- 20
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 39
- 1/48двое суток
- 44
- 1/72трое суток
- 48
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ውሰደን እንዳንል ቅጣትህ አስፈራን፥ አኑረን እንዳንል ኖረን ምን አፈራን፥ ፀሎቱ ጠፍቶናል በፈለከው ምራን። By andina @getem @getem @paappii
ሰላም ውዶቼ ስለትግስታቹ አመሰግናለሁ በአንዳንድ ምክንያት ፖስት ማረግ አልቻልኩም ለሰው ማጋራት ምትፈልጉትን ታሪክ በውስጥ ንገሩኝ በአሪፍ መልክ ማጋራው ይሆናል እወዳቹዋለው @zecutegirl0
⏳
እግር የማይረግጠው ሰው የማይደርስበት ዝምብሎ ለጌጥ ከተፈለፈለ የማይረባ አለት ውጪ አይታየኝም ሰው የሚያሰነብት ከሰማይ ጠቀስ ፎቅ ባዶነት ከሞላው ባይጠቅስ ይቅር ልክ እንደኋላው(እንደባቢሎን) ከተሽቆጠቆጠው ከአስፓልቱ ጀርባ ብዙ ጨካኝ አለ ህዝብን የሚያስነባ አይገርመኝም የተዋበ አይደላኝም የተጌጠ የስንቱ ደም ስንቱን እምባ ከመጠጠ ያማረቤት ወና እኮነው ያለ እናት ባዶ እኮ ነው ያለ አባት በተራበ ሆድ ባልጠገበ ሆድ ልብስ እንደመደረብ ካለብርድ ፍሬ
ቅኝ ገዢወች የአንድን አገር ማዕድን ሌላም ቁሳዊ ሐብት ዘርፈው መሄዳቸው የታወቀ ነው፤ ደቡብ አፍሪካዊያንን ግን ጭንቅላታቸውን ነቅለው ነው የወሰዱባቸው። ነፃነት ካለጭንቅላት ጋጠወጥነት ነው!! ነውረኞች! በነገራችን ላይ ሌሎችም አገራት ዛሬ ላይ ሰላም ነው ብላችሁ ሐብት የምታፈሩ ኢትዮጵያዊያን ምንጊዜም ይሄን አስታውሱ "እንቁላላችሁን አንድ ቅርጫት ውስጥ አታስቀምጡ" በተለይ አፍሪካ አገራት ውስጥ።
ሰው የፈለገ ቢሳሳት የመቃብር ሐውልት ላይ ፊደል ይሳሳታል? (አሌክስ አብርሃም) አሜሪካ ውስጥ በአገሩ ዘግናኝ ወንጀል የፈፀመ፣ ወይም ቢሊየን ብሮች የዘረፈ ወንጀለኛ ተሰዶ ይኖራል። አሁን እንደምነግራችሁ አይነት ሚስኪን ሰው ደግሞ አለ፣ በአንዲት ፊደል ምክንያት ለስደት የተዳረገ። በአንዲት ፊደል ብቻ! ባለፈው ወደሆነ ቦታ በኡበር ታክሲ እየሄድኩ ነበር። ሹፌሩ ከማሌዢያ የመጣ ትልቅ ሰው ነው። እያወራኝ "ሀገሬ ላይ በጣም አሪፍ ቢዝነስ ነበረኝ። የመቃብር ላይ ጽሑፍ እጽፍ ነበር፤ ተንደላቅቄ ነበር የምኖረው" አለኝ። ባዘነ ድምፅ። "እና ታዲያ ለምን ወደዚህ መጣህ?" "የተሰደድኩት የአንድ የተረገመ ባለስልጣን ሚስት የመቃብር እምነበረድ ላይ አንዲት ፊደል ተሳስቼ በመጻፌ፣ ሊገድለኝ ስለፈለገ ነበር" አለኝ። "እውነትህን ነው? ለአንዲት ፊደል?!" "አዎ ጌታዬ! አየህ፣ የምንጠቀመው ማላይኛ (ባሃሳ ማሌዢያ ይሉታል) በላቲን ፊደላት ነው የሚጻፈው። አንዲት ፊደል የምትፈጥረው ስህተት ቀላል እንዳይመስልህ። በእኛ ቋንቋ 'Kota' ማለት 'ከተማ' ማለት ነው። እኔም ሐውልቱ ላይ (('ባልሽ ብቻ ሳይሆን ቸርነትሽን የቀመሰው ሙሉ ከተማው አንቺን ይናፍቃል)) ብዬ አሳምሬ ጻፍኩ። ነገር ግን የሐውልቱ ምርቃት ቀን፣ ድፍን የከተማው ባለስልጣናትና ሀብታሞች በተሰበሰቡበት የተሸፈነበት ጨርቅ ሲነሳ... 'Kota' የሚለው ቃል ላይ ተሳስቼ 'a'ን በ 'e' ተክቻት ነበር። የተረገመች 'e'!" አለና መሪውን በቡጢ ነረተው። "እና 'e' ስትጨምርበት ምን ሆነ?" አልኩት። "Kote ሆነ!" "እኮ 'Kote' ምንድን ነው?" "የወንድ ብልት!" አሌክስ አብርሀም
Salam ychanale betsboch temlshalw🫴🫴
"ቪያ ዶሎሮሳ" የመከራ መንገድ (አሌክስ አብርሃም) ኢየሱስ ሊሰቀል መስቀሉን ተሸክሞ የሄደበት፣ ስድስት መቶ ሜትር ያህል የሚረዝም መንገድ "ቪያ ዶሎሮሳ" (የመከራ መንገድ) ይባላል። ይህም በኢየሩሳሌም ከተማ ውስጥ ከሚገኘው፣ የሮማውያን ገዢ ከነበረው ከጰንጤናዊው ጲላጦስ የፍርድ አደባባይ ተነስቶ፣ ከከተማው ቅጥር ውጭ ወደሚገኘው ቀራኒዮ ድረስ ማለት ነው። በመሀል መንገድ ኢየሱስ ደከመ። ሲገረፍ ነው የዋለው፤ የእሾህ አክሊል ራሱ ላይ እየደፉ ሲዘባበቱበት ነው የዋሉት፤ ደክሟል። ያንን ትልቅ የመሰቀያ ግንድ መሸከም ከባድ ነው። ወታደሮቹ በወደቀበት እንዳይሞት ሰጉ። "ተሰቅሎ ይሙት እንጂ መንገድ ላይ ይሙት" አይደለም ትዕዛዙ። ኃጢአተኛ ነው፤ ከተማቸው ውስጥ ከሞተ ምድራቸውን ያረክስባቸዋል፤ እስከዚህ ድረስ ነበር የተጸየፉት። ዞር ብለው መስቀሉን በመሸከም የሚረዳ ሰው በዓይናቸው ፈለጉ። የሚበዙት እንባ የሚራጩ የኢየሩሳሌም እናቶች ናቸው። ያንን ሁሉ ዓሣና ዳቦ ከኢየሱስ እጅ በልቶ የጠገበው ሕዝብ የለም! በተዓምር ከሽባነት የተፈወሰው ሁሉ የለም! ዓይኑ የበራለት የለም! ከሞት የተነሳችው የለችም! አጋንንት የወጣለት የለም! ከሰላሳ ስምንት ዓመት ደዌ ተፈውሶ አልጋውን ተሸክሞ የሄደው የለም! ያ ሁሉ በመማል፣ በመገዘት "አንለይህም" ያሉ ደቀ መዛሙርት ዓይን ውስጥ አልገቡም። ወደ ቀራኒዮ ጉዞዋ ለብቻ ናት! ይሄ ነው የሚገርመኝ፤ አንድ ባላገር ጨው ሊገዛ ይምጣ ላምባ አይታወቅም፣ ብቻ ከተማ መጥቶ ግርግሩን እየተመለከተ ነበር። የቀሬናው ስምዖን ይባላል። ወታደሮቹ "ና" አሉና የኢየሱስን መስቀል አስገድደው አሸከሙት። ይሄ ሰውዬ ከየት እንደመጣ ታውቃላችሁ? ከአሁኗ ሊቢያ። ቀሬና ማለት ሊቢያ ውስጥ ነው የምትገኘው። በስደት ወደዚያ ከሄዱ አይሁዳውያን አንዱ ይሆናል። ብቻ ያ ሁሉ ድግስና ተዓምር ላይ ያልነበረ ሰው፣ መስቀሉ ላይና መከራው ላይ እግሩ ጣለው። በኋለኛ ዘመን ታሪኩ፣ ይህ ሰው በክርስትና ውስጥ እንዳለፈ የሚያትቱ ድርሳናት አሉ። የሆነ ሆኖ ተገደንም ይሁን ወደን፣ የማንን መከራ፣ የማንን መስቀል እንደተሸከምን አናውቅም ይሆናል። ደስታና ፍሥሐውን ያላየን እኛ፣ በመከራ መንገድ ላይ እግራችን ጥሎን ይሆናል፤ ግን ትንሣኤ አለ። የተሸከምነው መከራ "መከራ" ባይሆንስ? መላው የሰው ልጅ ይድንበት ዘንድ፣ እኛም በዘላለሙ መዝገብ ታሪካችን ይከተብ ዘንድ መፍትሔው ቢሆንስ? አስባችሁታል? በሰው ልጅ ታሪክ "አምላኩን የረዳ" የሚል ስያሜ ያለው ሌላ ሰው የለም። ይሄ ምስኪን ገጠሬ በሰውኛ ሲታይ ያደረገው ይሄንን ነው። በሁለት መስመር ጽሑፍ የዘላለም ታሪክ የሆነ ሰው! በራሴ ትንሽ ልበላቹ ፈጣሪ በምድር ስጋ ለብሶ ያደረጋቸው የኛ ህይወት ገፆች ናቸው አስተማሪያችንም ነው
በትላንትናው እለት ቴዲ አልበም እንካችሁ ብሎናል እኔ ወድጄዋለሁ
የኔ ነው ያልሽኝ ለት..... የኔም ስለነበር የኔ ያሉት ሁሉ የራስ ላይሆን ነገር የኔ ነው አትበይ..ያልኩሽ ለዛ ነበር ✍ብፅእት ስዩም
መልካም የሴቶች ቀን!
ባንድ ጭንቅላት በጠባብ ደረት ስንቱን ስሸከም ስንቱን ስደርት ለመሀላንኳ ምሳሌ ሚሆን ህያው ምልክት አንድም ሳላስቀር በሁሉም ሳጌጥ አጣሁኝ የክት እግሬ በመራው በነዳው ሲሄድ ጢሻ ለጢሻ ልቤም እንደ ዘር የትም ሲበተን ባገኘው እርሻ ለፈጠረኝም ለገደለኝም ስቆም ላምልኮ ስንት ብሆን ነው?.... አንድ ሰው ብቻ አልመስልምኮ!! By Tadios Alemayehu @getem @getem @paappii
አንዳንድ ቀኖች አሉ ምን አልባት ለናንተ ይሮጣሉ ለኔ ግን የአመት ያክል ዝግታ ያላቸው
የሰራቹኝን ስራ ያፈረሳቹትን ቃል የተናገራቹትን ቅስም ሰባሪ ንግግር ዞር ስል እየሰማው ያወራቹትን ወሬ ለመርሳት እየሞከርኩ ነው
አታፍቅር እያልኩት ለራሱ ሳስቼ ተቃቅፎ አየሁት እኔው ተሳስቼ አጃኢብ ከዛ በማግስቱ ትምርት እየሄድን ነገረኝ ማዘኑን እንደሆነ በድን አናላቹ ድንገት ሲሳለም አየሁት የሻምሱን እንጨት ቤት ፍሬ✍✍✍ https://t.me/blackiy77 https://t.me/blackiy77 https://t.me/blackiy77 https://t.me/blackiy77
የረሳሁክ መስሎኝ ስራመድ መንገዴን ሳሰላስል ጊዜ ናፈኩት መውደዴን ሂድ ብዬ ያነሳሁት እግሬ ሊራመድ ተሳነው መሄድንም ፈራው ልቤም አለች ለኔ: የተገፋ መውደድ የያዘ አፍቃሪ ተመልሶ የለም ብዙ አታቀርቅሪ ፍቅር ቢመላለስ ከመለየት ልቆ ከለቀቁ አይመጣ መያዝ ነው አጥብቆ ፍሬ ✍
ለመሄድ ቢሆንም እግር የተሰጠው ለማሰብ እኮ ነው ጭንቅላት የኖረው
ጥር 8፤2018 - ተወዳጁ አርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ በቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢነት፣ በተዋናይነትና በሌሎች የጥበብ ስራዎች ውስጥ ስመጥር እና ተወዳጅ ከሆኑ የጥበብ ሰዎች አንዱ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባደረበት ህመም በድንገት ከዚህ ዓለም ተለይቷል፡፡ ለበርካታ ዓመታት በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው የቤተሰብ ጨዋታ ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ የሆነው ነጻነት ወርቅነህ ባለትዳርና የ3 ልጆች አባት ነበር። ፈጣሪ ለወዳጅ ዘመዶቹ እንዲሁም ለአድናቂዎቹ መፅናናትን ለእርሱ መንግስተ ሰማያትን እመኛለሁ
በፍቅር እንጂ በንዋይኽ ላትገዛኝ ጊዜም ገለህ ከነገ ላይ አታባክነኝ ፍሬ የፃፈችው https://t.me/blackiy77 https://t.me/blackiy77 https://t.me/blackiy77 https://t.me/blackiy77
#ብትሰብረኝም ና.. ተመለስ እንዳሻህ ሁን እንታረቅ በማሪያም ጣት፣ ይሻለኛል መጎዳቱ ለኔ ሞትነው አንተን ማጣት!! #ኤዶምገነት_ፃፈችው @arifgtmbcha https://t.me/blackiy77https://t.me/blackiy77 https://t.me/blackiy77 https://t.me/blackiy77