- Последний пост
- 15 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 3
- Всего постов
- 27
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Книги (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 690
- 1/48двое суток
- 790
- 1/72трое суток
- 852
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
"ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ “የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም፤ በእኔ የሚያምንም ለዘለዓለም አይጠማም።" — ዮሐንስ 6:35
በመጽሐፍ ቅዱስ እጅግ ውብ ከሚባሉ ምሳሌዎች መካከል በዋነኝነት የሚጠቀሱት በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 15 ላይ የሚገኙት ሦስቱ ምሳሌዎች ናቸው:: ስለ እነዚህም ምሳሌዎች ማብራሪያ በመምህራችን በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የቀረበውን ትምህርት ታዳምጡ ዘንድ ጋበዝናችሁ!!👇👇👇 https://youtu.be/FaBReT_evYA?si=KPSyoX24oq8PLjUe
https://youtu.be/pQOrLH_Jch0?si=HJ9x1BtjVpCbALFg
ሠላሳ ሰባት ጥንዶች ጋብቻቸውን በቅዱስ ቁርባን አተሙ:: ከኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በሆነው ጃን ቃና ዘገሊላ ከ 2 እስከ 21 አመት የትዳር ቆይታ ያላቸው 37 ጥንድ ባለትዳሮች ኦርቶዶክሳዊ የጋብቻ ሕይወት እና የንስሐ ትምህርት ተምረውና በመምህረ ንስሐቸው ፈቃድ አግኝተው ትዳራቸውን በቅዱስ ቁርባን ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ. ም ሲኤምሲ ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስባርከዋል :: በዕለቱም ለጥንዶቹ ያልታሰበ በረከት ሆኖ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘ ኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በዕለቱ በቅዳሴው ላይ በመገኘታቸው ጥንዶቹ ከቅዱስነታቸው ቡራኬ ማግኘት ችለዋል :: ከ ሥርዓተ ቅዳሴ በኋላ የወንጌል አና የዝማሬ አገልግሎት እና የቁርስ መርሐ ግብር የተደረገ ሲሆን ጋብቻቸውን ከሥርዓተ ቤተክርስቲያን ውጪ ለፈጸሙ ባለትዳሮች ጋብቻቸውን በቅዱስ ቁርባን እንዲቀድሱ ያነሣሣ ዝግጅት ነበረ:: በኢጃት ጃን ቃና ዘገሊላ ፕሮጀክት ለአራት ዓመታት ኦርቶዶክሳውያን በሥርዓተ ተክሊልና በቅዱስ ቁርባን ጋብቻቸውን እንዲፈጽሙና በድምቀቱ ተስበው በዓለማዊ መንገድ ጋብቻቸውን እንዳይፈጽሙ ለማድረግ ቅድመ ጋብቻ ትምህርት ሠጥቶ ቤተክርስቲያን ልጆችዋን የምትድርበትን ሁኔታ ሲያመቻች ቆይቶአል:: በዚህም ከመቶ በላይ ሙሽሮች የተጋቡ ሲሆን ማኅበራዊና መንፈሳዊ ትስስር ፈጥረው የሚጠያየቁና በርካታ ሕፃናትን ያፈሩ ማኅበረሰብ ወደ መሆን ያደጉ መሆናቸው ተገልጾአል:: በመጪዎቹ ሦስት ዓመታት ፕሮጀክቱ ትኩረቱን ከሰርግ ወደ ጋብቻ ሕይወት በማስፋት የትዳር ችግሮችንና የፍቺ ፈተናዎች ላይ ያተኮረ ፕሮፖዛል በመቅረጽ ለመሥራት በዝግጅት ላይ መሆኑን የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ወ/ሪት መቅደስ ገልጸዋል:: ትዳሬን በ ቅዱስ ቁርባን እንዳላስባርክ የሚከለክለኝ ምንድነው?
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
4ኛ ትውልድ ሱባዔ ጉባኤ ስልጠና መካፍል የምትፈልጉ በድሬዳዋ እና አቅራቢያ የምትገኙ በሙሉ ከዚህ በታች ባለው መስፈንጠሪያ(ሊንክ) ይመዝገቡ። https://forms.gle/nf1UEjzps8VbSMDY7
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
የማደጎ ልጆች አስተዳደግ ሴሚናር ተካሄደ! ከኢጃት ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ በሆነው በጃን ቂርቆስ አዘጋጅነት የተሰናዳ በማደጎ/ጉዲፈቻ ልጆች አስተዳደግ ላይ ያተኮረ ሴሚናር ቅዳሜ ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ም. በአፍሪክ ኅብረት ቅ/ሚካኤል ካቴድራል ሰ/ት/ ቤት በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል። 300 የሚሆኑ ታዳሚዎች በተሳተፉበት በዚህ መድረክ ላይ፣ የማደጎ ልጆች አስተዳደግ መንፈሳዊ፣ ስነ ልቡናዊና ማሕበራዊ ገፅታ ሁለንተናዊ እይታን በገነባ መልኩ ተዳሷል። በመርሐ ግብሩ ላይም "የማደጎ/ጉዲፈቻ ወላጅነት በመንፈሳዊ ዕይታ" በሚል ርዕስ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን "የልብ ምጥ" በሚል ርዕስ የማደጎ/ጉዲፈቻ ወላጅነት ሥነ-ልቦናዊና ማኅበራዊ ገፅታን በተመለከተ ሙያዊ ገለፃ በሥነ-ልቦና ባለሙያ ተሰጥቷል። ከትምህርታዊ ገለፃዎቹ በተጨማሪም የማደጎ/ ጉዲፈቻ ልጆችን ወስደዉ እያሳደጉ ያሉ ወላጆች የማደጎ/ጉዲፈቻ ልጆች አስተዳደግን በተመለከተ የህይወት ተሞክሯቸውን አጋርተዋል። ይህ የልምድ ማካፈል መድረክ ታዳሚው ስለ ማደጎ ልጆች አስተዳደግ ተግባራዊ ግንዛቤን እንዲጨብጥና አዳዲስ እውቀቶችን እንዲቀስም ትልቅ በር የከፈተ ነበር። መድረኩ በርካታ ጉዳዮች የተዳሰሱበትና ስኬታማ የነበረ ሲሆን፣ ከተሳታፊዎችና ከተመልካቾች ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎች ምላሽ ተሰጥቷል። በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት ጥቂት የማይባሉ ታዳሚዎችም የማደጎ/ጉዲፈቻ ልጆችን ለመውሰድ ያላቸውን ከፍተኛ ፍላጎት የገለጹ ሲሆን፣ ይህንን በጎ ምኞታቸውን ወደ ተግባር ለመቀየርም በቀጣይነት ያለው የስልጠና አና የማማከር አገልግሎት የሚያገኙ ይሆናል።
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи