tgindex

ሂዳያ መልቲሚዲያ | ʜɪᴅᴀʏᴀ ᴍᴜʟᴛɪᴍᴇᴅɪᴀ

описание

- አንዳንድ ማስታወሻና ምክሮች - ታሪኮች እና ግጥሞች - አጫጭር የዳዕዋ ቪድዮዎች - የተለያዩ ደርሶችና ፈታዋዎች - ጥያቄና መልስ ፕሮግራሞች የሚጋሩበት የሆነ ቻናል ነው። Join እና Share በማድረግ አጋርነታችሁን ግለፁ!! 🔘በተጨማሪም የዩቱብ ቻናላችን ይቀላቀሉ! https://www.youtube.com/@hidaya_multi 🗳ለአስተያየት @annafiabot ይጠቀሙ!

2 393
подписчиков
Охват к подписчикам
4,9%
ERR
Реакции к просмотрам
10,26%
239 на 20 постов
Пересылки к просмотрам
0,04%
1
Постов в день
0,0
всего 20

Где отзываются чаще

доля реакций к просмотрам
  • 1 июн.የዕለተ ሰኞ የዓቂዳ ተከታታይ ትምህርት ክፍል - 5 نواقض الإسلام - እስልምናን የሚያበላሹ ተግባራት النَّاقِضُ الثَّالِثُ: مَن لَّمْ يُكَفِّرِ الْمُشْرِكِينَ أَوْ شَكَّ فِي كُفْرِهِمْ أَوْ صَحَّحَ مَذْهَبَهُمْ كَفَرَ إِجْمَاعًا. 3ኛው እስልምናን የሚያበላሽ ተግባር: “ሙሽሪኮችን የማያከፍር፤ ወይም ካፊር መሆናቸውን የተጠራጠረ፤ ወይም መንገዳቸውን ትክክል ነው ያለ; በዑለሞች ስምምነት መሰረት ይከፍራል።” ይቀጥላል…. #ይህ እስልምናን የሚያበላሽ ተግባር በውስጡ ሶስት ነገሮች ይዟል; #1ኛ. «مَن لَّمْ يُكَفِّرِ الْمُشْرِكِينَ» ሙሽሪኮችን የማያከፍር እራሱ ይከፍራል የሚለው አ.ነገር ሲሆን; ሙሽሪክ የሚባሉት በቁርአን እና በሐዲስ ሙሽሪክ ተብለው የተገለፁ እንደ አህለል ኪታቦች፣ ሀይማኖት የሌላቸው ሰዎችና ሌሎችም ሰዎችን ነው። #አንድ ሰው ላ ኢላሀ ኢለላህ ሲል; ሁለት ነገሮች ግድ ይሉታል; 1ኛ. ላ ኢላሀ፦ አምላክ የሚባሉ ማንኛቸውንም መካድ እና 2ኛ. ኢለላህ፦ አምልኮን ለአላህ ብቻ መስጠት ሙሽሪኮች/ካፊሮችን የማያከፍር ሰው በ1ኛው( አምላክ የሚባሉ ማንኛቸውንም መካድ) የሚለውን አጉድሏል። #2ኛ. «شَكَّ فِي كُفْرِهِمْ» ሙሽሪኮች ካፊር ናቸው ወይስ በሚለው የተጠራጠረ የሚለው አ.ነገር ሲሆን; ይህን የፈፀመ ሰው ከ8ቱ የላ ኢላሀ ኢለላህ መስፈርቶች አንዱ የሆነውን “እርግጠኝነት” አጉድሏል። እርግጠኝነት፦ ማለት አንድ ሰው ላ ኢላሀ ኢለላህ ሲል; ከአላህ ውጪ በሐቅ የሚመለክ አለመኖሩን እርግጠኛ መሆን አለበት ማለት ነው፤ ስለዚህ ሙሽሪኮች በአላህ መካዳቸውን የተጠራጠረ ሰው ከአላህ ውጪ በሐቅ የሚመለክ መኖሩን ተጠራጥሯል ማለት ነው። #3ኛ. «صَحَّحَ مَذْهَبَهُمْ» መንገዳቸውን(የሙሽሪኮቹን) ትክክል ነው ያለ ሰው ይከፍራል ማለት ሲሆን; ይህም “አላህ ዘንድ ትክክለኛው ሀይማኖት እስልምና ነው” የሚለውን የቁርአን አንቀፅ ማስተባበል ይሆናል።15,12%
  • 28 мая📌 التَّكْبِيرُ الْجَمَاعِيُّ دُبُرَ الصَّلَوَاتِ عِنْدَ عُلَمَاءِ الْمَالِكِيَّةِ: قَالَ الْحَطَّابُ: (وَأَمَّا مَا يَفْعَلُهُ بَعْضُ النَّاسِ الْيَوْمَ أَنَّهُ إِذَا سَلَّمَ الْإِمَامُ مِنْ صَلَاتِهِ كَبَّرَ الْمُؤَذِّنُونَ عَلَى صَوْتٍ وَاحِدٍ عَلَى مَا يُعْلَمُ مِنْ زَعَقَاتِهِمْ، وَيُطَوِّلُونَ فِيهِ، وَالنَّاسُ يَسْتَمِعُونَ إِلَيْهِمْ وَلَا يُكَبِّرُونَ فِي الْغَالِبِ، وَإِنْ كَبَّرَ أَحَدٌ مِنْهُمْ فَهُوَ يَمْشِي عَلَى أَصْوَاتِهِمْ، وَذَلِكَ كُلُّهُ مِنَ الْبِدَعِ، وَفِيهِ إِخْرَامُ حُرْمَةِ الْمَسْجِدِ، وَالتَّشْوِيشُ عَلَى الْمُصَلِّينَ وَالتَّالِينَ وَالذَّاكِرِينَ) 📚 ((مَوَاهِبُ الْجَلِيلِ)) (2/582). وَقَالَ الْعَدَوِيُّ: (وَيُكَبِّرُ كُلُّ وَاحِدٍ وَحْدَهُ فِي الطَّرِيقِ، وَفِي الْمُصَلَّى، وَلَا يُكَبِّرُونَ جَمَاعَةً؛ لِأَنَّهُ بِدْعَةٌ) 📚((حَاشِيَةُ الْعَدَوِيِّ)) (1/497). وَقَالَ النَّفْرَاوِيُّ: (وَلَا يُكَبِّرُونَ جَمَاعَةً؛ لِأَنَّهُ بِدْعَةٌ) 📚 ((الْفَوَاكِهُ الدَّوَانِي)) (2/649). 📌 በማሊኪያ ዑለሞች (ሊቃውንት) ዘንድ ከሶላት በኋላ በጋራ (በአንድ ድምፅ) ተክቢራ ማድረግ፡ አል-ሐጧብ እንዲህ ይላሉ፦ (“ዛሬ በአሁኑ ጊዜ አንዳንዶች የሚያደርጉት ነገር፤ ኢማሙ ከሶላቱ አሰላምቱ እያለ ሲያበቃ፣ ሙአዚኖቹ ከጩኸታቸው እንደሚታወቀው በአንድ ድምፅ ተክቢራ ያደርጋሉ፣ ያረዝሙታልም። ሰዎቹም እነሱን ያዳምጣሉ እንጂ በአብዛኛው አብረው ተክቢራ አያደርጉም። ከነሱ መካከል ተክቢራ የሚያደርግ ቢኖርም እንኳ በነሱ ድምፅ እየተመራ (እየተከተለ) ነው። ይህ ሁሉ ከቢድዓ (በዲን ውስጥ ከተፈጠሩ አዳዲስ ነገሮች) ይመደባል፤ በውስጡም የመስጂድን ክብር መድፈር፣ እንዲሁም ሶላት ሰጋጆችን፣ ቁርኣን ቀሪዎችንና ዚክር አድራጊዎችን መረበሽ አለበት።”) 📚 ((መዋሂቡል ጀሊል)) (2/582) አል-ዐደዊ እንዲህ ይላሉ፦ (“እያንዳንዱ ሰው በመንገድ ላይም ሆነ በሶላት መስገጃ ቦታ (ሙሶላ) ላይ ለየብቻው ተክቢራ ያደርጋል፤ በቡድን (በጋራ) ግን ተክቢራ አያደርጉም፣ ምክንያቱም እሱ ቢድዓ ነው።”) 📚 ((ሐሺየቱል ዐደዊ)) (1/497) አን-ነፍራዊ እንዲህ ይላሉ፦ (“በጋራ ተክቢራ አያደርጉም፤ ምክንያቱም እሱ ቢድዓ ነው።”) 📚 ((አል-ፈዋኪሁ አድ-ደዋኒ)) (2/649)14,41%
  • 26 маяየማለዳ መልእክት #21 የሐጅ ምንዳን የሚያስገኙ ተግባራት - 3 ለወላጆች መልካምን መዋል عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ: أَتَى رَجُلٌ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَقَالَ: إِنِّي أَشْتَهِي الْجِهَادَ وَلَا أَقْدِرُ عَلَيْهِ، قَالَ: «هَلْ بَقِيَ مِنْ وَالِدَيْكَ أَحَدٌ؟» قَالَ: أُمِّي، قَالَ: «فَاتَّقِ اللَّهَ فِيهَا، فَإِذَا فَعَلْتَ ذَلِكَ فَأَنْتَ حَاجٌّ، وَمُعْتَمِرٌ، وَمُجَاهِدٌ». (رواه أبو يعلى والطبراني) ከአነስ ኢብኑ ማሊክ በተላለፈ ሐዲስ; እንዲህ ብሏል: «አንድ ሰው የአላህ መልእክተኛ ﷺ ጋር መጣና; እኔ ጂሀድ መሳተፍ እፈልጋለሁ ግን አቅሙ የለኝም አላቸው፥ እሳቸውም ﷺ " ከወላጆችክ (በህይወት)የቆየ አለን?” አሉት፤ እናቴ አለች አላቸው፤ እሳቸውም ﷺ “በሷ(በእናትክ) ጉዳይ አላህን ፍራ፤ ይህን ካደረክ አንተ ሀጅ ያደረገ፤ ዑምራ ያደረገ፤ እና በአላህ መንገድ ላይ የተዋጋ ሰው ነክ” አሉት» አቡ የዕላ እና ጦበራኒይ ዘግበውታል13,58%
  • 19 мая"كَبِّرُوا لِيَبْلُغَ تَكْبِيرُكُمْ عَنَانَ السَّمَاءِ، ተክቢራችሁ የሰማይ ጣሪያ እስከሚደርስ ድረስ ተክቢራ አድርጉ كَبِّرُوا فَإِنَّ اللَّهَ عَظِيمٌ يَسْتَحِقُّ الثَّنَاءَ አላህ ትልቅ ነው ሊመሰገን እና ሊወደስ ይገባዋል እና ተክቢራ አድርጉ أَكْثِرُوا مِنَ الْأَعْمَالِ الصَّالِحَةِ، መልካም ስራን አብዙ وَتَزَوَّدُوا مِنْ سَاعَاتِ هَٰذِهِ الْأَيَّامِ وَلَيْلِهَا، በነዚህ ቀናት እና ለሊቶች ያሉ ሰአታትን መልካም ስራን ተሰነቁባቸው فَهِيَ تِجَارَةٌ رَابِحَةٌ .ምክንያቱም ይህ(መልካም ስራ) አትራፊ ንግድ ነው وَاعْلَمُوا أَنَّ لِلَّهِ تَعَالَىٰ نَفَحَاتٍ ለአላህ የእዝነትና የችሮታ እድሎች እንዳሉት እወቁ فَاسْتَكْثِرُوا مِنَ الصَّالِحَاتِ ، ስለዚህ መልካም ስራን አብዙ وَتَطَهَّرُوا مِنْ دَنَسِ الْمَعَاصِي وَالسَّيِّئَاتِ . ከወንጀል እና ከመጥፎ ስራ ቆሻሻም ፅዱ إِنَّ الْعُمْرَ لَا يَعُودُ، ያለፈ እድሜ አይመለስም وَالْمَوْسِمَ لَا يَدُومُ. እነዚህ የመልካም ስራ እድሎችም አይዘወትሩም وَتَزَوَّدُوا فَإِنَّ خَيْرَ الزَّادِ التَّقْوَىٰ ۚ وَاتَّقُونِ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ. " «(የመልካም ስራን ስንቅ) ተሰነቁ፤ ከስንቆች ሁሉ በላጩ አላህን የመፍራት ስንቅ ነው፤ እናንተ የልቦና ባለቤቶች ሆይ! እኔን ፍሩኝ»12,84%
  • 25 маяየማለዳ መልእክት #20 የሐጅ ምንዳ የሚያስገኙ ተግባራት - 2 ሰዎችን ሐጅ እንዲያደርጉ መምከር፣ ማነሳሳትና መገፋፋት عَنْ أَبِي مَسْعُودٍ عُقْبَةَ بن عَمْرٍو الْأَنصَارِيِّ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ ﷺ : «مَنْ دَلَّ عَلَى خَيْرٍ فَلَهُ مِثْلُ أَجْرِ فَاعِلِهِ» رواه مسلم. ከአቢ መስዑድ ዑቅበተ ብኒ ዓሚር አልኣንሷሪይ በተላለፈ ሐዲስ; እንዲህ ብሏል: የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል: «ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው (መልካሙን ነገር) የሰራውን ሰውዬ አጅር ያገኛል።» ሙስሊም ዘግበውታል። ማስታወሻ፦ (መልካሙን ነገር) የሰራውን ሰውዬ አጅር ያገኛል ሲባል፦ መልካሙን ነገር የሰራው ሰውዬ ምንም አያገኝም ወይም አጅሩን ያካፍለዋል ማለት አይደለም፤ ይልቁንም መልካሙን ነገር ያመላከተውም የሰራውም ሙሉ ሙሉ አጅር ያገኛሉ ማለት ነው የተፈለገበት።12,50%
  • 25 маяየዕለተ ሰኞ የዓቂዳ ትምህርት ክፍል - 4 نواقض الإسلام - እስልምናን የሚያበላሹ ተግባራት የኪታቡ ፀሓፊ- ሸይኽ ሙሀመድ ኢብኑ ዐብዲልወሃብ النَّاقِضُ الثَانِي: مَن جَعَلَ بَيْنَهُ وَبَيْنَ اللهِ وَسَائِطَ، يَدْعُوهُمْ، وَيَسْأَلُهُمُ الشَّفَاعَةَ، وَيَتَوَكَّلُ عَلَيْهِمْ كَفَرَ إِجْمَاعًا. 2ኛው እስልምናን የሚያበላሽ ተግባር፦ ከአላህ እና ከእሱ መካከል ወሳኢጥ ያደረገ; እነሱን(ወሳኢጦቹን) የሚለምን፤ ምልጃ(ሸፋዓህ) የሚጠይቅ፤ በነሱ የሚመካ ሰው; በሁሉም ዑለሞች ስምምነት መሰረት ከእስልምና ይወጣል(ይከፍራል)። #ባለፈው ሳምንት እንዳየነው ከአላህ ውጪ ያሉ አካላትን ወደ አላህ መቃረቢያ(وَسَائِط) አድርጎ መያዝ ሁለት አይነት ነው፦ 1ኛ. የአላህን ትእዛዝ በመፈፀም ወደሱ ለመቃረብ፦ የነቢያትን እና የወራሾቻቸውን(ዑለሞች) ትምህርቶች በመማር በተማርነው እየሰራን ወደ አላህ ስንቃረብ፥ እነዚህ አካላት(ነቢያት ፣ ዑለሞች) በኛ እና በአላህ መካከል (وَسَائِط)/ የሚያቃርቡ ይባላሉ። #ይህ አይነቱ ወደ አላህ መቃረብ ሸሪዓችን የደነገገው ሲሆን; ይሄን መቃወም ከእስልምና ያስወጣል። 2ኛ. ከአላህ ውጪ ያሉ አካላትን በመለመን፤ ሸፈዓ(ምልጃ) በመጠየቅ፤ በኑ በመመካት… ወደ አላህ መቃረብ፦ ይህ ተግባር ለአላህ ብቻ የሚገቡ አምልኮዎችን(ዱዓ፣ ሸፈዓ፣ተወኩል…) ከአላህ ውጪ ላሉ አካላት መስጠት ስለሆነ የሚያከፍር ተግባር ነው። #ወደ አላህ መቃረብ የሚቻልባቸው መንገዶች የሚከተሉት ናቸው፦ 1. አላህን በስሞቹ እና በመገለጫዎቹ በመለመን 2. መልካም ስራን በመስራት ወደ አላህ መቃረብ 3. አላህ ለባሮቹ የዋለውን ውለታ በማውሳት ወደ አላህ መቃረብ; (ሙሳን ከፊርአውን ነፃ ያወጣኸው አላህ እኔንም….) 4. የሰራናቸውን መልካም ስራዎች በማውሳት ወደ አላህ መቃረብ; (እኔ ባለፈው እንዲህ ያደረኩት ላንተ ብዬ ከነበረ ይህን አርግልኝ…) 5. በህይወት ያሉ ሰዎች ዱዓእ ከዚህ ውጪ የሞቱም ይሁኑ በህይወት ያሉ ሰዎችን ወደ አላህ አቃርቡኝ ማለት ሺርክ ሲሆን፤ አላህን በነሱ ይሁንብክ እያሉ መጠየቅ ደግሞ ቢድዓህ ነው።12,22%
  • 26 маяየዕለተ ማክሰኞ የፊቅህ ተከታታይ ትምህርት - 4 #ትጥበት ማለት፦ ሸሪዓው በደነገገው መልኩ ሰውነት ላይ ውሀን መጠቀም ነው። ትጥበትን ግድ የሚያደርጉ ነገሮች ከሶስቱ አንዱ የተከሰተበት/ባት ሰው/ሴት ትጥበት ግድ ይለዋል/ይላታል። 1ኛ የዘር ፈሳሽ መፍሰስ 2ኛ ፆታዊ ግንኙነት ማድረግ 3ኛ ሀይድ/ የወሊድ ደም(ኒፋስ) መፍሰስ የዉዱእ እና ትጥበት ጥቅሞች የዉዱእ እና ትጥበት ጥቅሞች ብዙ ናቸው፤ ዋና ዋናዎቹም፦ 1. እስልምና መንፈሳዊም አካላዊም ንፅህናን የያዘ መሆኑን ያሳያል 2. ወንጀልን ያስምራል 3. የሰውነት ጤና እና ንፅህና እንዲሁም ንቃትን ይሰጣል 4. ከአላህ ጋር በምንገናኝ ጊዜ ባማረ ሁኔታ ላይ ሆነን እንድንገናኝ…11,88%
  • 24 маяየማለዳ መልእክት #19 የሐጅ ምንዳ የሚያስገኙ ተግባራት - 1 ሐጅ ለማድረግ ትክክለኛ ኒያ ማድረግ عَنْ أَبِي كَبَشَةَ عُمَر بن سَعدٍ الأَنمَاري رَضِيَ اللهُ عَنْهُ أنَّهُ سَمِعَ رَسُولَ اللهِﷺ يَقُولُ: «إِنَّمَا الدُّنْيَا لِأَرْبَعَةِ نَفَرٍ: عَبْدٍ رَزَقَهُ اللهُ مَالًا وَعِلْمًا، فَهُوَ يَتَّقِي فِيهِ رَبَّهُ، وَيَصِلُ فِيهِ رَحِمَهُ، وَيَعْلَمُ لِلَّهِ فِيهِ حَقًا، قَهَذَا بِأَفْضَلِ الْمَنَازِلِ. عَبْدٍ رَزَقَهُ اللهُ عِلْمًا وَلَمْ يَرْزُقْهُ مَالًا، فَهُوَ صَادِقُ النِّيَّةِ يَقُولُ: لَوْ أنَّ لِي مَالًا لَعَمِلْتُ بَعَمَلِ فُلَانٍ، فَهُوَ بِنِيَّتِهِ فَأَجْرُهُمَا سَوَاءٌ.» الحديث.أخرجه الترمذي وابن ماجة وأحمد. ከአቢ ከበሸተ ዑመር ኢብኑ ሰዕድ አልአንማሪይ በተላለፈ ሐዲስ; እሱ የአላህን መልእክተኛﷺ እንዲህ ሲሉ ሰምቷቸዋል: «ዱንያ ለአራት አይነት ሰዎች ትከፈላለች: አላህ ገንዘብን እማ ጠቃሚ እውቀትን የሰጠው አለ; ይህ ሰው በገንዘቡ አላህን ይፈራበታል፤ ዝምድናን ይቀጥልበታል፤ በገንዘቡ ውስጥ አላህ ያለውን ሐቅ ያውቃል፤ ይሄ ከሁሉም በላጭ ደረጃ ነው ያለው። ሌላኛው ባሪያ አላህ ጠቃሚ እውቀትን ብቻ ይሰጠዋል ገንዘብ እይሰጠውም; እሱም በትክክለኛ ኒያ “አላህ ገንዘብ ቢሰጠኝ እንደ እገሌ አይነት ስራ እሰራበት ነበር ይላል፤ ይሄ ሰው በኒያው ከላይኛው ሰወዬ ጋር አጅራቸው እኩል ነው።» ቲርሚዚይ፣ ኢብኑ ማጀህ እና አሕመድ ዘግበውታል. ማስታወሻ፦ በገንዘቡ አላህን ይፈራበታል ማለት፦ አላህ በገንዘቡ እንዲፈፅም ያዘዘውን ይፈፅማል እእዲከለከል ያዘዘውን ይከለከላል ማለት ነው። በገንዘቡ ውስጥ አላህ ያለውን ሐቅ ያውቃል ማለትም፦ ገንዘቡ የሱ ሳይሆን የአላህ መሆኑን አውቆ ገንዘቡን አላህ አውጣ ባለው ቦታ(እንደ ዘካ፣ ሐጅ እና ወ.ዘ.ተ) ያወጣል ማለት ነው። በዚህ ሐዲስ መሰረት; አንድ ሰው ገንዘብ ባይኖረውም ትክክለኛ ኒያ ኖሮት ገንዘብ ያለው ሰው የሚፈፅመውን ተግባር ከተመኘ; የዛን መልካም ስራ ምንዳ ያገኛል ማለት ነው። ከመልካም ስራዎች መካከል አንዱ ሐጅ በመሆኑ ገንዘብ ባይኖረንም ሐጅ የማድረግ ትክክለኛ ኒያ እና ምኞት ሊኖረን ይገባል።11,28%
  • 19 маяየዕለተ ማክሰኞ የፊቅህ ተከታታይ ትምህርት ክፍል - 3 ዉዱእን የሚያበላሹ ነገሮች ሶስት ናቸው። እነሱም፦ 1. ከሁለቱ ሀፍረተ ገላዎች የሚወጣ ነገር 2. ዓቅል በእንቅልፍ፣ እብደት፣ ራስን በመሳት ወይም በስካር ምክንያት ከጠፋ 3. የግመል ስጋ መብላት ናቸው። https://t.me/fawaid_0010,71%
  • 4 июн.የማለዳ መልእክት #24 የሐጅ ምንዳን የሚያስገኙ ተግባራት - 6 ከግዴታ ሰላት ቡሀላ እነዚህን ዚክሮች ማለት عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ، أَنَّ فُقَرَاءَ الْمُهَاجِرِينَ أَتَوْا رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَقَالُوا: ذَهَبَ أَهْلُ الدُّثُورِ بِالدَّرَجَاتِ الْعُلَى، وَالنَّعِيمِ الْمُقِيمِ. فَقَالَ: «وَمَا ذَاكَ؟» قَالُوا: يُصَلُّونَ كَمَا نُصَلِّي، وَيَصُومُونَ كَمَا نَصُومُ، وَيَتَصَدَّقُونَ وَلَا نَتَصَدَّقُ، وَيُعْتِقُونَ وَلَا نُعْتِقُ. فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «أَفَلَا أُعَلِّمُكُمْ شَيْئًا تُدْرِكُونَ بِهِ مَنْ سَبَقَكُمْ وَتَسْبِقُونَ بِهِ مَنْ بَعْدَكُمْ؟ وَلَا يَكُونُ أَحَدٌ أَفْضَلَ مِنْكُمْ إِلَّا مَنْ صَنَعَ مِثْلَ مَا صَنَعْتُمْ؟» قَالُوا: بَلَى يَا رَسُولَ اللَّهِ. قَالَ: «تُسَبِّحُونَ، وَتَحْمَدُونَ، وَتُكَبِّرُونَ، خَلْفَ كُلِّ صَلَاةٍ ثَلَاثًا وَثَلَاثِينَ مَرَّةً» (رواه البخاري ومسلم) ከአቡ ሁረይራ (ረዲየላሁ አንሁ) እንደተወራው፡ የሙሃጅር ድሆች ወደ አላህ መልክተኛﷺ መጥተው እንዲህ አሉ፦ “ባለሀብቶች እኮ ከፍተኛውን ደረጃና ዘላቂውን ፀጋ ይዘውት ሄዱ።” የአላህ መልክተኛምﷺ ፦ “ምንድነው እሱ?” አሏቸው። እነሱም፦ “እኛ እንደምንሰግደው ይሰግዳሉ፣ እኛ እንደምንጾመው ይጾማሉ፣ (ነገር ግን) እነሱ ይመጸውታሉ እኛ አንመጸውትም፣ እነሱ ባሪያ ነጻ ያወጣሉ እኛ ግን ማውጣት አንችልም (በገንዘባቸው በላጩን ስራ ሰሩ)” አሉ። የአላህ መልክተኛምﷺ እንዲህ አሉ፦ “ከእናንተ በፊት የቀደሟችሁን የምታገኙበት፣ ከእናንተ በኋላ የሚመጡትን የምትቀድሙበት፣ እንዲሁም እናንተ የሰራችሁትን የሰራ ካልሆነ በስተቀር ማንም ከእናንተ በላይ በላጭ የማይሆንበትን ነገር ላስተምራችሁን?” እነሱም፦ “አዎን ያስተምሩን የአላህ መልክተኛ ሆይ!” አሉ። እሳቸውምﷺ ፦ “ከእያንዳንዱ ሶላት በኋላ ሰላሳ ሶስት (33) ጊዜ ‘ሱብሀነላህ’፣ ‘አልሀምዱሊላህ’፣ ‘አላሁ አክበር’ በሉ።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)10,34%
  • 27 маябез подписи10,09%
  • 18 маяየዕለተ ሰኞ የዓቂዳ ትምህርት ክፍል - 3 نواقض الإسلام - እስልምናን የሚያበላሹ ተግባራት النَّاقِضُ الثَانِي: مَن جَعَلَ بَيْنَهُ وَبَيْنَ اللهِ وَسَائِطَ، يَدْعُوهُمْ، وَيَسْأَلُهُمُ الشَّفَاعَةَ، وَيَتَوَكَّلُ عَلَيْهِمْ كَفَرَ إِجْمَاعًا. 2ኛው እስልምናን የሚያበላሽ ተግባር፦ ከአላህ እና ከእሱ መካከል ወሳኢጥ ያደረገ; እነሱን(ወሳኢጦቹን) የሚለምን፤ ምልጃ(ሸፋዓህ) የሚጠይቅ፤ በነሱ የሚመካ ሰው; በሁሉም ዑለሞች ስምምነት መሰረት ከእስልምና ይወጣል(ይከፍራል)። ማብራሪያ፦ «مَن جَعَلَ بَيْنَهُ وَبَيْنَ اللهِ وَسَائِطَ»: ወሳኢጥ(وَسَائِطَ) የሚባለው በአንድ ባሪያ እና በአላህ መካከል የሆነን ነገር የሚያደርስ ሲሆን; ለሁለት ይከፈላል፦ 1ኛ. ሸሪዐው የደነገገው ማድረስ፦ ይህን ስራ የሚሰሩት ነቢያት፣ መልእክተኞች እና የነሱ ወራሽ የሆኑት ዑለሞች ሲሆኑ; የአላህን ትእዛዝና ክልከላ ወደ ባሮች ያደርሳሉ(በማስተማር)። ይህ ሸሪዓችን የደነገገው ሲሆን ይህም ያስተባበለ(አልቀበልም ያለ) ይከፍራል። 2ኛው. ሺርክ የሆነው ማድረስ፦ ይሄ ከላይ እንደተጠቀሰው ለአላህ ብቻ የሚገቡ አምልኮዎችን ከአላህ ውጪ ላሉ አካላት በመስጠት(በነሱ በኩል ካለሆነ አላህ አይሰማኝም እና መሰል ምክንያት በማቅረብ) ወደ አላህ ለመቃረብ መሞከር ሲሆን ይሄ ሺርክ ነው። «يَدْعُوهُمْ» ዱዐእ ዒባዳአ ሲሆን ; ሁለት ክፍሎች አሉት: 1ኛው. «دعاء العبادة» የአምልኮ ዱዐእ፦ ለአላህ የተለያዩ አምልኮዎችን በመፈፀም ምንዳቸውን ከአላህ መፈለግ ማለት ነው። 2ኛው. «دعاء الطلب» የጥያቄ ዱዐእ፦ የምንፈልገውን ነገር ቀጥታ አላህን የምንጠይቅበት(ማረኝ፣ ጀነት አስገባኝ… ) የዱዐእ አይነት ነው። እነዚህ ሁለቱንም የዱዐእ አይነቶች ከአላህ ውጪ ላለ አካል መስጠት ሺርክ ነው። «وَيَسْأَلُهُمُ الشَّفَاعَةَ» ሸፈዐህ(ምልጃ የሚጠየቀው አላህ ብቻ ሲሆን; ከአለአህ ውጪ ላለ አካል መስጠት ሺርክ ይሆናል። «وَيَتَوَكَّلُ عَلَيْهِمْ» ተወኩል፦ በሸሪዐ የተፈቀዱ ሰበቦችን ከማድረስ ጋር በአላህ መደገፍ እና ነገሮችን ወደሱ ማስጠጋት ሲሆን; ከአላህ ውጪ ላለ አካል መስጠት ሺርክ ይሆናል። ይቀጥላል… https://t.me/fawaid_0010,00%