- Последний пост
- 13 авг.
- Последнее чтение
- 07:54
- Постов за неделю
- 3
- Всего постов
- 21
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 14 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 2 018
- 1/48двое суток
- 2 312
- 1/72трое суток
- 2 494
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ንስር በወፎች ዓለም ውስጥ በግርማ ሞገሱ፣ በጠንካራ ማንነቱ እና በከፍተኛ በረራው ይታወቃል። ይህ ግሩም ፍጡር ለልጆቹ የሚያሳየው የእንክብካቤ እና የማሰልጠን ሂደት ለሰው ልጅ ወላጆች ጥልቅ አስተምህሮን ይሰጣል። በአሁኑ ዘመን ልጆቻችንን ተንከባክቦ ማሳደግ ብቻ ሳይሆን፣ ነገ በራሳቸው እግር መቆም የሚችሉ ጠንካራ ዜጎች ማድረግ የወላጆች ትልቁ ፈተና ሆኗል። ንስር ልጆቹን እንዴት እንደሚያሰለጥን እና እንደሚቀርጽ በመመልከት ለወላጅነታችን ትልቅ ትምህርት መውሰድ እንችላለን። 1. ምቹና ደህንነቱ የተጠበቀ መኖሪያ ማዘጋጀት ንስሮች ጎጇቸውን የሚሠሩት በጣም ከፍ ባሉ ድንጋዮች ወይም ዛፎች ላይ ነው። ጎጆው ከውጭ እሾህ እና ሻካራ እንጨቶች ያሉት ሲሆን፣ ከውስጥ ግን በስላሳ ላባዎች እና ቅጠሎች የተሸፈነ ነው፦ 👉 ለወላጆች ያለው ትምህርት፦ ልጆች በሕፃንነታቸው ጊዜ ፍቅር፣ እቅፍ፣ ደህንነት እና ሞቅ ያለ መኖሪያ ያስፈልጋቸዋል። በፍቅር የተሞላ አካባቢ የልጁን የስነ-ልቦና ጥንካሬ ይገነባል። 2. ምቾትን በማስወገድ ለለውጥ ማዘጋጀት የንስር ጫጩቶች ሲያድጉ፣ እናት ንስር በጎጆው ውስጥ ያሉትን ለስላሳ ላባዎችና ቅጠሎች ባዶ በማድረግ ሸካራዎቹን እንጨቶችና እሾሆች ታወጣቸዋለች። ከዚያም ጫጩቶቹ ምቾት ማጣት ይጀምራሉ። "ምቾት ባለው ቦታ ውስጥ ጥንካሬ አይፈጠርም።" 👉 ለወላጆች ያለው ትምህርት፦ ልጆቻችን እንዳደጉ እና እያደጉ እንደሆነ ስናይ ሁሉንም ነገር አዘጋጅተን በመስጠት "ከምቾት ቀጠናናቸው (comfort zone)" እንዳይወጡ ማድረግ የለብንም። አልፎ አልፎ የሚያጋጥሟቸውን ተፈጥሯዊ ፈተናዎች እና ኃላፊነቶች እንዲወጡ መተው አለብን። 3. የመብረር ልምምድ እና እምነት ንስር ጫጩቷን ከከፍተኛ ቦታ ላይ ገፍትራ ትጥላታለች። ጫጩቷ በሚወድቅበት ወቅት በፍርሃት ክንፉን ያንቀሳቅሳል። ጫጩቱ ወደ መሬት ተከሰክሶ ከመውደቁ ጥቂት ሰከንዶች በፊት ግን፣ አባት ወይም እናት ንስር በፍጥነት በመብረር ከሥሩ በመግባት በክንፎቻቸው ይሸከሙታል። ይህ ልምምድ ጫጩቱ በራሱ መብረር እስኪችል ድረስ ይደጋገማል። 👉 ለወላጆች ያለው ትምህርት፦ ልጆቻችን እንዲሞክሩ፣ እንዲሳሳቱ እና ከስህተታቸው እንዲማሩ እድል መስጠት አለብን። ነገር ግን ሲወድቁ እና ሲቸገሩ ከጎናቸው ሆነን እንደምንደግፋቸው እና እንደምንጠብቃቸው ማሳየት አለብን። 4. ራሳቸውን እንዲመግቡ ማሰልጠን ንስሮች ጫጩቶቻቸው ሲያድጉ ምግቡን አዘጋጅተው አፋቸው ውስጥ አያጎርሷቸውም። ይልቁንም ምግቡን ከጎጆው አቅራቢያ በማስቀመጥ ራሳቸው ወጥተው እንዲወስዱ ያደርጋሉ። 👉 ለወላጆች ያለው ትምህርት፦ ልጆቻችን የራሳቸውን ችግር የመፍታት፣ ራሳቸውን የማስተዳደር እና ኃላፊነት የመውሰድ ብቃት እንዲያዳብሩ ማሰልጠን አለብን። -------------------------------- የንስር ወላጅነት ዓላማ ጫጩቶቹን ለዘላቂ ጥገኝነት ሳይሆን ለነጻነት እና ለጠንካራ በረራ ማዘጋጀት ነው። እኛም እንደ ንስር ወላጆች፡- 1. ለልጆቻችን ፍቅርና ጥበቃ እንስጣቸው። 2. ፈተናዎችንና ኃላፊነቶችን የመጋፈጥ ልምድ እንዲያዳብሩ እድል እንስጣቸው። 3. በራሳቸው አቅም እንዲተማመኑ እና በሕይወት አውሎ ነፋስ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ እንዲበሩ እናስልጠናቸው። 4. ልጆቻችንን ከምቾት ቀጠና አውጥተን ጠንካራና በከባድ የአየር ሁኔታ ላይ ከፍ ብለው የሚበሩ ንስሮች እናድርጋቸው!
без подписи
ውድ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች አርብ ነሀሴ 8/2018 በትምህርት ቤቱ ከጧቱ 2:00 - 3:30 እንድትገኙ። በኡላዱላ የማይማሩ እንዲገኙና ምርጫቸውን እንዲያስተካክሉ መልዕክት አስተላልፉ። ትምህርት ቤቱ!
ማሳሰቢያ በኡላ ዱላ የክረምት ትምህርት እየተከታተላችሁ ላላችሁ የ 11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ይህ የቴሌግራም ቻናል መከፈቱና የተወሰኑ ተማሪዎች join በማድረጋችሁ መረጃ እንለዋወጣለን። ስለሆነም ከዚህ በመቀጠል 2 ጉዳዮችን ልብ ትሉ ዘንድ በጥብቅ እናሳስባለን! 👉 የቀሩት ተማሪዎች join በማድረግ እንዲሁም እንድያደርጉ እርሰ በርስ መረጃ እንድትለዋወጡ 👉 ከቀን ወደ ቀን በመማር ማስተማር ዙሪያ ያለ ቅሬታ ካለ በቻናሉ እያረሙ መገኘት እንጂ መቅረት አይቻልም። ይህ ካልሆነ በሚቀሩ ተማሪዎች ላይ ኃላፊነቱን ትምህርት ቤቱ እንደማይወስድ እንድትገነዘቡ እናሳስባለን። ትምህርት ቤቱ
ማስታወቂያ! (ሀምሌ 27/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2019 የትምህርት ዘመን በእቴጌ መነን የልጅ አገረዶች እና በገላን የወንዶች መካከለኛና ሁለተኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በሚኒሊክ ሳይንስ ሼርድ ካንፓስ የ7ኛ እና የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት በኦን ላይን/online/ ምዝገባ ያከናወናችሁና የመግቢያ ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች በሙሉ ;- ውጤታችሁን https://bs.ministry.et ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ Beeksisa! Biiroon Barnootaa Bulchiinsa Magaalaa Finfinnee bara barnootaa 2019tti Mana Barnootaa Bultii addaa Sadarkaa Giddu-galeessaa fi Waliigalaa Sadarkaa 2ffaa Shamarranii Itegee Manan, Mana Barnootaa Bultii addaa Dhiiraa Galaan fi Kaampaasii Saayinsii Sheerdiitti barattoota kutaa 7ffaa fi 9ffaa simatee barsiisuuf beeksisa baase irratti hundaa'uun: Barattoonni onlaayiniidhaan (online) galmooftanii fi qormaata seensaa fudhattan hundi;- Bu'aa keessan marsariitii https://bs.ministry.et irratti ilaaluu kan dandeessan ta'uu ni beeksifna.
ውድ ወላጆች ነባርና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ነገ ቅዳሜ ሀምሌ 25/2018 ባንኮች ተገኝተው ሳትጉላሉ ምዝገባ የምናደርግ መሆኑን በገለፅነው መሰረት ልዩ ጊዜ ገደብ ከተሰጣችሁ በስተቀር ነገ ጧት ከ2:20 -7:00 የምናከናውን ይሆናል። ትምህርት ቤቱ!
WHY PARENTS SHOULD RESPECT THEIR CHILDREN'S TEACHERS 👉 Every parent dreams of seeing their child succeed in school and in life. But one of the greatest gifts a parent can give a child is teaching them to respect the people who educate them. 👉 Respecting teachers does not mean they are always right. 👉👉 Teachers are human and can make mistakes. However, disagreements should be handled with maturity, respect, and a shared desire to help the child—not in anger or in front of the learner. 👉 A teacher spends thousands of hours with your child every year. They do much more than teach Mathematics, English, or Science. They teach discipline, responsibility, teamwork, honesty, resilience, and respect for others. They encourage children when they are discouraged, comfort them when they are hurting, and celebrate their achievements. This is a responsibility that should never be taken lightly. 👉 When parents speak negatively about teachers in front of their children, several things can happen: 👉 The child starts believing that teachers do not deserve respect. 👉 The child becomes less willing to follow classroom rules. 👉 Discipline problems increase because the learner feels protected from any consequences. 👉 Learning suffers as the relationship between the teacher and the learner weakens. 👉 Other learners may also be affected by the disruptive behaviour. 👉 On the other hand, when parents support teachers: 👉 Children develop respect for authority. 🤣 Learners become more responsible for their actions. 👉 Communication between home and school improves. 👉 Problems are solved more quickly because both sides are working together. 👉 The child benefits from consistent guidance both at home and at school. 👉 Parents and teachers have different but equally important roles. Parents shape a child's character at home, while teachers build knowledge, skills, and values in school. Neither can succeed fully without the support of the other. 👉 If your child comes home complaining about a teacher, listen carefully. Show empathy, but also remember that every story has more than one side. Contact the teacher, seek clarification, and work together to find a solution. Most conflicts are resolved through respectful conversation, not confrontation. 👉 Children are always watching us. If they see adults treating teachers with dignity, they learn to value education, respect authority, and resolve disagreements peacefully. Those are life skills that will benefit them long after they leave school. 👉 A respectful parent-teacher partnership does not just build better learners—it builds better citizens. 👉 Let's remember: The child is not on the parent's side or the teacher's side. We are all on the child's side.
ውድ ወላጆች በዝርዝሩ ውስጥ በምታገኙት መረጃ በመጠቀም በመፈተኛ ጣቢያዎች እንድትገኙ።
ጥብቅ ማሳሰብያ ቀን 20/11/2018 ዓ/ም በ2019 ዓ/ም 1.ለእቴጌ መነን አዳሪ ት/ቤት 2.ለገላን አዳሪ ት/ቤት እና 3.ለሚኒሊክ/ ኮተቤ ሳይንስ ሼርድ/ ትምህርት ቤት ለመማር ያመለከቱ ተማሪዎች የመገረቢያ ፈተና የሚሰጠው በ22/11/2018 ዓ/ም እና 23/11/2018 ዓ/ም የመፈተኛ ጣቢያዎች ሲሆን ፤ እንደ ክፍለ ከተማ የፈተና መስጫ ጣቢያዎች 1. የካ አባዶ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 2. እድገት ጮራ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 3. ጋራ ጉሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እና 4. አንዶዴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በመሆናቸው ተቋማት በተያያዘው የስም ዝርዝር እና የመፈተኛ ቦታ መሰረት በተገለጸው የፈተና ቀን እና ቦታ ጠዋቱ 1፡30 ጀምሮ ግቢ ውስጥ በመገኘት ፈተናውን እንዲወስዱ ለተፈታኝ ተማሪዎች በእናንተ በኩል መልክቱን እንድታስተላልፉ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ ------ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት-------
без подписи
ጥብቅ ማሳሰብያ ቀን 20/11/2018 ዓ/ም በ2019 ዓ/ም 1.ለእቴጌ መነን አዳሪ ት/ቤት 2.ለገላን አዳሪ ት/ቤት እና 3.ለሚኒሊክ/ ኮተቤ ሳይንስ ሼርድ/ ትምህርት ቤት ለመማር ያመለከቱ ተማሪዎች የመገረቢያ ፈተና የሚሰጠው በ22/11/2018 ዓ/ም እና 23/11/2018 ዓ/ም የመፈተኛ ጣቢያዎች ሲሆን ፤ እንደ ክፍለ ከተማ የፈተና መስጫ ጣቢያዎች 1. የካ አባዶ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 2. እድገት ጮራ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 3. ጋራ ጉሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እና 4. አንዶዴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በመሆናቸው ተቋማት በተያያዘው የስም ዝርዝር እና የመፈተኛ ቦታ መሰረት በተገለጸው የፈተና ቀን እና ቦታ ጠዋቱ 1፡30 ጀምሮ ግቢ ውስጥ በመገኘት ፈተናውን እንዲወስዱ ለተፈታኝ ተማሪዎች በእናንተ በኩል መልክቱን እንድታስተላልፉ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ ------ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት-------
ጥብቅ ማሳሰብያ ቀን 20/11/2018 ዓ/ም 1.ለእቴጌ መነን አዳሪ ት/ቤት 2.ለገላን አዳሪ ት/ቤት እና 3.ለሚኒሊክ/ ኮተቤ ሳይንስ ሼርድ/ ትምህርት ቤት ለመማር ያመለከቱ ተማሪዎች የመገረቢያ ፈተና የሚሰጠው በ22/11/2018 ዓ/ም እና 23/11/2018 ዓ/ም የመፈተኛ ጣቢያዎች ሲሆን ፤ እንደ ክፍለ ከተማ የፈተና መስጫ ጣቢያዎች 1. የካ አባዶ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 2. እድገት ጮራ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 3. ጋራ ጉሪ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እና 4. አንዶዴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በመሆናቸው ተቋማት በተያያዘው የስም ዝርዝር እና የመፈተኛ ቦታ መሰረት በተገለጸው የፈተና ቀን እና ቦታ ጠዋቱ 1፡30 ጀምሮ ግቢ ውስጥ በመገኘት ፈተናውን እንዲወስዱ ለተፈታኝ ተማሪዎች በእናንተ በኩል መልክቱን እንድታስተላልፉ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ ------ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት-------
ውድ ወላጆች ለምዝገባ ጊዜ ከጠየቃችሁና ከተፈቀደላችሁ በስተቀር ምዝገባ ለነባርና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ይጠናቀቃል። ስለሆነም ዛሬ ባንኮች እዚያው እያሉ እስከ7:00 ምዝገባ በማጠናቀቅ እንዳትጉላሉ ማስታወስ እንወዳለን።
ውድ ተሳታፊዎች የአካባቢ ጥበቃ መድረክ በአድዋ ሙዚዬም ተዘጅቷል። በመድረኩ ማርይዞና ትምህርት ቤትን በመወከል የተመረጣችሁ ተማሪዎች ጧት 12:30 በማርይዞና ትምህርት ቤት ዩኒፎርም ለብሳችሁ እንድትገኙ። ከመምህራና አመራሮች ጋር በመሆን በተመደበው ሰርቪስ የምትጓዙ ይሆናል። ትምህርት ቤቱ
без подписи
ውድ ወላጆች ዛሬ የ2019/ምዝገባ ሲካሄድ ውሏል። ያልተመዘገባችሁ ነባርና አዲስ ተማሪዎች እስክ ቅዳሜ ሀምሌ 18/2018 ከቀኑ 7:00 ድረስ ብቻ እንዲመዘገቡ በድጋሚ እናስታውሳለን። ትምህርት ቤቱ
без подписи
ውድ ወላጆች የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ሀምሌ 1-10 ተከናውኖ እንደነበር እስከ ሀምሌ 15/2018 ተራዝሞም ዛሬ ተጠናቋል። በዚህ መሰረት ለአዲስ ተማሪ ከኬጂ እስከ 5ኛ ክፍል ብቻ ቦታ ያለን በመሆኑ እስከአሁን ያልተመዘገባችሁ ነባር ተማሪዎችና አዲስ ተመዝጋቢዎች እስከ ቅዳሜ ሀምሌ 18/2018 ግማሽ ቀን፣ ባንኮች እዚያው ተገኝተው መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። ትምህርት ቤቱ!
ይህ ፓስፖርት ስለተገኘ ባለቤቱ ማርይዞና ትምህርት ቤት መጥተው ይጠይቁ።
ኬጂ 3 የተቀበልናቸው ተማሪዎች 1.Melona Biniyam 2.Yafet Behailu 3. Barkot Cheramlak 4.Amen Misgana ኬጂ 2 የተቀበልናቸው ተማሪዎች 1.Sefen Assefa 2.Misgna Kendo 3.Hallelujah Gizaw