tgindex
@ArtsTvWorld - Arts TV - አርትስ ቲቪ

@ArtsTvWorld - Arts TV - አርትስ ቲቪ

Статистика
@ArtsTvWorldTelegramВидеоанглийский

Official Arts Tv World Channel Arts Tv frequency11512V / 27500 http://www.artstv.tv Facebook, Youtube, Instagram & Twitter @ArtsTvWorld

Последний пост
1 июл. 2025 г.
Последнее чтение
02:02
Постов за неделю
0
Всего постов
46
Тип
открытый
Язык
английский
Категория
Видео
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
2 589
−3 за 4 дн.
Сутки
0
0,00%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
2 380
40 постов
Вовлечённость
91,9%
к подписчикам
Постов в день
0,0
всего 46
Упоминаний
0
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
1/48двое суток
1/72трое суток

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • без подписи

  • 1 июл. 2025 г.3 390233из Arts_tv

    የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በ24/10/17 ባደረገው ስብሰባ ወላይታ ድቻ የ2017 የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ እንዲሆን ወሰነ ። የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ዛሬ ስብሰባ አድርጎ የተለያዩ ውሳኔዎችን ያስተላለፈ ሲሆን ከተደረጉት ውሳኔዎች መካከል በሲዳማ ቡና አሸናፊነት የተጠናቀቀው የኢትዮጵያ ዋንጫ አግባብነት የሌለው ተጫዋች በመሰለፉ ምክንያት ዋንጫው ለወላይታ ድቻ እንዲሰጥ እና ወላይታ ድቻ በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ ኢትዮጵያን ወክሎ እንዲሳተፍ ተወስኗል ። ከወራጅ ክለቦች ጋር በተያያዘ አዳማ ከተማ ፣ መቀሌ 70 እንደርታ ፣ ስሁል ሽረ እና ወልዋሎ አዲግራት በቀጣይ አመት በፕሪሚየር ሊጉ እንደሚሳተፉ ተረጋግጧል በተጨማሪም የቀጣይ አመት ፕሪሚየር ሊግ በ20 ክለቦች መካከል የሚደረግ ሲሆን አራት ክለቦች የሚወርዱ ይሆናል። ከውሳኔው በኃላ የተስተካከለ የደረጃ ሰንጠረዥ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር በአዲስ መልክ እንዲያሳውቅ ፌዴሬሽኑ ትዕዛዝ ተሰጥቷል ። የፌዴሬሽኑ ሙሉ ውሳኔዎች ከታች በምስሉ ተያይዘዋል ።

  • без подписи

  • без подписи

  • 1 июл. 2025 г.2 8606из Arts_tv

    ለዋንጫ የተገመቱት ማንችስተር ሲቲ እና ኢንተር ሚላን ተሰናበቱ ። ሁለቱ የ2023 የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ተፋላሚዎች ከውድድሩ ተሰናብተዋል ። በክለቦች ዓለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ የዘንድሮው የአውሮፓ ቻምፒየንስ የፍጻሜ ተፋላሚ የነበረው ኢንተር ሚላን በብራዚሉ ተወካይ ፍሎሜንሴ ተሸንፎ ከውድድሩ ውጭ ሆኗል፡፡ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በባንክ ኦፍ አሜሪካ ስቴዲየም በተደረገው ጨዋታ ፍሉሚነንስ 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ጀርማን ካኖስ እና ሄርኩለስ ናስሜንቶ የፍሉሚነንስን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡ ለሊት 10 ሰዓት ላይ በተጀመረው የማንችስተር ሲቲ እና አል ሂላል ጨዋታ በአል ሂላል አሸናፊነት 4 ለ 3 ተጠናቋል ። ጥሩ ፉክክር የታየበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በሁለት አቻ በመጠናቀቁ ጭማሪ 30 ደቂቃ የተጨመረ ሲሆን የሳውዲው አል ሂላል የፔፕ ጋርዲዮላን ማንቸስተር ሲቲ 4 ለ 2 በማሸነፍ ከውድድሩ አሰናብቶታል ። ለአል ሂላል ሊዮናርዶ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ማልኮም እና ኩሊባሊ ቀሪ ግቦችን ለሳውዲው ክለብ አስቆጥረዋል ። ሁለቱ የ2023 የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ተፋላሚዎች ወደ ሀገራቸው ሲሰናበቱ አል ሂላል እና ፍሎሜንሴ በሩብ ፍጻሜው የሚገናኙ ክለቦች ሆነዋል ። በዮናስ ግርማ

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи

  • 30 июн. 2025 г.2 18061из Arts_tv

    የአፍሪካ የጠበቆች ማህበራት ህብረት ፓሉ ምክር ቤት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያዊውን አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸውን የህብረቱ ፕሬዚደንት አድርጎ ሾሟል። ይህም ፕሬዚደንት ቴዎድሮስ ፓሉን በፕሬዚደንትነት እንዲመሩ የተመረጡ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ብቻም ሳይሆን የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካዊ ዜጋ ያደርጋቸዋል፡፡ 15ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአይቮሪ ኮስት አቢጃን እያከናወነ ያለው የአፍሪካ የጠበቆች ማህበራት ህብረት ፓሉ ምክር ቤት ባከናወነው ምርጫ ኢትዮጵያዊውን አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸውን የህብረቱ ፕሬዚደንት አድርጎ መርጧል። 54ቱን የአፍሪካ ሀገራት የጠበቆች ማህበራት እና 8 አካባቢያዊ ተቋማትን በአባልነት ይዞ የሚገኘው የአህጉራችን አፍሪካ ግዙፉና ቀዳሚው የህግ ተቋም የአፍሪካ የጠበቆች ህብረት በታሪኩ ለመጀመሪያ ግዜ ኢትዮጵያዊ የህግ ባለሙያ የሆኑትን አቶ ቴዎድሮስ ጌታቸውን አህጉራዊውን ተቋም በፕሬዚደንትነት እንዲመሩ በከፍተኛ ድምጽ መርጧል፡፡ በአይቮሪኮስት ዋና ከተማ አቢጃን እየተካሄደ ባለው በፕሬዚደንታዊ ምርጫው ከፕሬዚደንት ቴዎድሮስ ጋር ለመጨረሻ ዙር ምርጫ የደረሱት የቀድሞ የፓሉ የሰሜን አፍሪካ ምክትል ፕሬዚደንት አልጄሪያዊቷ ወ/ሮ አይሻ ቡዳይፍ የነበሩ ሲሆን በድምጽ አሰጣጡ ከ 1/3 አባል በሀገራትን ድምጽ በማግኘት ተሸንፈዋል፡፡ ፕሬዚደንት ቴዎድሮስ ድምጽ ከሰጡ የአፍሪካ ሀገራት የጠበቆች ማህበራት ውስጥ ከ3/4ኛ በላይ የሆነ ከፍተኛ ድምጽ አግኝተው በቀጣይ 3 አመታት አህጉራዊ ድርጅቱን እንዲመሩ ተመርጠዋል፡፡ ቴዎድሮስ የሚተኳቸው ላለፉት 3 አመታት ተቋሙን በፕሬዚደንትነት የመሩትን ካሜሮናዊው ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ሚ/ር ካሪ አብዱልባጎይን ይሆናል፡፡ ከፕሬዚደንታዊ ምርጫው በተጨማሪ ለሌሎች የስራ አስፈጻሚ ሀላፊነቶች በተደረገው ውድድር 5 ም/ፕሬዚደንቶች(ምስራቅ፤ ምእራብ፤ መሀከለኛው፤ ሰሜን እና ደቡብ አፍሪካ ክልሎችን /Regions/ የሚመሩ)፤ የድርጅቱ ዋና ጸሀፊ እና ሌሎች 9 የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን መርጧል፡፡

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи

  • без подписи