ኢስላማዊ ግጥም
Статистикаtelegram.me/abdul_fettah በአቡ ያሲር የተገጠሙ - የተለያዩ ኢስላማዊ ግጥሞች ወደ እናንተ የሚደርስበት ቻናል ነው"Join"አድርጋችሁ ተቀላቀሉኝ ማስተካከልን እንጂ ሌላን አልሻም !! @abdulfettahjemal
- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 4
- Всего постов
- 23
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 392
- 1/48двое суток
- 449
- 1/72трое суток
- 484
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ምርጫው የእናንተ ነው የተመቻቹን ንኩት👇👇👇
አታክብረው ይቅር (2) ከአባቱ በላይ አውቃለሁ ማለቱ ቡዳነት ነው አሉ ሰዎች ሲተርቱ ✍️አቡ ያሲር_አብዱል ፈታህ 👇👇👇👇 https://t.me/abdul_fettah https://t.me/abdul_fettah
አጠር ያለች ግጥም ስለ መውሊድ 🗞አታክብረው ይቅር..!!🗞 መውሊድ ቢድዓ ነው ሱና እኮ አይደለም በኢስላም ተልዕኮ አስ-ተምሮው የለም ✍️አቡ ያሲር_አብዱል ፈታህ 👇👇👇👇 https://t.me/abdul_fettah https://t.me/abdul_fettah
👂ቁርዓን የልብ ፈውስ ነው ። https://t.me/abdul_fettah
||በሚያስፈልግበት ቦታ ጥንካሬን (ሺዳን) መጠቀም አስፈላጊ ነው !! 🎙 ፈዲለቱ ሸይኽ : ዐብዱል ሐሚድ አል'ለተሚይ (ሐፊዘሏህ) ||ቴሌግራም ቻናል •━════✿🔰🔰✿════━• t.me/Bilal_Al_ghamassi t.me/Bilal_Al_ghamassi
https://t.me/abdul_fettah
በሕይወትህ ውስጥ አንዳንዴ በጨለማ የተዋጥከው የተቀበርክ መስሎህ ሊሆን ይችላል .. ነገር ግን አሏህ እንደ ዘር ዘርቶህ (ሊያበቅልህ) ሊሆን እንደሚችል አትርሳ .!! ✍️#bilal gallery https://t.me/abdul_fettah
🎤 ═ ❁ ታላቅ የዳዕዋ ጥሪ ❁ ═ 📢 ✅ ውድና የተከበራችሁ የሱናህ ቤተሰቦቻችን ዕለተ ሰኞ 20/11/2018 ለኢሎስ ከተማ እና አከባቢዋ እንዲሁም በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጪም ለምትገኙ ሙስሊሞች በሙሉ በፉርቃን መድረሳ በአይነቱ ለየት ያለ የዳዕዋ ፕሮግራም ማዘጋጀታችንን ስናበስራችሁ በታላቅ ደስታ ነው። 🪑የእለቱ ተጋባዥ እንግዶቻችን፦ ➴➷➘➴➴➴➴➴➴➴ ➊ኛ╰┈➢ ሸይኽ አብዱልሀሚድ ቢን ያሲን አል-ለተሚይ (ሐፊዘሁላህ) ❷ኛ╰┈➢ ሸይኽ መህቡብ ከሳንኩራ (ሐፊዘሁላህ) ❸ኛ╰┈➢ ሸይኽ ሰይፉላህ ከምስራቅ ስልጢ (ሐፊዘሁላህ) ❹ኛ╰┈➢ ሸይኽ ዘይኑ ከመናከሪያ (ሐፊዘሁላህ) ❺ኛ╰┈➢ ኡስታዝ አቡ ኑዕማን (ሐፊዘሁላህ) ❻ኛ╰┈➢ ኡስታዝ ስራጅ ከወራቤ (ሐፊዘሁላህ) ╰┈➢ ኢንሻ አላህ ሌሎችም ተጋባዥ እንግዶች ይኖራሉ። ◉አድራሻ➟“ስልጤ ዞን፣ ስልጢ ወረዳ፣ ╰┈➢➢[~ኢሎስ 01 ቀበሌ] 🗓 የፕሮግራሙ ፦ዕለተ ሰኞ ሐምሌ 20/ 11/ 2018 ⌚️ሰዓት፡- ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ⚙️ የፕሮግራሙ አዘጋጅ፦ መድረሰቱል ፉርቃን 🔎እውቀት ከንግግርም ከተግባርም ይቀድማ !!ል!!!!! 🔍 🔎ቤተሰቦቻችንን ከባዕድ አምልኮና ከተለያዩ ሸሪዓዊ ጥሰቶች እንታደግ !!! 🔍 ማሳሰቢያ፡- 1. ይህ በአይነቱ ለየት ያለ የዳዕዋ ፕሮግራም አዘጋጅተን የእርሶ መምጣትን በጉጉት እንጠብቃለን። 2. ለሴቶችም በቂ ቦታ ተዘጋጅቷል። 🔔 ሼር በማድረግ ሓላፊነታችንን እንወጣ ባረከሏሁ ፊኩም !!! 👉⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️ https://t.me/KHALID_ASELEFY
🚨በጽሑፎቻችን ውበት አትታለሉ🚨 ኢማም አሕመድ እንዲህ አሉ፦ እኛ ምስኪን ሕዝቦች ነን፤ አላህ ደካማነታችንንና ስህተታችንን መደበቁ ባይኖር ኖሮ በተዋረድን ነበር። ✍አቡ ያሲር_አብዱልፈታህ 👇👇 https://t.me/abdul_fettah https://t.me/abdul_fettah
🚫 የሰው ልጅ አመጣጥ ከዝንጆሮ ነውን ⁉️ የሰው ልጅ ካልነበረበት ያስገኘውን አምላክ ክዶ በስሜት ፈረስ ሲጋልብ በኩፍር ማዕበል ሲናወጥና ግራ የመጋባት አውሎ ንፋስ ከተለያዩ የሀሳብ ቋጥኞች ጋር ሲያላትመው በደመ ነፍስ የመጣለትን ሀሳብ እምነቱ አድርጎ ሌሎችን በዚሁ የደመ ነፍስ ሀሳብ መርከብ አሳፍሮ እየነዳ ወደ ኩፍር አዘቅት ይነጉዳል ። ከእነዚህ ኢአማንያን የክህደት መርከብ ሹፌሮች አንዱ የሆነው እንግሊዛዊው ቻርልስ ዳርዊን የሰው ልጅ አመጣጥ ከዝንጆሮ ነው ይላል !!! ። ይህ ቅዠት እሱ ላይ በቆመ ኖሮ መልካም ነበር ። በጣም የሚገርመው እንዲህ አይነቱን የቁሳዊያን አምላክ የለም ባይ ምእራባዊያን አስተምሮ ዛሬ ሙስሊም ተብዬ መምህራን ጭምር በየትምህርት ቤቱ የሙስሊም ልጆችን ሲግቱ እያየንና እየሰማን ነው ። የዚህ አይነቱን አስተምሮ ኢስላም ፈፅሞ የማይቀበለው ከመሆኑም በላይ ባለቤቱንም በክህደት ማማ ጫፍ ላይ ነው የሚያስቀምጠው ። አንዳንድ ምስኪን ሙስሊሞች አላህ በቅዳሜ ቀን አሳ በማጥመድ ወሰን ያለፉትን እስራኤላዊያን ወደ ዝንጆሮነት መቀየሩን የተናገረበትን የሚቀጥለውን አንቀፅ ለዚህ መረጃ እየመሰላቸው ሌሎችን ሊያሳምኑበት ሲሞክሩ ይስተዋላል ። መጀመሪያ አንቀፁን እንመልከት :– { وَلَقَدْ عَلِمْتُمُ الَّذِينَ اعْتَدَوْا مِنكُمْ فِي السَّبْتِ فَقُلْنَا لَهُمْ كُونُوا قِرَدَةً خَاسِئِينَ } البقرة ( 65 ) " እነዚያንም ከእናንተ ውስጥ በቅዳሜ ቀን (ዐሣን በማጥመድ) ወሰን ያለፉትንና ለነሱ «ወራዳዎች ስትኾኑ ዝንጀሮዎች ኹኑ» ያልናቸውን በእርግጥ ዐወቃችሁ "፡፡ የዚህንና ከዚህ ጋር ተመሳሳይነት ስላላቸው አንቀፆች ሶሓባዎች የአላህ መልእክተኛን – ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም – ጠይቀው የሚከተለውን መልስ ሰጥተውዋቸዋል ። عن عبد الله بن مسعود – رضي الله عنه – قال : قيل لرسول الله – صلى الله عليه وسلم -: «القردة والخنازير: هي مما مسخ ؟ فقال رسول الله – صلى الله عليه وسلم -: " إن الله لم يهلك قوما أو يعذب قوما فيجعل لهم نسلا، وإن القردة والخنازير كانت قبل ذلك». أخرجه الإمام مسلم ከርከሮና ዝንጆሮ አላህ ካጠፋቸው የሰው ዝሪያዎች ናቸውን ? ተብለው ተጠየቁ እሳቸውም እንዲህ ብለው መለሱ :– " አላህ ህዝቦችን አጥፍቶ ወይም ቀጥቶ ዝርያ አያደርግለትም ። ከርከሮና ዝንጆሮ ከዛ በፊትም ነበሩ " የቁርኣኑ አንቀፅ የሚያስረዳን አላህ የተቆጣባቸው ሰዎች ወደ ዝንጆሮ መቀየራቸውን እንጂ ዝንጆሮ ወደ ሰው መቀየሩን አይደለም ። ሐዲሱም ላይ የተጠየቀው የዛን ጊዜ ስለነበሩ ዝንጆሮዎች ዝርያቸው ከተቀየሩት ሰዎች ነው ወይ የሚል ነው ። መልሱ ደግሞ አይደለም ዝንጆሮና ከርከሮ ከዛ በፊትም ነበሩ የሚል ነው ። ሰውም ከዝንጆሮ አይደለም ዝንጆሮም ከሰው አይደለም የተገኘው ሁሉም የራሱ ዝርያ አለው ይህን አስመልክቶ አላህ እንዲህ ይለናል : – { وَمَا مِن دَابَّةٍ فِي الْأَرْضِ وَلَا طَائِرٍ يَطِيرُ بِجَنَاحَيْهِ إِلَّا أُمَمٌ أَمْثَالُكُم ۚ مَّا فَرَّطْنَا فِي الْكِتَابِ مِن شَيْءٍ ۚ ثُمَّ إِلَىٰ رَبِّهِمْ يُحْشَرُونَ } الأنعام ( 38 ) " ከተንቀሳቃሽም በምድር (የሚኼድ) ፤ በሁለት ክንፎቹ የሚበርም በራሪ መሰሎቻችሁ ሕዝቦች እንጅ ሌላ አይደሉም ፡፡ በመጽሐፉ ውስጥ ምንንም ነገር አልተውንም ከዚያም ወደ ጌታቸው ይሰበሰባሉ " ፡፡ የሰው ዘር መነሻውም ከአፈር ነው መጨረሻውም አፈር ነው ። ይህን አስመልክቶ አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይለናል : – { مِنْهَا خَلَقْنَاكُمْ وَفِيهَا نُعِيدُكُمْ وَمِنْهَا نُخْرِجُكُمْ تَارَةً أُخْرَىٰ } طه ( 55) " ከእርሷ (ከምድር) ፈጠርናችሁ ፡፡ በእርሷም ውስጥ እንመልሳችኋለን ፡፡ ከእርሷም በሌላ ጊዜ እናወጣችኋለን "፡፡ የሰው ዘር መገኛ የሆነውን አባታችን አደምን ከምን እንደ ፈጠረው ከሚቀጥለው ቃሉ እንመልከት : – { وَلَقَدْ خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن سُلَالَةٍ مِّن طِينٍ } المؤمنون ( 12) " በእርግጥም ሰውን ከነጠረ ጭቃ ፈጠርነው" ፡፡ የተቀሩትን የሰው ልጆች ደግሞ ተገፈታትሮ ከሚወጣ የፍትወት ጠብታ የፈጠረው መሆኑን እንዲያስተነትኑ እንዲህ ብሎ ይጋብዛል : – { فَلْيَنظُرِ الْإِنسَانُ مِمَّ خُلِقَ } ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት ፡ { خُلِقَ مِن مَّاءٍ دَافِقٍ } ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ ፡፡ { يَخْرُجُ مِن بَيْنِ الصُّلْبِ وَالتَّرَائِبِ} الطارق ( 7–9 ) ከጀርባና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከኾነ (ውሃ) ፡፡ ይህ ነው የሙስሊሞች ዐቂዳ በሰው ልጅ አፈጣጠር ከዚህ ውጪ ያለ ፍልስፍና ውድቅ ከመሆኑም ሌላ መረጃ ከደረሰው በኋላ አምኖ የተቀበለው ከእስልምና መውጣቱ የተረጋገጠ ነው ። አላህ ሐቅን አውቆ ከሚከተሉትና ባጢልን አውቀው ከሚርቁት ያድረገን ። https://t.me/bahruteka
ኢስላማዊ ግጥም pinned «🫵ዱኒያን ተጠንቀቁ 🔴 قالَ الإِمامُ ابْنُ الجَوْزِي رَحِمَهُ اللهُ: احْذَرُوا الدُّنْيَا فَإِنَّهَا أَسْحَرُ مِنْ هَارُوتَ وَمَارُوتَ፤ ذَانِكَ يُفَرِّقَانِ بَيْنَ المَرْءِ وَزَوْجِهِ وَهَذِهِ تُفَرِّقُ بَيْنَ العَبْدِ وَرَبِّهِ . المُدْهِش ٣٨٦ ኢማም ኢብኑል ጃውዚ (ረሒመሁላህ)…»
🫵ዱኒያን ተጠንቀቁ 🔴 قالَ الإِمامُ ابْنُ الجَوْزِي رَحِمَهُ اللهُ: احْذَرُوا الدُّنْيَا فَإِنَّهَا أَسْحَرُ مِنْ هَارُوتَ وَمَارُوتَ፤ ذَانِكَ يُفَرِّقَانِ بَيْنَ المَرْءِ وَزَوْجِهِ وَهَذِهِ تُفَرِّقُ بَيْنَ العَبْدِ وَرَبِّهِ . المُدْهِش ٣٨٦ ኢማም ኢብኑል ጃውዚ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ብለዋል፦ "ዱንያን ተጠንቀቁ! ምክንያቱም ከሃሩትና ማሩት ይልቅ የበለጠ አሳሳች ናት። እነርሱ በአላህ ፍቃድ በሰውና በሚስቱ መካከል መለያየትን ያመጣሉ፤ ዱንያ ግን በባሪያውና በጌታው (በአላህ) መካከል መለያየትን ታመጣለች።" 📚 አል-ሙድሂሽ (ገጽ 386) ✍አቡ ያሲር_አብዱልፈታህ 👇👇 https://t.me/abdul_fettah https://t.me/abdul_fettah
👆 እህት ላላችሁ ወንድሞች ሁሉ ..!! t.me/abdul_fettah t.me/abdul_fettah
"ነፍስም ሁሉ አብሯት ነጂና ምስክር ያለባት ሆና ትመጣለች።" አቡ ሑረይራ እንዳለው ወደ መህሸር ነጂው ፦ መላእክት ሲሆኑ ምስክሩ ደግሞ ፦ ሥራው ይሆናል 📘ተፍሲር ኢብን ከሲር ✍አቡ ያሲር_አብዱልፈታህ 👇👇 t.me/abdul_fettah t.me/abdul_fettah
без подписи
⏲የተምዪዕ አፈሳ ⏲ ▻ አዲስ ግጥም ◅ እስኪ ከጅማሮው በኢትዮ ሀገር የተምዪዕ አፈሳ ወገቡን አጥብቆ ከአመታት በፊት ሱናን ሲያሳሳ በአጭር ስንኞች እስኪ እንዘክር ታሪኩን እናውሳ በኢልያስ አህመድ በጀነራላቸው አዋጁ ተሰጠ በሠላሳው ከይድ የማስተኛው መርፊ እራሱን ገለጠ ኢኽዋን ፈነጠዘ ሚሆነው አሳጣው በደስታ ተናጠ በሚሞሪው ጭኖ ለሀገር አዳረሰው እየተሯሯጠ መፍረክረክ ጀመረ አብዘሃኛው ሱኒይ ልቡ…
🤲ወደ እሱ ተጠጋ🤲 እገዛ አስፈልጎህ እጅህ ስትዘረጋ ተስፋ የጣልክበት በር ሁሉ ቢዘጋ አንዱ ግን ክፍት ነው እንዳትዘናጋ በጥዋትም በማታ ወደእሱ ተጠጋ ✍️አቡ ያሲር አብዱልፈታህ https://t.me/abdul_fettah https://t.me/abdul_fettah
без подписи
.قال الشيخ صالح الفوزان حفظه اللّٰـه ؛ الذِّي لا يُحذِّر من دُعاة الضلال يُعتبر من الكاتمين للعِلم .◂ شرح إغاثة اللَّهفان | ሸይኽ ሷሊህ አልፈውዛን እንዲህ አሉ ወደ ስህተት የሚጠሩ የጥመት ሰዎችን ማሕበረሰቡ እንዲጠነቀቅ የማያስጠነቅቅ ሰው፣ እውቀቱን ከሚደብቁ ሰዎች መካከል ይቆጠራል። ✍️አቡ ያሲር አብዱልፈታህ https://t.me/abdul_fettah
↪️ኢስላማዊ ግጥም↩️ 🔑መድረሳ ይሂድ ልጅህ ቁርዓን ይቅራ 🔑እሱ በመቅራቱ ሰበብ አንተ በአኼራ 🔑ትልቅ አጅር አለህ አባት ሆይ አደራ ⏺ቁርዓን ከልተማረ መድረሳ ካልገባ ⏺ልጅህ ዋጋ ቢስ ነው ሆኖዋል ገለባ ⏺ቁርዓን ከቀራ ግን በቀን በለሊት ⏺ና ስማኝ አባቴ _^^_የቂያማ ለት ⏺ተዘጋጅቶልሃል ^ ትልቅ ሽልማት 🫵የወለድከው ልጅህ ሸሪዓ ይማር 🫵ኡማውን አገልጋይ ሊሆንልህ ጣር 📝የሰው ልጅ ሲሞት ስራው ይቋረጣል 📝የሶስት አይነት ሰዎች ሲቀር ተብሏል ✋ልጅህ ያንብብ ይማር ተውሂድን ይወቅ ✋ስራ አውዳሚውን ሽርክን ይጠንቀቅ 👌ሲኖር በአዱንያ ቁርዓንን የቀራ 👌በአኼራ ይሆናል ከመላኢኮች ጋራ 📂አደራ ውዶቼ ቁርዓንን አንብቡ 📂የቂያማ እለት ጀነት እንድትገቡ ⏺ቁርዓን መድሃኒት ነው ለሁሉም በሽታ ⏺ወንድሜ አንብበው በጥዋትም በማታ ☣አብዱል ፈታህ☣ ⏬ጆይን⏬ t.me/abdul_fettah t.me/abdul_fettah