tgindex
Последний пост
11 июн.
Последнее чтение
15 авг.
Постов за неделю
0
Всего постов
23
Тип
открытый
Язык
und
Категория
Новости и СМИ (по похожим)
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
12 698
+3 за 4 дн.
Сутки
+4
+0,03%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
11,6 тыс
23 постов
Вовлечённость
91,0%
к подписчикам
Постов в день
0,0
всего 23
Упоминаний
0
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
1/48двое суток
1/72трое суток

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • 11 июн.4 7402116

    የመጽሐፍ ማየስ / Book Review ርዕስ: የአእምሯዊ ንብረት ሕግ ደራሲ: ዳዊት በዛብህ ገምጋሚ: ካሴ መልካም ይህ ግምገማ የዳዊት በዛብህን 281 ገፅ ያለውን “የአእምሯዊ ንብረት ሕግ” መፅሐፍ ያስተዋውቃል። መፅሐፉ የፈጠራ፣ የቅጂ መብት፣ የንግድ ምልክት፣ የንግድ ሚስጥር፣ AI እና ዓለም አቀፍ የአእምሯዊ ንብረት ክርክሮችን ከኢትዮጵያ ሕግ ጋር በማያያዝ የሚዳስስ የሕግ ሙያ መፅሐፍ ነው። 🔗 ሙሉውን ያንብቡ፦ https://abyssinialaw.com/blog/intellectual-property-book-review-by-kassie-melkam

  • 12 февр.10,2 тыс4233

    Can Courts Invoke an Arbitration Agreement on their Own Motion? A Case Comment on Dashen Bank S.C vs. Richel Tesfaye Trading PLC (158634/2018) By: Giday Belay Assefa Ethiopia’s Federal Supreme Court Cassation Division released its latest volume of decisions (28) recently. One of the compiled decisions concerns whether a court may decline jurisdiction on the basis of an arbitration agreement even when the defendant has not invoked the arbitration agreement to object to the jurisdiction of the court. While the court, in accordance with the repealed provisions of the Civil Code and Civil Procedure Code, decided that the courts may invoke arbitration clause on their own motion, the reasoning and outcome would likely differ under the new law i.e. the Arbitration and Conciliation Working Procedure Proclamation No. 1237/2021 (Arbitration Proclamation). Because the case has been published and released recently, it may create the impression that this is the current state of arbitration law of Ethiopia. This piece looks at the case in light of the provisions of the Arbitration proclamation in order to inform practitioners that it is not applicable for cases governed by the 2021 Arbitration Proclamation. https://www.abyssinialaw.com/blog/can-courts-invoke-an-arbitration-agreement-on-their-own-motion-a-case-comment-on-dashen-bank-s-c-vs-richel-tesfaye-trading-plc-158634-2018

  • 13 дек.12,2 тыс2620

    без подписи

  • 1 дек.13,3 тыс312

    የዘንድሮ የፌዴራል ጠበቆች ፕሬዝዳንት እና ሥራ አስፈጻሚ ምርጫ ቅስቀሳን እንዴት ተመለከቱት? በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ የሆነ ሪፖርት የሚፈልጉ ከሆነ ያሳውቁን፤

  • 15 нояб.16,3 тыс3266

    We have corrected some of the bugs in the negari application. We are working to include the latest laws and cassation decisions. Currently we have updated the court calculation fee based on the Federal Supreme Court Calculation. Uninstall and install the apk again.

  • 27 окт.16,7 тыс2851

    ማስታወቂያ

  • 13 окт. 2025 г.15,7 тыс2332

    በግልግል ዳኝነት የፍርድ ቤቶች ሚና ጸሐፊ፡ ፍቃዱ አንዳርጌ መኮንን (ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ) ይህ ጽሑፍ፣ ከፍርድ ቤት ውጪ በግልግል ዳኝነት በሚፈቱ አለመግባባቶች ውስጥ መደበኛ ፍርድ ቤቶች ያላቸውን ወሳኝ ሚና ይተነትናል። የግልግል ዳኝነት ራሱን የቻለ ሥርዓት ቢሆንም፣ የግልግል ጉባዔን በማቋቋም፣ ጊዜያዊ ትዕዛዞችን በመስጠት፣ በማስረጃ አሰባሰብ ላይ ድጋፍ በማድረግ፣ እንዲሁም በግልግል የተሰጡ ውሳኔዎችን በማስፈጸምና በይግባኝ በመመርመር ረገድ የፍርድ ቤቶች ድጋፍ የግድ አስፈላጊ መሆኑን ጽሑፉ በዝርዝር ያስረዳል። https://www.abyssinialaw.com/blog/the-role-of-courts-in-arbitration

  • 7 окт. 2025 г.14,6 тыс515

    ሶስቱም መመሪያዎች ፀድቀዋል የአባላት መዋጮ ሶስት ሺ ብር ሆኖ ተወስኗል የጠቅላላ ጉባኤ መልአተ ጉባኤ 15 ፐርሰንት ሆኖ ተወስኗል

  • 7 окт. 2025 г.15,6 тыс5

    без подписи

  • 7 окт. 2025 г.16,3 тыс5

    без подписи

  • 7 окт. 2025 г.13,3 тыс7

    без подписи

  • 7 окт. 2025 г.12,2 тыс5

    без подписи

  • 7 окт. 2025 г.15,6 тыс25

    без подписи

  • без подписи

  • 7 окт. 2025 г.10,6 тыс54

    ረቂቅ መተዳደሪያ ደንቦች እና መመሪያዎች ማጠቃለያ እነዚህ ሰነዶች በ2ኛው ጠቅላላ ጉባኤ በተመደቡት አስራ ሦስት ኮሚቴ አባላት የተዘጋጁ ረቂቆች ሲሆኑ፣ ማኅበሩ በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 የተሰጡትን ሥልጣንና ተግባራት የሚመራበትን ሥርዓት ለመዘርጋት የቀረቡ ናቸው። 1. የኢፌጠማ ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ * አቅራቢ: ደጀኔ ግርማ (ዶ/ር) ዋና ዋና ድንጋጌዎች * ተፈጻሚነት: የጥብቅና ፈቃድ በተሰጣቸው…

  • 7 окт. 2025 г.11,7 тыс2211

    ረቂቅ መተዳደሪያ ደንቦች እና መመሪያዎች ማጠቃለያ እነዚህ ሰነዶች በ2ኛው ጠቅላላ ጉባኤ በተመደቡት አስራ ሦስት ኮሚቴ አባላት የተዘጋጁ ረቂቆች ሲሆኑ፣ ማኅበሩ በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 የተሰጡትን ሥልጣንና ተግባራት የሚመራበትን ሥርዓት ለመዘርጋት የቀረቡ ናቸው። 1. የኢፌጠማ ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ * አቅራቢ: ደጀኔ ግርማ (ዶ/ር) ዋና ዋና ድንጋጌዎች * ተፈጻሚነት: የጥብቅና ፈቃድ በተሰጣቸው የፌዴራል ጠበቆችና የጥብቅና አገልግሎት ድርጅቶች ላይ ተፈጻሚ ይሆናል። * ዓላማ: የሕግ የበላይነት እንዲረጋገጥ፣ ለዜጎች ነፃ የሕግ አገልግሎት እንዲመቻች፣ የጥብቅና ሙያን ደረጃና ሥነ-ምግባር እንዲጎለብት መስራት ነው። * የአባልነት አስገዳጅነት: የፌዴራል የጥብቅና ፈቃድ ያለው ጠበቃ ወይም ድርጅት በአስገዳጅነት የማኅበሩ መደበኛ አባል ይሆናል። * አመራር እና ሥልጣን: ማኅበሩ ጠቅላላ ጉባኤ (ከፍተኛ አካል)፣ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ (7 አባላት ያሉት)፣ ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንትና ዋና ጸሐፊ ይኖሩታል። የሥራ ዘመናቸው 3 (ሦስት) ዓመት ሲሆን፣ አንድ ጊዜ በድጋሚ ሊመረጡ ይችላሉ። * ቋሚ ኮሚቴዎች: በአዋጁ መሠረት ሥልጣን የሚረከቡትን 3 ኮሚቴዎች ጨምሮ በድምሩ 12 ቋሚ ኮሚቴዎች እንደሚኖሩት ተቀምጧል። 2. ረቂቅ ተከታታይ የሕግ ሥልጠና መመሪያ * አቅራቢ: ሕይወት ብርሃኑ ዋና ዋና ድንጋጌዎች * የሥልጠና ግዴታ: ማንኛውም ጠበቃ በአንድ የሥልጠና ዓመት ውስጥ ቢያንስ ለ24 (ሃያ አራት) ሰዓት ሥልጠና መውሰድ አለበት። * የሥልጠና ዘርፎች: የሚሰጠው ስልጠና ከሙያ ሥነ-ምግባር፣ የግጭት መፍቻ መንገዶች፣ የሙግት ክህሎት፣ ዓለም አቀፍ ሕግ፣ የግብር ሕጎች እና ሌሎች ተዛማጅ ዘርፎች ጋር ተያያዥነት ሊኖረው ይችላል። * የዕውቅና ሥርዓት: ማንኛውም ተቋም ሥልጠና ለመስጠት ከማኅበሩ ዕውቅና ማግኘት አለበት፤ ይህ ዕውቅና ለሶስት (3) ዓመት የፀና ይሆናል። * ግምገማው በሕግ ትምህርት፣ ምርምርና ስልጠና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ይከናወናል። * የሥልጠና ክፍያ: ክፍያው የሚወሰነው በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሕግ ት/ቤቶች በድህረ-ምርቃ ፕሮግራም ለአንድ ኮርስ በሚከፈለው ክፍያ መሠረት ነው። * ሥልጠናን ማቋረጥ: ከአስገዳጅ ምክንያት ውጪ ሥልጠናውን ካለበት ሰዓት ከሶስት አራተኛ በታች ወስዶ ያቋረጠ ሰልጣኝ የከፈለው ክፍያ አይመለስለትም፣ እና ድጋሚ ሲመደብ ሙሉ ክፍያ ከፍሎ መውሰድ ይኖርበታል። 3. ረቂቅ የአባላት መዋጮ መመሪያ * አቅራቢ: ፋሲል ስለሺ ዋና ዋና ድንጋጌዎች * ተፈጻሚነት: በአዋጁ መሠረት ፈቃድ በተሰጣቸው ጠበቆች እና የጥብቅና አገልግሎት ድርጅቶች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል። * የመዋጮ መጠን: የማኅበሩ መደበኛ አባል በአመት የሚከፍለው የመዋጮ መጠን ብር 5000 ነው። * አከፋፈል: መዋጮው በአንድ ጊዜ ፈቃድ በሚታደስበት ወቅት የሚፈፀም ይሆናል። * የጥብቅና ድርጅት: የጥብቅና አገልግሎት ድርጅት እንደ አንድ መደበኛ አባል የአባልነት መዋጮ ይከፍላል። በድርጅቱ ውስጥ የሚሰሩ ጠበቆች የአባልነት መዋጮ የመክፈል ግዴታን አያስቀርም። * የግዴታ አለመወጣት ውጤት: የመደበኛ መዋጮ ግዴታውን ያልተወጣ አባል ከማኅበሩ ምንም ዓይነት አገልግሎት አያገኝም።

  • без подписи

  • የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር (ኢፌጠማ) የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ይህ ከግንቦት 2016 ዓ.ም እስከ መስከረም 2018 ዓ.ም ድረስ የተከናወነው የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ማጠቃለያ ለ3ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ያልተገኙ አባላትና ባለድርሻ አካላት መረጃ እንዲያገኙ ለማሳወቅ ብቻ የቀረበ ነው። ጠቃሚ ማስታወሻ ይህ ሪፖርት የሚቀርበው ለመዘገብ (ለሪፖርት አላማ) ብቻ ሲሆን፣ በምንም መልኩ ቢሆን በAbyssinia Law እንደ ድጋፍ ወይም እንደ ይሁንታ (endorsement) ተደርጎ ሊወሰድ አይገባም። ዋና ዋና ተግባራት አፈጻጸም ማጠቃለያ 1. ተቋማዊ ግንባታ እና የህግ ማዕቀፍ ማዘጋጀት * ከ2ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ በኋላ በሦስት አመራሮች መልቀቅ ምክንያት በተጓደለ አመራር ውስጥ በርካታ ጠንካራ ስራዎች እንደተከናወኑ ተገልጿል። * የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ፣ የክፍያ መመሪያ፣ የስልጠና መመሪያ እና ክለሳን የሚመለከቱ ደንቦችና መመሪያዎች በ2ኛው መደበኛ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት መዘጋጀታቸው ተመልክቷል። * በአዋጅ ቁጥር 1249/13 የተቋቋሙት የሶስቱ ዋና ዋና ኮሚቴዎች (የጠበቆች ዲሲፕሊን ኮሚቴ፣ የጥብቅና ሙያ መግቢያ ፈተና ኮሚቴ እና የፈቃድ ገምጋሚ ኮሚቴ) ረቂቅ የአሰራር መመሪያዎች፣ የሰራተኞች አስተዳደር ማኑዋል እና የፋይናንስ ረቂቅ መመሪያ የማዘጋጀት ስራዎች እንደተከናወኑ ሪፖርት ተደርጓል። 2. የአባላት ምዝገባ እና የመረጃ አደረጃጀት * በመላው ኢትዮጵያ ከሚገኙ ከ7,000 በላይ አባላት ውስጥ የ5,200 የፌደራል ጠበቆችና የህግ አማካሪዎች የተሟላ መረጃ በጥራት እንደተደራጀ ተጠቅሷል። * የቴክኖሎጂ ድጋፍ ያለው የስራ መታወቂያ እንዲኖራቸው መደረጉ ታውቋል። * በበጀት ዓመቱ አዲስ የጥብቅና ፈቃድ ላወጡ 461 ጠበቆች የአባልነት ምዝገባ የተደረገ ሲሆን፣ እስከ አሁን ድረስ በአጠቃላይ 3,390 የታተመ መታወቂያዎች ለአባላት እንደተሰጠ ተመልክቷል። 3. የኮሚቴዎች የስራ አፈጻጸም * የዲሲፕሊን ጉባኤን በተመለከተ በበጀት ዓመቱ 339 የዲሲፕሊን ክሶች ቀርበው 299 ውሳኔ ያገኙ ሲሆን፣ ከነዚህ ውስጥ 246ቱ ጥፋተኛ የተባሉ መሆናቸው ተመዝግቧል። * የፈተና ኮሚቴን በተመለከተ ጥራት ያለው ፈተና በመስጠት በድምሩ 92 ለሚሆኑ ጠበቆች ፈተናውን አልፈው ፍቃድ ወስደዋል። * የፍቃድ ገምጋሚ ኮሚቴን በተመለከተ ለ716 የፌደራል ጠበቆችና የህግ አማካሪዎች ፍቃድ መስጠቱ ተመልክቷል። * የፈቃድ እድሳትን በተመለከተ ማረጋገጫ ለሰጠባቸው 4,820 የፌደራል ጠበቆችና የጥብቅና ድርጅቶች የእድሳት አገልግሎት እንደተሰጠ ተዘግቧል። 4. የህግ አወጣጥ ሂደቶች ላይ የተደረገ ተሳትፎ * ማህበሩ በኢሚግሬሽንና ዜግነት አዋጅ፣ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብን ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብን ለመከላከል ረቂቅ አዋጅ፣ በውጭ ዜጎች የቋሚ ንብረት ባለቤትነት ረቂቅ አዋጅ እና በፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ ማሻሻያ ላይ ጠንካራ ትችቶችንና አማራጭ ሀሳቦችን በማቅረብ ተገቢውን ሚና እንደተወጣ ተመልክቷል። * በኢሚግሬሽንና ዜግነት አዋጅ ላይ ያቀረባቸው አማራጭ የረቂቁ ማሻሻያ ሀሳቦች በአብዛኛው ተቀባይነት እንዳገኙ ታውቋል። * በፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ክፍያ እና ውሳኔ አሰጣጥ ረቂቅ መመሪያዎች ላይ፣ እንዲሁም በፌደራል ጠበቆችና የጥብቅና ድርጅቶች የሥነ ምግባር ጥሰት ክስ አቀራረብ ረቂቅ መመሪያ ላይ ገንቢ አስተያየቶች እንደተሰጡ ተመዝግቧል። 5. የጠበቆች የታክስ አስተዳደር ስርአት * በተለይም በታክስ አስተዳደር ስርአቱ ላይ የሚታዩ መሰረታዊ ጉድለቶችን በግልጽ ማሳየት የቻለው ጥናት ጉልህ ተጽእኖ ማሳደር የቻለ መሆኑ ተጠቅሷል። * ከፍትህ ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር እና ከአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ጋር በመግባባት ለጠበቆች ልዩ መመሪያ እንደሚያስፈልግ ውሳኔ ላይ እንደተደረሰ ተመዝግቧል። * አዲስ በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ ላይ ለጠበቆችና የጥብቅና ድርጅቶች ልዩ መመሪያ የሚወጣበት አንቀጽ የህጉ አካል እንዲሆን መደረጉ ተዘግቧል። 6. አለም አቀፍ ትብብሮች * 14ኛውን የአፍሪካ ጠበቆች ማህበራት ህብረት (PALU) መደበኛ ጉባኤን በአዲስ አበባ በስኬት በማስተናገድ ትልቅ ታሪክ እንደተመዘገበ ተጠቅሷል። * በኡጋንዳ (ካምፓላ) በተካሄደው በ29ኛው የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ መደበኛ ጉባኤ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር በይፋ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የህግ ማህበረሰብን (EALS) በአባልነት እንደተቀላቀለ ተዘግቧል። * በቅርቡ ህዳር ወር ላይ የሚካሄደውን 30ኛውን የEALS ጉባኤን በአዲስ አበባ ከተማ ለማስተናገድ እድሉን መውሰዱ ታውቋል። 7. ነፃ የህግ አገልግሎት እና ሌሎች ማህበራዊ ተግባራት * ለ17,262 ለሚደርሱ ዜጎች ነጻ የህግ አገልግሎት ተሰጥቷል። * በበጀት ዓመቱ ብቻ ከ40 በላይ በሚሆኑ የስልጠና ርእሶች ላይ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው አለም አቀፍ ስልጠናዎችን በነጻ ለአባላቱ መስጠቱ ተዘግቧል። * ማህበሩ በኤፍ ኤም 102.1 ሬዲዮ ጣቢያ "አልሰማንም እንዳትሉ" የሚለውን ፕሮግራም ስፖንሰር በማድረግ ለህብረተሰቡ የህግ ግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ እያከናወነ ይገኛል። * "የህግ ባለሙያዎች ለመቄዶንያ" በሚል መሪ ቃል በአይነት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ እና በገንዘብ 2,505,500.00 ብር ጨምሮ በድምሩ ከ17 ሚሊዮን ብር በላይ ለማዕከሉ ድጋፍ መደረጉ ተመዝግቧል። ....

  • አጭር ማስታወሻ የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማኅበር 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ኢንተር ሌግዥሪ ሆቴል፣ አዲስ አበባ በሚገኘው በዛሬው ዕለት መስከረም 27 ቀን 2018 ዓ.ም እየተካሄደ ነው። በፕሮግራሙ መሠረት ዋና ዋናዎቹ ተግባራት: * የአባላት ምዝገባ ተከናውኗል። * የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት እና የጉባኤው ይፋዊ የመክፈቻ ንግግር ቀርቧል። * ከ2016 ግንቦት ወር እስከ መስከረም 2018 ዓ.ም የተከናወነ የሥራ ክንውን ሪፖርት እንዲሁም የ2018 ዕቅድ እና የፋይናንስ ሪፖርት እየቀረበ ነው። * ከዚያ በኋላ የማህበሩ ረቂቅ መተዳደሪያ ደንብ፣ ተከታታይ የሕግ ሥልጠና የሚመራበትን ሥርዓት ለመወሰን የወጣ ረቂቅ መመሪያ እና የአባላት መዋጮ ረቂቅ መመሪያ ላይ ውይይት ይደረጋል።

  • без подписи