መጽሐፈ ግጻዌ
Статистикаይህ ቻናል በየዕለቱ በቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚባሉትን ምስባክና የሚነበቡትን የወንጌል ንባባት የሚያስተላልፍ ነው።
- Последний пост
- 12 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 11
- Всего постов
- 21
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Книги (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 1 182
- 1/48двое суток
- 1 354
- 1/72трое суток
- 1 460
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማቴ. 16፥13-24፡ "ወበጺሖ ኢየሱስ ብሔረ ቂሣርያ" ኢየሱስም፡ወደፊልጶስ፡ቂሳርያ፡አገር፡በደረሰ፡ጊዜ፡ደቀ፡መዛሙርቱን፦ሰዎች፡የሰውን፡ልጅ፡ማን፡እንደ፡ኾነ፡ይሉታል፧ብሎ፡ጠየቀ። እነርሱም፦ አንዳንዱ፡መጥምቁ፡ዮሐንስ፥ ሌላዎችም፡ኤልያስ፥ ሌላዎችም፡ኤርምያስ፡ወይም፡ከነቢያት፡አንዱ፡ነው፡ይላሉ፡አሉት። ርሱም፦እናንተስ፡እኔን፡ማን፡እንደ፡ኾንኹ፡ትላላችኹ፧አላቸው። ስምዖን፡ጴጥሮስም፡መልሶ፦አንተ፡ክርስቶስ፡የሕያው፡እግዚአብሔር፡ልጅ፡ነኽ፡አለ። ኢየሱስም፡መልሶ፡እንዲህ፡አለው፦የዮና፡ልጅ፡ስምዖን፡ሆይ፥በሰማያት፡ያለው፡አባቴ፡እንጂ፡ሥጋና፡ደም፡ይህን፡አልገለጠልኽምና፡ብፁዕ፡ነኽ።እኔም፡እልኻለኹ፥ አንተ፡ጴጥሮስ፡ነኽ፥በዚችም፡አለት፡ላይ፡ቤተ፡ክርስቲያኔን፡እሠራለኹ፥የገሃነም፡ደጆችም፡አይችሏትም። የመንግሥተ፡ሰማያትንም፡መክፈቻዎች፡እሰጥኻለኹ፤በምድር፡የምታስረው፡ዅሉ፡በሰማያት፡የታሰረ፡ይኾናል፥በምድርም፡የምትፈታው፡ዅሉ፡በሰማያት፡የተፈታ፡ይኾናል። ያን፡ጊዜም፡ርሱ፡ክርስቶስ፡እንደ፡ኾነ፡ለማንም፡እንዳይነግሩ፡ደቀ፡መዛሙርቱን፡አዘዛቸው፡፡ ከዚያን፡ቀን፡ጀምሮ፡ኢየሱስ፡ወደ፡ኢየሩሳሌም፡ይኼድ፡ዘንድ፡ከሽማግሌዎችና፡ከካህናት፡አለቃዎች፡ከጻፊዎችም፡ብዙ፡መከራ፡ይቀበልና፡ይገደል፡ዘንድ፡በሦስተኛውም፡ቀን፡ይነሣ፡ዘንድ፡እንዲገባው፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ይገልጥላቸው፡ጀመር። ጴጥሮስም፡ወደ፡ርሱ፡ወስዶ፦ አይኹንብኽ፡ጌታ፡ሆይ፤ይህ፡ከቶ፡አይደርስብኽም፡ብሎ፡ሊገሥጸው፡ ጀመረ። እርሱ፡ግን፡ዘወር፡ብሎ፡ጴጥሮስን፦ወደ፡ኋላዬ፡ኺድ፥አንተ፡ሰይጣን፤የሰውን፡እንጂ፡ የእግዚአብሔርን፡አታስብምና፡ዕንቅፋት፡ኾነኽብኛል፡አለው። በዚያን፡ጊዜ፡ኢየሱስ፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡እንዲህ፡አለ፦እኔን፡መከተል፡የሚወድ፡ቢኖር፥ራሱን፡ይካድ፡መስቀሉንም፡ተሸክሞ፡ይከተለኝ። ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ቅዳሴ ዘእግዝእትነ ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
без подписи
7/12/2018 ዓ.ም (፯/፲፪/፳፻፲፯ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ብፁዕ ብእሲ ዘአንተ ገሠጽኮ እግዚኦ። ወዘመርሀኮ ሕገከ። ከመ ይትገኀሥ እምመዋዕለ እኩያት። መዝ. 93፥12 🕯 ትርጉም ከክፉዎች ዘመናት ይወገ ዘንድ። አቤቱ አንተ የገሠጽኸው ሕግህንም ያስተማርኸው ሰው ምስጉን ነው። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልእክታት ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ 🕯ዕብ. 9፥1-11፡- "ወለቀዳሚትኒ ደብተራ።" 🕯1ኛ ጴጥ. 2፥6-18፡ -"እስመ ከመዝ ጽሑፍ ናሁ እሠይም።" 🕯ግብ: ሐዋ: 10፥1-30፡ - "ወሀሎ ፩ ብእሲ በሀገረ ቂሣርያ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዕለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማቴ. 1:1-17 "መጽሐፈ ልደቱ ለእግዚእነ" - "የዳዊት፡ልጅ፡የአብርሃም፡ልጅ፡የኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ትውልድ፡መጽሐፍ። አብርሃም፡ይሥሐቅን፡ወለደ፤ይሥሐቅም፡ያዕቆብን፡ወለደ፤ያዕቆብም፡ይሁዳንና፡ወንድሞቹን፡ወለደ፤ ይሁዳም፡ከትዕማር፡ፋሬስንና፡ዛራን፡ወለደ፤ ፋሬስም፡ኤስሮምን፡ወለደ፤ ኤስሮምም፡አራምን፡ወለደ፤አራምም፡ዐሚናዳብን፡ወለደ፤ዐሚናዳብም፡ነአሶንን፡ወለደ፤ነአሶንም፡ ሰልሞንን፡ወለደ፤ ሰልሞንም፡ከራኬብ፡ቦኤዝን፡ወለደ፤ቦኤዝም፡ከሩት፡ኢዮቤድን፡ወለደ፤ ኢዮቤድም፡እሴይን፡ወለደ፤ እሴይም፡ንጉሥ፡ዳዊትን፡ወለደ። ሰሎሞንም፡ሮብዓምን፡ወለደ፤ ሮብዓምም፡አቢያን፡ወለደ፤አቢያም፡አሣፍን፡ወለደ፤ አሣፍም፡ኢዮሳፍጥን፡ወለደ፤ ኢዮሳፍጥም፡ኢዮራምን፡ወለደ፤ኢዮራምም፡ዖዝያንን፡ወለደ፤ ዖዝያንም፡ኢዮአታምን፡ወለደ፤ኢዮአታምም፡አካዝን፡ወለደ፤ አካዝም፡ሕዝቅያስን፡ወለደ፤ሕዝቅያስም፡ምናሴን፡ወለደ፤ምናሴም፡አሞፅን፡ወለደ፤ አሞፅም፡ኢዮስያስን፡ወለደ፤ኢዮስያስም፡በባቢሎን፡ምርኮ፡ጊዜ፡ኢኮንያንንና፡ወንድሞቹን፡ወለደ። ከባቢሎንም፡ምርኮ፡በዃላ፡ኢኮንያን፡ሰላትያልን፡ወለደ፤ሰላትያልም፡ዘሩባቤልን፡ወለደ፤ ዘሩባቤልም፡አብዩድን፡ወለደ፤አብዩድም፡ኤልያቄምን፡ወለደ፤ኤልያቄምም፡አዛርን፡ወለደ፤ አዛርም፡ሳዶቅን፡ወለደ፤ሳዶቅም፡አኪምን፡ወለደ፤አኪምም፡ኤልዩድን፡ወለደ፤ ኤልዩድም፡አልዓዛርን፡ወለደ፤አልዓዛርም፡ማታንን፡ወለደ፤ማታንም፡ያዕቆብን፡ወለደ፤ ያዕቆብም፡ክርስቶስ፡የተባለውን፡ኢየሱስን፡የወለደች፡የማርያምን፡ዕጮኛ፡ዮሴፍን፡ወለደ። እንግዲህ፡ትውልድ፡ሁሉ፡ከአብርሃም፡እስከ፡ዳዊት፡አሥራ፡አራት፡ትውልድ፥ከዳዊትም፡እስከባቢሎን፡ምርኮ፡ዐሥራ፡አራት፡ትውልድ፥ ከባቢሎንም፡ምርኮ፡እስከ፡ክርስቶስ፡አሥራ፡አራት፡ትውልድ፡ነው።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
без подписи
7/12/2018 ዓ.ም (፯/፲፪/፳፻፲፯ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በዕለቱ በነግህ የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን። ያበድሮን እግዚአብሔር ለአናቅጸ ጽዮን። እምኵሉ ተዓይኒሁ ለያዕቆብ። መዝ. 86፥1 🕯 ትርጉም መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራራዎች ናቸው። ከያዕቆብ ድንኳኖች ይልቅ። እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች ይወዳቸዋል፡፡ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማር. 16፥9-19፡ "ወተንሢኦ በጽባሕ በእሁድ ሰንበት" - "ከሳምንቱም፡በመጀመሪያው፡ቀን፡ማልዶ፡በተነሣ፡ጊዜ፥አስቀድሞ፡ሰባት፡አጋንንት፡ላወጣላት፡ለመግደላዊት፡ማርያም፡ታየ። እርሷ፡ሄዳ፡ከርሱ፡ጋራ፡ሆነው፡ለነበሩት፡ሲያዝኑና፡ሲያለቅሱ፡ሳሉ፡አወራችላቸው፤ እነርሱም፡ሕያው፡እንደ፡ሆነ፡ለእርሷም፡እንደ፡ታያት፡ሲሰሙ፡አላመኑም። ከዚህም፡በኋላ፡ከነእርሱ፡ለሁለቱ፡ወደ፡ባላገር፡ሲሄዱ፡በመንገድ፡በሌላ፡መልክ፡ተገለጠ፤ እነርሱም፡ሄደው፡ለሌላዎቹ፡አወሩ፤እነዚያንም፡ደግሞ፡አላመኗቸውም። ኋላም፡በማእዱ፡ተቀምጠው፡ሳሉ፡ለዐሥራ፡አንዱ፡ተገለጠ፥ተነሥቶም፡ያዩትን፡ስላላመኗቸው፡አለማመናቸውንና፡የልባቸውን፡ጥንካሬ፡ነቀፈ። እንዲህም፡አላቸው፦ወደ፡ዓለም፡ሁሉ፡ሂዱ፥ወንጌልንም፡ለፍጥረት፡ሁሉ፡ስበኩ። ያመነ፡የተጠመቀም፡ይድናል፥ያላመነ፡ግን፡ይፈረድበታል። ያመኑትንም፡እነዚህ፡ምልክቶች፡ይከተሏቸዋል፤በስሜ፡አጋንንትን፡ያወጣሉ፤በዐዲስ፡ቋንቋ፡ይናገራሉ፤እባቦችን፡ይይዛሉ፥ የሚገድልም፡ነገር፡ቢጠጡ፡አይጎዳቸውም፤እጃቸውን፡በድውዮች፡ላይ፡ይጭናሉ፡እነርሱም፡ይድናሉ። ጌታ፡ኢየሱስም፡ከነርሱ፡ጋራ፡ከተናገረ፡በኋላ፡ወደ፡ሰማይ፡ዐረገ፡በእግዚአብሔርም፡ቀኝ፡ተቀመጠ።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ቅዳሴ ዘእግዝእትነ አው ግሩም ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
без подписи
6/12/2018 ዓ.ም (፮/፲፪/፳፻፲፯ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ወይሰግዳ ሎቱ አዋልደ ጢሮስ በአምኃ። ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኲሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር። ኲሉ ክብራ ለወለተ ንጉሠ ሀሴቦን። መዝ. 44፥12 🕯 ትርጉም የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትሽ ይማለላሉ። ለሐሴቦን ንጉሥ ልጅ ሁሉ ክብርዋ ነው። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዕለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልእክታት ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ 🕯1ኛ ቆሮ. 3፥10-22፡- "ወበከመ ጸጋሁ ለእግዚአብሔር።" 🕯1ኛ ጴጥ. 3፥1-7፡ -"ወከማሁ አንትንሂ አንስት ተኰነና።" 🕯ግብ: ሐዋ: 16፥13-19፡ - "ወወፃዕነ በዕለተ ሰንበት እምአንቀጸ ሀገር።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በዕለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ዮሐ. 20:11-19 "ወማርያምሰ ቆመት" - "ማርያም፡ግን፡እያለቀሰች፡ከመቃብሩ፡በስተውጭ፡ቆማ፡ነበር።ስታለቅስም፡ወደ፡መቃብር፡ዝቅ፡ብላ፡ተመለከተች፤ ሁለት፡መላእክትም፡ነጭ፡ልብስ፡ለብሰው፡የኢየሱስ፡ሥጋ፡ተኝቶበት፡በነበረው፡አንዱ፡በራስጌ፡ሌላውም፡በእግርጌ፡ተቀምጠው፡አየች። እነርሱም፦አንቺ፡ሴት፥ስለ፡ምን፡ታለቅሻለሽ፧ አሏት። እርሷም፦ጌታዬን፡ወስደውታል፡ወዴትም፡እንዳኖሩት፡አላውቅም፡አለቻቸው። ይህንም፡ብላ፡ወደ፡ኋላ፡ዘወር፡ስትል፡ኢየሱስን፡ቆሞ፡አየችው፤ኢየሱስም፡እንደ፡ሆነ፡አላወቀችም። ኢየሱስም፦አንቺ፡ሴት፥ስለ፡ምን፡ታለቅሻለሽ፧ ማንንስ፡ትፈልጊያለሽ፧አላት። እርሷም፡የአትክልት፡ጠባቂ፡መስሏት፦ጌታ፡ሆይ፥አንተ፡ወስደኸው፡እንደ፡ሆንህ፡ወዴት፡እንዳኖርኸው፡ንገረኝ፡እኔም፡እወስደዋለሁ፡አለችው። ኢየሱስም፦ ማርያም፡አላት። እርሷ፡ዘወር፡ብላ፡በዕብራይስጥ፦ረቡኒ፡አለችው፤ ትርጓሜውም፦ መምህር፡ሆይ፡ማለት፡ነው። ኢየሱስም፦ገና፡ወደ፡አባቴ፡አላረግሁምና፡አትንኪኝ፤ነገር፡ግን፥ወደ፡ወንድሞቼ፡ሄደሽ፦እኔ፡ወደ፡አባቴና፡ወደ፡አባታችሁ፡ወደ፡አምላኬና፡ወደ፡አምላካችሁ፡ዐርጋለሁ፡ብለሽ፡ንገሪያቸው፡አላት። መግደላዊት፡ማርያም፡መጥታ፡ጌታን፡እንዳየች፡ይህንም፡እንዳላት፡ለደቀ፡መዛሙርቱ፡ነገረች። ያም፡ቀን፡እርሱም፡ከሳምንቱ፡ፊተኛው፡በመሸ፡ጊዜ፥ደቀ፡መዛሙርቱ፡ተሰብስበው፡በነበሩበት፥ አይሁድን፡ስለ፡ፈሩ፡ደጆቹ፡ተዘግተው፡ሳሉ፥ ኢየሱስ፡መጣ፤በመካከላቸውም፡ቆሞ፦ሰላም፡ለእናንተ፡ይሁን፡አላቸው።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨