የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መዝሙር 🇪🇹
Статистика@Tewahdo27 የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮች 🌠በዝህ ቻናል የተለያዩ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙሮች የሚያገኙበት ቻናል ነው። መራግብራችን :-👇 ✅መዝሙሮች✅ የንስሐ መዝሙሮች✅ ያሬዳዊ ዜማ✅ የማርያም ውዳሴዎች✅ መፅሐፍ ሀይማኖት........ ወ.ዘ.ተ 🔵 YouTube 🔴ለሃሳብ እና አስታያየት @Tewahdo27
- Последний пост
- 4 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 140
- Тип
- открытый
- Язык
- am
- Категория
- Видео
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 593
- 1/48двое суток
- 679
- 1/72трое суток
- 732
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
https://youtube.com/shorts/WjrYbctx_8M?si=itntmc3b5RAxdQQv
ምክንያቱም የሕይወት መንፈስ ሕግ በክርስቶስ ኢየሱስ ከኀጢአትና ከሞት ሕግ ነጻ አውጥቷችኋል። ሮሜ 8፥2 እግዚአብሔር ይመስገን! ጽድቃችንን ለማረጋገጥና ድነታችንን ለማግኘት ሲባል ሕግን ከመጠበቅ ኢየሱስ አዳነን። የእግዚአብሔርን ፈቃድ በሕይወታችን መኖር የቻልነው በመንፈስ ቅዱስ ኀይል ነው። እርሱ የሕግ ፍጻሜ የሆነውን (ማቴዎስ 5፥17) ኢየሱስን ይበልጥ እንድንመስል ያደርገናል (ሮሜ 8፥28-29)፤ ይለውጠናል (2 ቆሮንቶስ 3፥18)። እግዚአብሔር ጥንት እንዳሰበው (ኤፌሶን 2፥8-10) መልካም ሥራን ለአዳኛችን ካለን ክብር የተነሣ ማድረግ እንችል ዘንድ በእምነት በኩል በጸጋ ዳንን። https://kedusbible.com
በዚህ ዓለም ነገር የሚጠቀሙም እንደማይጠቀሙበት ይሁኑ፤ የዚህ ዓለም መልክ ዐላፊ ነውና። 1 ቆሮንቶስ 7፥31 ይህ በአዲስ ኪዳን ውስጥ በተደጋጋሚ በኢየሱስ የተነገረ ጭብጥ ሲሆን፣ በኋላም ሐዋሪያው ጳውሎስ በድጋሚ አስተምሮታል። ይህም፣ ሕይወታችንን ጊዜያዊ በሆነ ነገር ላይ ማጥፋት እንደሌለብን የሚያስታውሰን ትልቅ ማሳሰቢያ መሆን አለበት። ሁሉም መንገሥታት፣ ሥርዐቶችና ኀይላት በመጨረሻ ያልፋሉ፤ ለዘላለምም ይጠፋሉ። ስለዚህ ለኢየሱስና ለመንግሥቱ ጊዜያችንና ጕልበታችንን እንስጥ። ለኢየሱስና ለመንግሥቱ የምናደርገው ነገር ብቻ ጸንቶ ይኖራል። https://kedusbible.com
https://youtube.com/shorts/6ZsWS-GJ1UA?si=xFCK5Oo-HlFdKbGT
ስለዚህ ሊይዙት ፈለጉ፤ ነገር ግን ጊዜው ገና ስላልደረሰ ማንም እጁን አላሳረፈበትም፤ ሆኖም ከሕዝቡ ብዙዎች በርሱ አምነው፣ “ታዲያ፣ ክርስቶስ ሲመጣ ይህ ሰው ከሚሠራቸው ታምራዊ ምልክቶች የበለጠ ያደርጋል?” አሉ። ዮሐንስ 7፥30-31 የኢየሱስ ጠላቶች በተደጋጋሚ ሊይዙት ጥረት አድርገዋል። የዮሐንስ ወንጌል፣ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ዕቅድ መሠረት በትክክለኛው ጊዜ ራሱን አሳልፎ እስኪሰጥ ድረስ ማንም ሊይዘው እንደማይችል በተደጋጋሚ ያስታውሰናል። ኢየሱስ የአብን ፈቃድ ለመታዘዝ ሲጠነቀቅ እንደ ነበረው ሁሉ፣ የእግዚአብሔርንም ጊዜ ሲጠብቅ ነበር። ስለዚህ ኢየሱስ ሲሞት፣ ሊያድነንና የአብን ፈቃድ ሊታዘዝ እንደ ሞተ ፍጹም ርግጠኞች መሆን እንችላለን። ጌታ የሞተው ራሱን ለመከላከል ዐቅም ስላጣ አይደለም። የኢየሱስ ሞት በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ መሥዋዕት ነው፤ ከራሱ የመትረፍ ፈቃድ ይልቅ፣ የአብን ፈቃድ የታዘዘበት ድል ነው። አዎ፣ ክፉ ሰዎች ኀላፊነቱን ቢወስዱም፣ ሞቱ እኛን ለማዳን የተደረገ የእግዚአብሔር ዕቅድ ነው! ኢየሱስ ታዘዘ፣ እኛም ዳንን! ከኀጢአት፣ ከሞት፣ ከሲኦልና ከክፉ ባርነት ነጻ እንወጣ ዘንድና ወደ እግዚአብሔር ቤተ ሰብ እንቀላቀል ዘንድ፣ በትክክለኛው በእግዚአብሔር ጊዜ ራሱን አሳልፎ ሰጠ! https://kedusbible.com
ትንሽ እንታገስ እንጂ እግዚአብሔር ያሳካዋል🙌💔
አምንሀለው🤲💔
በፊትህ ለዘላለም ጸንቶ እንዲኖር፣ አሁንም የባሪያህን ቤት እባክህ ባርክ። ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህን አንተው ራስህ ተናግረሃል፤ በበረከትህም የባሪያህ ቤት ለዘላለም ይባረካል። 2 ሳሙኤል 7፥29 እግዚአብሔር ንጉሥ ዳዊትን እጅግ ባርኮታል። እግዚአብሔር ከተናቀ ታናሽ ወንድምና እረኛ ከመሆን ወደ ታላቅ ተዋጊና የእስራኤል ንጉሥ ወደ መሆን አምጥቶታል። ዳዊት ከትንሽ ልጅ ወደ ጀግና ጦረኛ፣ ከማትታወቅ ትንሽ ከተማ ወደ ታላቅ ሀገር መሪነት ተሻግሯል። ነገር ግን፣ የዳዊት ሐሳብ የነበረው፣ እግዚአብሔር ለርሱና ለዘሩ ቅርብ እንዲሆንና የሰጠውንም ተስፋ እንዲጠብቅ ነበር። ዳዊት በሕይወቱ ከተማራቸው ብዙ ነገሮች መኻል ትልቁና ዋነኛው ወደ ፊቱ ወይም የትኛውም ጦርነት እና ተስፋ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ከርሱና ከዘሩ ጋራ ባለው ዐብሮነት ላይ የተመሠረተ መሆኑ ነው። እግዚአብሔር ሲናገር ቃሉን ይጠብቃል። እግዚአብሔር ሲሠራ፣ ነጻ ያወጣል ያድናል፤ ድልንም ያጐናጽፋል። ስለዚህ ዳዊት እግዚአብሔርን የጠየቀው ራሱ እግዚአብሔር ሊያደርግ የሚፈልገውን ነገር ነው፤ ይኸውም፣ ሕዝቡን እንዲባርክና ቃሉን እንዲጠብቅ ነው። በተመሳሳይም ለእኛ ሊያደርግ እንደሚችል ይህ ክፍል ያስታውሰናል! https://kedusbible.com
ኢየሱስ ማስተማሩን በፈጸመ ጊዜ፣ ሕዝቡ በትምህርቱ ተደነቁ። ምክንያቱም እንደ አይሁድ ሃይማኖት መምህራናቸው ሳይሆን እንደ ባለሥልጣን ያስተምራቸው ስለ ነበር ነው። ማቴዎስ 7፥28-29 በዘመኑ እንደ ነበሩት አስተማሪዎች፣ ኢየሱስ ትምህርቱን ለማስተማር በፊት ከነበሩት አስተማሪዎች ወይም ከታዋቂ ረቢዎች አባባል ወይም ጥቅስ መጥቀስ አይጠበቅበትም ነበር። ራሱ የእግዚአብሔር ቃል የሆነው ኢየሱስ (ዮሐንስ 1፥1-18) የሚናገረው የእግዚአብሔር ቃል ነበር። አብ የፈቀደውን ይናገርና ይፈጽም ነበር። ሕይወቱና ንግግሩ እውነት ነበሩ። ወንጌላት (ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስና ዮሐንስ) የኢየሱስን ኀይልና ሥልጣን በማሳየት፣ በዘመናት ውስጥ የኢየሱስን እውነት እንድንቀበልና እንደ ጌታችን እንድንከተለው ይጠሩናል። ይህ አስተማሪያችና አዳኛችን ኢየሱስ፣ ከሌሎቹ ታላላቅ አስተማሪዎች፣ ጠቢባንና ነቢያቶች በላይ ነው። ቃላቶቹ ኀያል ናቸው። ትምህርቶቹም ሥልጣን አላቸው። ሕይወቱ አስደናቂ ነው። ፍቅሩ ወደር የለውም። ስለዚህ ውድ የኢየሱስ ወዳጅ ሆይ የርሱ ፈቃድ ያንተም ፍላጎት ሊሆን ይገባል! https://kedusbible.com
አስጸያፊ ነገርን ወደ ቤትህ ወይም ወደ ራስህ አታምጣ፤ አለዚያ አንተም እንደ እርሱ ለጥፋት ትዳረጋለህ፤ ፈጽመህ ጥላው፤ ተጸየፈውም፤ ለጥፋት የተለየ ነውና። ዘዳግም 7፥26 ትንሽ ሙስና፣ ትንሽ መርዝና ትንሽ የበሰበሰ ነገር ያን ያህል መጥፎ አይደሉም አይደል? በፍጹም፣ መጥፎ ናቸው! እግዚአብሔር በክርስቶስ በኩል ንጹሕና ፍጹም አድርጎናል (ቈላስይስ 1፥21-23)። እንዴት ደስ የሚል ሐሳብ ነው! ታዲያ ይህን ፍጹም ማንነት በክፋት፣ በበሰበሰ ነገርና በሚያጸይፍ ነገር የምናቈሽሸው ለምንድን ነው? አባታችን ራሳችንን ለርሱ አሳልፈን እንድንሰጥና እንደ እርሱ ቅዱስ ሕዝብ እንድንኖር ይፈልጋል (ሮሜ 12፥1-2፤ 1ጴጥሮስ 1፥13-16)። እግዚአብሔር በሙሴ ሥር የነበሩት እስራኤላውያን፣ ለጥፋት ከለያቸው ነገሮች መራቅ እንዳለባቸው እንዲያውቁ እግዚአብሔር ይፈልጋል። እንዲህ ያለውን ማስጠንቀቂያ ችላ ማለት ብንፈልግ እንኳ፣ እግዚአብሔር በጳውሎስ በኩል ለመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን ለነበሩ ክርስቲያኖች ሁሉንም ዐይነት ክፉ ነገሮች እንዳይቀበሉ ይናገራል። እነዚህን ክፍሎች አንብቡ፤ 1 ተሰሎንቄ 4፥3-8፤ 5፥22 https://kedusbible.com
እኔ ምን ዐይነት ጐስቋላ ሰው ነኝ! ከዚህ ለሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ሊያድነኝ ይችላል? በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ምስጋና ለእግዚአብሔር ይሁን! ሮሜ 7፥24-25 ሰውነታችን ሟችና ጕድለት ያለበት ነው። ድካማችንና ኀጢአታችን የተበላሸ አድርጎታል። ነገር ግን፣ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በተሰጠን የእግዚአብሔር ጸጋ (ኤፌሶን 2፥1-10) እና በሚለውጠው በመንፈስ ቅዱስ ኀይል (2 ቆሮንቶስ 3፥17-18) ምክንያት ወደ ፊታችን ከሚበሰብሰው ሥጋችን ጋራ አይደለም። ይልቁንስ ፍጹም በሚያደርገው ጌታችን እጅ ውስጥ ነው። ጳውሎስ በሮሜ 8 ላይ ይበልጥ እንደሚያብራራው ኢየሱስ አዳኛችን ነው፤ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ኀይላችን ነው! https://kedusbible.com
በመካከልህ ያለው አምላክህ እግዚአብሔር ታላቅና የሚያስፈራ አምላክ ስለ ሆነ አያስደንግጡህ። ዘዳግም 7፥21 እንደ እግዚአብሔር ሕዝብ የሚያሸንፈን ማን ነው? የቅዱሱን እግዚአብሔር መገኘት በደስታ ስንቀበል ማንም ሊያሸንፈን አይችልም። አምላካችን በኀይል ታላቅ፣ በቅድስናው የሚያስፈራ ከጠላቶቻችንም የሚበልጥ አምላክ ነው። በታሪክ ውስጥ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያለውን ፍቅር፣ ዐብሮ መገኘትና ኀይል አሳይቷል። ስለዚህ ክፉው እንድናደርግ የሚያስፈራራንን መቃወም እንችላለን። ምክንያቱም አዳኛችን ሲኦልን፣ ኀጢአትን፣ ሰይጣንና አጋንንቶችን አሸንፏል። አንድ ቀን ደግሞ ይህን ድል ለዘላለም ዐብረን እናጣጥመዋለን። https://kedusbible.com
ትክክለኛውን ነገር የሚያደርግና ፈጽሞ ኀጢአት የማይሠራ ጻድቅ ሰው በምድር ላይ የለም። መክብብ 7፥20 አዎ፣ ሁላችንም ወድቀናል፣ እንከን አለብን፣ ተበክለናል (ሮሜ 3፥9-11፣ 23-24)። ወይም እግዚአብሔር እኛን ከማዳኑ በፊት፣ መንፈስ እኛን ከማንጻቱ በፊት፣ ኢየሱስ እኛን ወደ ቤተ ሰቡ ከመቀላቀሉ በፊት እንዲህ ነበርን (1 ቆሮንቶስ 6፥9-11)። እግዚአብሔር ይመስገን! ስለ ጸጋው እግዚአብሔር ይመስገን! ስለ ኢየሱስ ሥራ እግዚአብሔር ይመስገን! ስለ መንፈስ ቅዱስ መገኘት እግዚአብሔር ይመስገን! ከእነዚህ የተነሣ፣ በእግዚአብሔር ፊት ቅዱስ፣ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ መቆም ችለናል (ቈላስይስ 1፥22)። https://kedusbible.com
ታላላቅ ፈተናዎችን፣ ታምራዊ ምልክቶችንና ድንቅ ነገሮችን አምላክህ እግዚአብሔር አንተን ያወጣበትን ብርቱ እጅና የተዘረጋች ክንድ በገዛ ዐይንህ አይተሃል። አምላክህ እግዚአብሔር አሁን በምትፈራቸው ሕዝቦች ሁሉ ላይ ያንኑ ያደርጋል። ዘዳግም 7፥19 ብዙ ጊዜ የእግዚአብሔርን የቀደመ ሥራ ተመልክተን፣ በአባቶቻችን ዘመን እንደ ተገለጠው የእግዚአብሔር ኀይል በእኛም ዘመን አናይም ብለን እናስባለን። እግዚአብሔር በሙሴ የስንብት ቃል በኩል፣ አባቶቻቸውን ከግብፅ ነጻ እንዳወጣቸው ከእነርሱም ጋራ ዐብሮ እንደሚሆንና እንደ አባቶቻቸው እንደሚያበረታቸው አዲሱን ትውልድ ያስታውሳቸዋል። ከምንጠይቀው ወይም ከምናልመው በላይ በእኛ ውስጥ ባለው ኀይሉ በኩል እንደሚያደርግ መጠበቅ አለብን (ኤፌሶን 3፥20-21)። እግዚአብሔር በእምነት አባቶቻችን በኩል ሲያደርግ የሰማነውን፣ በእኛም ጊዜ እንዲያደርግ መጸለይ አለብን (ዕንባቆም 3፥2)። ውድ የኢየሱስ አማኝ፣ የአዳኛችንን ተስፋ ልናስታውስ ይገባል። https://kedusbible.com
ነገር ግን የልዑሉ ቅዱሳን መንግሥቱን ይወስዳሉ፤ ለዘላለምም ይይዙታል፤ አዎን፤ ለዘላለም ይይዙታል። ዳንኤል 7፥18 መንግሥቱ ለእግዚአብሔር ቅዱሳን፣ ለልጆቹ፣ ለኢየሱስ ተከታዮችና ለልዑሉ ሕዝብ ይሆናል (ዳንኤል 7፥27)። ለዘላለም! መንግሥቱ የእኛ ይሆናል! የሰው ልጅ ከእኛ ጋራ ይሆናል (ዳንኤል 7፥13) መንግሥቱም ለዘላለም የእኛ ይሆናል። ለሰጠን ተስፋ፣ ለጸጋውና ለታማኝነቱ እግዚአብሔር ይመስገን። ውሱን በሆነው ሰዋዊ እይታችን ወደ ፊታችን ምንም ያህል አስፈሪ ቢመስልም፣ እግዚአብሔር በሰጠን ተስፋና ኢየሱስ በኀጢአት፣ በሞትና በሲኦል ካለው ድል የተነሣ ወደ ፊታችን ርግጥ ነው! https://kedusbible.com
ምክንያቱም በዙፋኑ መካከል ያለው በግ እረኛቸው ይሆናል፤ ወደ ሕይወት ውሃ ምንጭም ይመራቸዋል፤ እግዚአብሔር እንባን ሁሉ ከዐይናቸው ያብሳል።” ራእይ 7፥17 እንዴት ደስ የሚል ምስል ነው! ስለ እኛ የሞተው ይመግበናል፤ ያድሰናል። ዘላለም የተንጠለጠለበት አምላክ እኛን በግል ለማጽናናት ጊዜ ይወስዳል። "ሞትን ደምስሶ ኢመዋቲነትን ወደ ብርሃን" (2ጢሞቴዎስ 1፥10) ያመጣው አምላክ ሕያው ውሃ የሆነውን መንፈስ ቅዱስን ልኮልናል (ዮሐንስ 7፥37-39)። ጳውሎስ አሁን ያለውን ሥቃይ ኢየሱስ ሊገልጥልን ካለው ክብር ጋራ ሲነጻጸር፣ ምንም እንዳይደለ ቢቈጥር አይገርምም (ሮሜ 8፥18)። https://kedusbible.com
በስሜ የተጠራው ሕዝቤ ራሱን አዋርዶ ቢጸልይ፣ ፊቴን ቢፈልግና ከክፉ መንገዱ ቢመለስ፣ ከሰማይ እሰማዋለሁ፤ ኀጢአቱን ይቅር እላለሁ፤ ምድሩንም እፈውሳለሁ። 2 ዜና 7፥14 በዚህ ዘመን ሰዎች ይህን ምንባብ ሀገራት፣ መንግሥታትና መሪዎች ንሰሓ መግባት እንደሚያስፈልጋቸው ለማሳየት የሚጠቀሙበት ክፍል ነው። ይህ ክፍል ከእስራኤል፣ ከእኛና "የእግዚአብሔር እስራኤል" ከሆነችው ቤተ ክርስቲያን ጋራ በትክክል የሚዛመድ መሆኑን እናስብ (ገላትያ 3፥26-29፤ 6፥16፤ ሮሜ 9፥6-9)። ከዐመፃ መንገድ ከተመለስን፣ የእግዚአብሔርን ይቅርታና መገኘት ከፈለግንና በየዕለቱ ለመጸለይ ከወሰንን በምድራችን፣ በአብያተ ክርስቲያኖቻችንና ባለንበት ስፍራዎች ሁሉ መነቃቃትን ማምጣት እንችላለን። https://kedusbible.com
'ሐምሌ አቦ'፣ 'ጉዝጉዞ'/'ደበሎ' ሀምሌ ፭(5) ቀን "ሀምሌ አቦ" የሚል የተለመደ ስያሜ አለው። እለቱ እንደየአካባቢው 'ደበሎ'፣ 'ጉዝጉዞ' ወይም 'አነባበሮ' የሚባል ምግብ እየተዘጋጀ ይከበራል። ከላይ የተጠቀሱት ምግቦች ያልቦካ ሊጥ በወፍራሙ ተጋግሮ ሁለቱን በማነባበር የሚዘጋጁ ሲሆኑ 'ደበሎ' የሚባለው ኑግና ተልባ ተወቅጦ በአነባበሮው መሃል ተቀብቶ የሚዘጋጅ ነው። ይህን ምግብ ያልበላ የክረምቱ ብርድ እንደሚበረታበት፣ የበላ ግን በልብስነት ያገለግል እንደነበረው ደበሎ(ለምድ) ሞቆት እንደሚከርም ይነገራል። ሀምሌ ፭ ቀን የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወርሀዊ በዓል ሲሆን ዋናው የዓመት በዓሉ ግን "#ጴጥሮስ_ወጳውሎስ" ይባላል። አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከኖሩት ጠቅላላ እድሜያቸው 562(፭፻፷፪) ዓመት ውስጥ 262 (፪፻፷፪)ቱን በኢትዮጵያ ውስጥ ኖረዋል። ሐምሌ 5(፭) ቀን ርእሰ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ እና ብርሀነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ያረፉባት ስለሆነች "ጴጥሮስ ወጳውሎስ" ተብሎ ይከበራል። ከጽኑእ ፍቅራቸው የተነሳ እረፍታቸው በአንድ ቀን ሆነ። ቅዱስ ጴጥሮስ አለቃ ነኝ ሳይል ቅዱስ ጳውሎስም ልጅ ነኝ ሳይል አንዱ አንዱን እየገሰጸው እየተመካከሩ ዓለምን ዙረው በወንጌል አጣፍጠዋት በዚህች ዕለት አርፈዋል። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ 67(፷፯) ዓ/ም ሀምሌ አምስት ቀን በኔሮን ቄሣር እጅ ቁልቁል ተሰቅሎ ሰማዕትነትን ተቀብሏል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም እንዲሁ 67(፷፯) ዓ/ም በአንድ ቀን በአንድ ቦታ በኔሮን ቄሣር እጅ አንገቱን ተቆርጦ ሰማዕትነትን ተቀብሏል። ለቅዱስ ጴጥሮስና ለቅዱስ ጳውሎስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን አንድ ላይ እንጂ ለየብቻ አይሰራላቸውም። ቤተክርስቲያኑም "ጴጥሮስ ወጳውሎስ" ተብሎ ይሰየማል። በዚህች ቅድስት ቤተክርስቲያን የኖሩት የሚኖሩትም ወደኋላ የቀሩ፣ ያልተማሩ፣ ጥቅስ መጥቀስ የማይችሉ፣ ባህልና ሃይማኖት ያለዩ፣ የምንላቸውና የሚመስሉን እናቶቻችን ሁለቱን እንጀራ፣ ቂጣ፣ ተልባ፣ ኑግ፣ ቅቤ የመሳሰሉትን በመጨመር አንድ ላይ አነባብረው የቅዱሳን ሐዋርያትን እረፍት ይዘክራሉ። ሁለቱ እንጀራ የቅዱስ ጴጥሮስና የቅዱስ ጳውሎስ ምሳሌ ከመካከል የሚደረገው ደግሞ የእምነታቸው ምሳሌ እያሉ ያስቧቸዋል። ለከርሞ ያድርሳችሁ።
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи