Saint George Sport Club - Offical Page/የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ይፋዊ ቴሌግራም ቻናል
СтатистикаProfessional Sport Club Website -http://saintgeorgefc.com/blog/ Facebook - https://www.facebook.com/Saint-George-SA-177342563049631 YouTube -https://www.youtube.com/channel/UC1M4f0IYEbdcwjMz-QQrepg 💛❤️አንድ ክለብ አንድ ቤተሰብ 💛❤️
- Последний пост
- 15 авг.
- Последнее чтение
- 14 авг.
- Постов за неделю
- 21
- Всего постов
- 204
- Тип
- открытый
- Язык
- французский
- Категория
- Видео
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 2 235
- 1/48двое суток
- 2 561
- 1/72трое суток
- 2 762
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
ስዩም ተሰይሟል ✅
Ready or not,a serial champion is in town ✌️
አሚኑ ነስሩ በቅዱስ ጊዮርጊስ ያለውን ውል አራዝሟል ✌️
📌
ፍስሃ ወልደ አማኑኤልን ስናስታውሰው ከ4⃣ኛው እስከ 7⃣ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ድረስ ተጫውቷል፡፡ኢትዮጵያ ባዘጋጀችው 6ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በኮንጎ 3 ለ 2 ተሸንፋ ከውድድሩ ስትወጣ ክፉኛ ያዘነው ፍስሃ ለ6 ቀናት ከጣይቱ ሆቴል ማረፊያው ሳይወጣ አልቅሷል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ክለባችን በታሪኩ ካያቸው ድንቅ ተጫዋቾች መሀከል አንዱ በሆኑት አቶ ፍስሃ ወልደ አማኑኤል እረፍት ክፉኛ ማዘኑን መግለጽ ይወዳል፡፡ጋሽ ፍስሃ በተጫዋችነታቸው ወርቃማ የሆነ ታሪክ የጻፉ ከመሆናቸውም በላይ ክለባቸውን በአስተዳደር ዘርፍም አገልግለዋል፡፡የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ለቤተሰቦቻቸው ፥ ለወዳጆቻቸው እንዲሁም ለመላው የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ደጋፊዎች መፅናናትን ይመኛል፡፡
ብሩክ እንዳለ በዛሬው እለት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በመገኘት በቅዱስ ጊዮርጊስ ለ2 አመታት የሚያቆየውን ውል ፈርሟል ✌️ እንኳን ወደ ትልቁ ቤት መጣህ 🏆 ቅዱስ ጊዮርጊስ 🤝 ብሩክ እንዳለ
FASIL TEKALIGN✌️ he was one of us! he is one of us! he will forever be one of us! 💛❤️
ግብ ጠባቂያችን ኮክ ኩዌስ ለተጨማሪ 2 አመታት በፈረሰኝነት የሚያቆየውን ውል ፈርሟል 🖊
ያሬድ የማነ ቅዱስ ጊዮርጊስን ተቀላቅሏል፡፡የግራ መስመር ተከላካዩ በኢትዮ ኤሌክትሪክ ውጤታማ የውድድር አመትን ያሳለፈ ሲሆን በሊጉ ካሉ ምርጥ የክንፍ ተከላካዮች አንዱ ነው፡፡በአሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጥሪ የተደረገለት ያሬድ በቅዱስ ጊዮርጊስ ለሁለት አመታት የሚያቆየውን ውል ፈርሟል✌️ ያያ ፥ ወደ ትልቁ ቤት እንኳን በደህና መጣህ 👋 ቅዱስ ጊዮርጊስ 🤝 ያሬድ የማነ
ላለፉት ሁለት አመታት ቡድናችንን በዋና አሰልጣኝነት የመራው ኢንስትራክተር ፋሲል ተካልኝ በክለባችን የነበረው የአሰልጣኝነት ቆይታ ተጠናቅቋል፡፡በተጫዋችነት በዋንጫዎች ያጌጠ ታሪክን በፈረሰኞቹ ቤት የሰራው ኢንስትራክተር ፋሲል በተለይም ክለባችን አስቸጋሪ ጊዜያትን ባሳለፈባቸው ባለፉት 2 አመታት በፍጹም ታማኝነት እና ትጋት ክለባችንን በማገልገሉ ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡ኢንስትራክተር ፋሲል በቀጣይ የእግር ኳስ ጉዞው ስኬትን እንዲገጥመው ምኞታችን ነው፡፡
ባለፈው ሳምንት ምን ተከናወነ? - የተስፋ ቡድናችን የአመቱን ውድድሩን መቻልን 4 ለ 1 በማሸነፍ አጠናቅቋል፡፡በዚህም መሰረት ውድድሩን አራተኛ ሆኖ በማጠናቀቁ ከነሀሴ 15 - 30 በአዳማ ከተማ ለሚካሄደው የማጠቃለያ ውድድር ተሳታፊነቱን አረጋግጧል፡፡ - በተጠናቀቀው ሳምንት በይፋ በተከፈተው የዝውውር መስኮት ቅዱስ ጊዮርጊስ የ3 ነባር ተጫዋቾችን ውል ሲያድስ ሁለት አዳዲስ ተጫዋቾችም ቅዱስ ጊዮርጊስን ተቀላቅለዋል፡፡በፈረሰኝነታቸው እንደሚቀጥሉ የተረጋገጠው ሶስት ተጫዋቾች ተከላካዩ ብሩክ ታረቀኝ ፥ የክንፍ አጥቂው ጸጋ ከድር እና አማካዩ ፉአድ አብደላ ሲሆኑ ግብ ጠባቂው ቢንያም ገነቱ ከወላይታ ድቻ እንዲሁም ተከላካዩ ቢንያም በቀለ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ አዲስ ፈራሚ ሆነዋል፡፡ - ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ቃል በገባው መሰረት የይድነቃቸው ተሰማ አካዳሚ እድሳት ዛሬ የተጀመረ ሲሆን የአካዳሚውን ደረጃ ከፍ የሚያደርግ የእድሳት ስራ ይከናወንበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡እድሳቱን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎችን በቀጣይ ቀናት የምናቀርብ ይሆናል፡፡ - የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ለረዥም ጊዜ ሲጠይቁት የነበረው የኦዲት ስራ በባለሙያዎች መከናወን ከጀመረ ሁለተኛ ሳምንት ላይ ደርሷል፡፡የክለቡን ወቅታዊ ቁመና በተመለከተ ተጨባጭ መረጃ ሊሰጥ ይችላል ተብሎ የሚጠበቀው የኦዲት ስራ ሂደትን እና አንድምታ በተመለከተ በቀጣይ መረጃዎች የምናደርስ ይሆናል፡፡ በዚህ ሳምንት ምን ይከናወናል? - በዚህ ሳምንት ሰነዶቻቸው የተሟላላቸው ተጫዋቾች በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በመገኘት ፊርማቸውን ያኖራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ - የፊታችን አርብ በሸራተን አዲስ ጋዜጣዊ መግለጫ ይደረጋል ተብሎ ታቅዷል፡፡ - ለአዲስ የውድድር ዘመን ዝግጅትን ለማከናወን የሚያስችሉ የዝግጅት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡ - ከ17 አመት በታች ቡድናችን ለአዳማው ውድድር ልምምዱን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ - የልምምድ ማእከሉ እድሳት እና የኦዲት ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ - ከክለቡ ጋር የተለያዩ ተጫዋቾች እና አሰልጣኞች ዝርዝር በዚህ ሳምንት ይፋ ይደረጋል፡፡
видео или голосовое, без подписи