Ethiopian Students Network 🇪🇹( ESN)
СтатистикаA space for every Ethiopian student — elementary, highschool, or university. Discussion: @EthioStudentsChat
- Последний пост
- 15 февр.
- Последнее чтение
- 13 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 40
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- —
- 1/48двое суток
- —
- 1/72трое суток
- —
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
#Haramaya_University #Biomedical_Engineering 🔬 Haramaya University has announced the opening of a new department, "Biomedical Engineering." @EthiopianStudentsTM @EthiopianStudentsTM
#NationalExam ትምህርት ሚኒስቴር ፤ " የዚህ አመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ይሰጣል " አለ። በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ2018 የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ " በዚህ ዓመት የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መቶ በመቶ በበይነ መረብ ይሰጣል " ሲሉ ተናግረዋል። ይህን ያሉት በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግማሽ ዓመት አፈፃፀም መድረክ ላይ ተገኝተው ነው። ባለፉት ሁለት ዓመታት ፈተናው በወረቀትና በበይነ መረብ ሲሰጥ እንደነበር አንስተው በዚህ ዓመት የሚሰጠውን ማጠናቀቂያ ፈተና ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ጠቁመዋል። ለዚህም የተለያዩ ግብዓቶች ለክልሎች ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰው በፈተና ጣቢያዎች በቂ የኢንተርኔት አቅርቦት እንዲኖር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመነጋገር ይሰራል ብለዋል። ክልሎች በዚህ ሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮች እንዳይኖሩ በቂ ኮምፒዩተር ፣ ኔትዎርክና አማራጭ የሀይል አቅርቦት እንዲኖር ልዩ ትኩረት ሰጥተው መዘጋጀት እንዳለባቸው አሳስበዋል። ለተማሪዎችም በቂ ሥልጠና መስጠት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የክልልና ከተማ መስተዳድሮች ይህንን አውቀው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል። በትምህርት ሚኒስቴር የዲጅታል ትምህርትና አይሲቲ ሥራ አስፈፃሚ ዘላለም አሰፋ (ዶ/ር) ፤ ተማሪዎች የሚለማመዱባቸው ሞዴል ፈተናዎች በበቂ ሁኔታ የተጋጁ መሆኑን ገልጸዋል። " ተማሪዎች አስቀድመው እንዲለማመዱና ሥልጠና እንዲያገኙ ማድረግ ይገባል " ብለዋል። #MoE @EthiopianStudentstm @EthiopianStudentstm
🚀 Level up your learning! Top 100 YouTube Channels to Learn Almost Anything — coding, science, languages, and more. #LearnOnline @EthiopianStudentsTM
ለ Fresh ተማሪዎች ምክር ቢጤ 🤹♀ ህይወት ብዙ ምርጫዎች አሏት የሰው ልጅም ከእነዚህ ምርጫዎች በአንዱ መወሰን ግዴታው ነው ። የምንመርጠው ምርጫ የወደፊት መንገድ ነው ። ዛሬም አንዱን ትመርጣለህ ወደድክም ጠላህም ። 📌 በዩንቨርሲቲ ቆይታህ በትምህርቱ ዘርፍ ሀ ..ብለህ ለመጀመር ምርጫ ትመርጣለህ በተለይ ለመጀመሪያ አመት ተማሪወች 👉ምን የትምህርት አይነት መማር አለብኝ ? 👉የኔ ዝንባሌ እና አቅሜ የሚችለው ምንድነው ? 👉እሆናለሁ ብዬ አስብ የነበረው ህልሜ ምንድነው ?? 🎯 እነዚህ ጥያቄዎችን መመለስ ከቻልክ የምትፈልገውን ለማግኘት አትቸገርም ። ነገር ግን መሆን የምትፈልገውንና መማር ምትፈልገውን መምረጥ ካቃተህ ዛሬውኑ እራስህን ጠይቅ ወይም 👨👩👧👧ቤተሰብ :ጓደኛህን/ሽን አማክር /ሪ ። ስታማክር የራሴ የምትለውን ነገር ይዘህ እንጂ ያማከርካቸው ሰወች ያሉህን አትውሰድ ። 📌በሰው ምርጫ አትወሰን ይልቅ ሰው መርጦልህ ከምትበሳጭ በራስህ ምርጫ ብትበሳጭ ይሻልህል ። 📌 በመረጥከው ምርጫ ስኬታማ ለመሆን ያለህን አቅም አሟጠህ ተጠቀም: የሚያስፈልገውን መስዋዕትነት ክፈል ትርጉም ያለው ህይወት ለመኖር ስትል ። የምትማረውን ትምህርት በተግባር ኑረው‼️ 🔨ህግ ተምረህ የግቢው አስበጥባጭ ተማሪ ከሆንክ ትምርቱ አልገባህም ማለት ነው!! 👷ኢንጂነሪንግ እየተማርክ ህንፃና ንብረት ለማጥፋት ከተነሳህ ምርጫህ ልክ አይደለም!! 👉ሶሺዮሎጂ እየተማርክ ማህበረሰብህን ካላወቅህ ባክነሀል ማለት ነው ትምህርቱን አቋርጥ!! 📙ታሪክን አጥንተህ በአድዋ ኮርተህ ስለአንድነት መስበክ ካልቻልክ ይቅርብህ አቋርጠው!! 🎯 የምትማረው ስርዓት ያለው ዜጋ ለመሆን ነውና መርጠህ ተማር የመረጥከውን ኑረው እየኖርክም ህዝብህን አገልግል ። የምትማረው በኢትዮጲያ ህዝብ ገንዘብ ነውና ። A space for every Ethiopian student — elementary, highschool, or university. @EthiopianstudentsTM
የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎች ይፋ ሆኑ፡፡ የ2017 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈተኑ ተፈታኞች በሚከተሉት አድራሻዎች ዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ፡፡ ዌብ ሳይትና ቴሌግራም አድራሻ የሚጠቀሙ ተፈታኞች ጊዜያዊ ሰርቲፊኬታቸውን ወዲያውኑ አውርደው (download አድርገው) መውሰድና መጠቀም ይችላሉ፡፡ አድራሻዎቹ፡ 1. ዌብ ሳይት፡ https://result.eaes.et 2. ቴሌገራም፡ https://t.me/EAESbot 3. አጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡ 6284 ስለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ትክክለኛ መረጃን ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማህበራዊ ሚዲያዎች ያገኛሉ፡፡ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መስከረም 05/ 2018 ዓ/ም @EthiopianStudentsTM
📈12ኛ ክፍል ተማሪዎች በአዲስ የምዘና ሥርዓት መመዘን ከጀመሩበት 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2017 ድረስ በጠቅላላው 🔗 3,011,607 ለፈተና ተቀምጠዋል 🔗 የማለፊያ ነጥቡን (50%) ያገኙት 🔗 በጠቅላላው 142,514 ተማሪዎች ወይም 4.7% ብቻ ናቸው 🔗 2,869,093 የሚሆኑት ወይም 95.3 % ተማሪዎች ማለፊያውን ማግኘት አልቻሉም:: JOIN:@EthiopianStudentsTM ✅
" ስንጠብቅ ያነበረው ይህንን ውጤት ነው " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑት 585,879 ተማሪዎች መካከል 48,929 ተማሪዎች 50 በመቶ አምጥተው አልፈዋል። ይህም 8.4 በመቶ ነው። በ2016 ዓ/ም ከ674,823 ተማሪዎች ያለፉት 36,409 ወይም 5.4 በመቶ ነበሩ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በ2017 ዓ/ም ተማሪዎች ስላስመዘገቡት ውጤት ምን አሉ? " ስንጠብቅ ያነበረው ይህንን ውጤት ነው። የመጀመሪያ ሾክ ነበር ከዛ ግን በራሱ ውጤት የሚያልፍ ተማሪ እየመጣ ነው። የፈተና ስርአታችን ሊያመጣው የሚፈልገው ውጤት እየመጣ ነው ትክክለኛው መስመር መሆኑን የተረዳንበት ነው። ይህንን ሃገር የሚጠበቅበት ቦታ ለማድረስ ለእዛ የሚበቃ ትውልድ እያፈራን ነው። በእዚሁ እንዲቀጥል ነው የምንሰራው። 15-20 በመቶ የሚሆን ማክሲመም ተማሪ እንዲያልፍ ነው የምንሰራው ሁለት እና ሦስት አመት ይፈጅብናል ነገር ግን እንደርስበታለን። ዘንድሮም ጥሩ ውጤት ነው የመጣው ነው ነገር ግን የሚያኩራራ አይደለም በሚቀጥሉት ሦስት አመታት የተሻለ ውጤት ይመጣል " ብለዋል። @EthiopianStudentsTM
ውጤት መቼ ይለቀቃል ? " ውጤት እስከ ነገ ቀን 6:00 ሰዓት ይለቀቃል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
ውጤት መቼ ይለቀቃል ? " ውጤት እስከ ነገ ቀን 6:00 ሰዓት ይለቀቃል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
ዘንድሮ የሬሜዲያል /አቅም ማሻሻያ/ ፕሮግራም ይኖራል ? በዘንድሮ ዓመት ሬሜዲያል /የአቅም ማሻሻያ/ ፕሮግራም እንደሚኖር የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል። " ከባለፈው ዓመት መግቢያውን ከፍ በማድረግ ሬሚዳል ይሰጣል " ነው ያሉት። ምን ያህል ተማሪዎች ሬሜዲያል ይገባሉ ? ለሚለው ጥያቄ ሚኒስትሩ " አልወሰንም " ሲሉ መልሰዋል። " ዘንድሮ ሪሚዲያል እድል የሚሰጣቸውን ተማሪዎች ቁጥር አልተወሰነም። 40-50 በመቶ መካከል ይሁን የሚለው ላይ በውይይት ላይ ነው " ብለዋል። ካለፈው አመት ግን መግቢያው ከፍ እንደሚደረግ እና የሚገባው ተማሪ ቁጥርም ቅናሽ እንደሚኖረው ተገልጿል። 📨 @EthiopianStudentsTM
የዘንድሮ ከፍተኛ ውጤት 591 ዶዶላ ኢፋቦሩ ትምህርት ቤት
2384 ተማሪዎች ዘንድሮ ከ 500 በላይ ያመጡ ተማሪዎች ተገኝተዋል
የዘንድሮ ከፍተኛ ውጤት 591 ዶዶላ ኢፋቦሩ ትምህርት ቤት
በኦንላይን ከተፈተኑት ተማሪዎች 21.7 በመቶ አልፈዋል በወረተት የፈተኑት ግን ባለፈውም 4.4 ነበረ አሁንም 4.4 ነው።
ካለፋት ተማሪዎች ተማሪዎች ሴት 18,478 የቀሩት ወንዶች ናቸው
ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች 48,929 ተማሪዎች አልፈዋል። @EthiopianStudentsTM
በሀገር ደረጃ 8.4 በመቶ ተማሪ 50% በላይ በማምጣት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን አልፏል። @EthiopianStudentsTM
ወንዶች 30, 444 ሴቶች 18,478 @EthiopianStudentsTM
አጠቃላይ 48, 929 ተማሪ አልፏል @EthiopianStudentsTM
48,929 ያክሉ ተማሪ ከ50% በላይ አምጥቶ አልፏል ተብሏል።