tgindex
መልካም ምክር

መልካም ምክር

Статистика

…… አስተሳሰብ የሚደክመው መልካም የሆነ ግንዛቤ ከህሊና ሲጠፋ ነው እዚህ ቤት ግን ሁሉንም አንድ ላይ ያገኛሉ …… ሀሳብ አስተያየቶን በ @KING_SGL ላይ ያስቀምጡ

Последний пост
21 апр.
Последнее чтение
13 авг.
Постов за неделю
0
Всего постов
21
Тип
открытый
Язык
ti
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
1 229
0 за 2 дн.
Сутки
0
0,00%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
837
21 постов
Вовлечённость
68,1%
к подписчикам
Постов в день
0,0
всего 21
Упоминаний
0
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
1/48двое суток
1/72трое суток

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • без подписи

  • 11 апр.1 02844

    📜 ለክብራትና ለክቡራን ቤተሰቦቼ እንዲሁም ወዳጆቼ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው (ለፋሲካ በዓል) በሰላም አደረሳችሁ። ይህ ታላቅ በዓል የጨለማ መሸነፍ፣ የብርሃን መውጣት እንዲሁም የሞት ድል መነሳት ተምሳሌት ነው። በዚህ ታላቅ በዓል፡ ቤታችሁ በበረከት፣ ልባችሁ በደስታ፣ ማዕዳችሁ በፍቅር እንዲሞላ እመኛለሁ። ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን - በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን! አሰረ ለሰይጣን - አጋዕዞ ለአዳም! ሰላም - እምይእዜሰ - ኮነ - ፍሥሐ ወሰላም! መልካም በዓል! ከ፡ ፊሊሞና✍

  • እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ! 🕊️✝️ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለል 🙏✨። የክርስቶስ ትንሣኤ ለሁላችንም አዲስ ተስፋን እና ብርሃንን ይዞልን ይምጣ 🌅🕯️።

  • https://www.youtube.com/@Filimona19 የዩቱብ ቻናላችንን በመቀላቀል በቅርብ ለሚጀመረው ስራችን አብሮነታችሁን አሳዩን

  • ተስፋችን እርሱ ክርስቶስ ነው https://youtube.com/watch?v=BCmVoFkr_z4&si=KJPHvnst6Pu9-JlB

  • @KING_SGL

  • 17 февр.85492из FENOT_ARTE

    የዕለቱ ስንቅ “አንተ ሰው የበደለህን ይቅር ሳትል ወደ ጾም አትግባ፡፡ አንተን በበደለህ ሰው ላይ በቁጣ እያለህ የምትጾመው ጾም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርም አይቀበለውም፡፡ ጾምህን በፍቅርና እርሱን ተስፋ በማድረግ በእምነት ካላደረግኸው አንተን ፈጽሞ ሊረዳህ አይችልም፡፡ በጠብ ሆኖና በውስጡ ጠላትነትን አንግሦ የሚጾም ጸዋሚ እግዚአብሔርን ይጠላዋል፤ ከመዳንም ፈጽሞ የራቀ ነው፡፡"     ✨ቅዱስ ኤፍሬም✨ መልካም ዕለት መልካም ጾም ❤️

  • #ቀጭኔ ቀጭኔ ልጇን ለመውለድ አንድ ዓመት ከሁለት ወር በማሕጸን መሸከም ግድ ይላታል ቀጭኔ ከመውለዷ በፊት ልጇን ተሸክማ 14 ወራትን ትቆያለች ምክንያቱም ለቀጭኔ ልጅ ለመውለድ እንደ ሌሎች እንስሳትና አራዊት በሦስት ወር እና በአምስት ወር መቆየት ሳይሆን ከአሥራ አራት ወራት ቆይታ በኋላ ነው ልጇን በዓይኗ ማየት የምትችለው 14 ወራትን ጠብቃ ከምጥና ከብዙ ድካም በኋላ በብዙ ምጥና ስቃይ ልጇን ትወልዳለች ግልገሏን ወልዳም እንደ ሌሎች እንስሳት ጡት ማጥባት ብቻ ሳይሆን ኃይል እንድታገኝ ትንፋሿን ሳይቀር እየመገበች በብዙ እንክብካቤ ማሳደግ ትጀምራለች ነገር ግን አንዳንዴ በቀላሉ መንገድ ሳታስበው  ልጇን ሳታውቅ ትነጠቃለች። 🤔 አራዊቶች የቀጭኔን ልጅ እንዴት እንደሚበሉባት ታውቃላችሁ? ✍️ አራዊት የቀጭኔን ልጅ የሚነጥቋት በጉልበት ሳይሆን የሚነጥቁ በመምሰል ዙሪያዋን እየተጠጉ በማንዣበብ ቀጭኔዋን ያበሳጯታል እንደሚታወቀው ደግሞ ቀጭኔ እግሮቿ ወይም የፊት እግር እንደ እጅ ስለሆነ የፊት እግሮቿ ወይም እጆቿ ረጃጅሞች ናቸው እናም አራዊቶቹ ሲጠጓት ግልገሏን ጉያ ውስጥ ታስገባና አራዊቶቹን ለማጥቃትና ልጆቿን ለመጠበቅ ረጃጅም እግሯን ማንሣት ትጀምራለች እግሮቿን ባነሣች ቁጥርም ሳታውቅ ግሌገሏን በእርግጫ ትመታታለች እርሷ እግሯን የምታነሣው ለአራዊት ቢሆንም የሚያርፈው ግን የግልገሏ ጭንቅላትና አንገት ላይ ነው😓 በዚህ ምክንያት ልጇን ቀጥቅጣ ትገድላትና አራዊቱ ሳይደክሙ ልጇን መብላት ይችላሉሉ 🤔አያሳዝንም? አንዳንድ መቆርቆሮችና መወራጨቶች ጥንቃቄ ከጎደላቸው ልክ እንደ ቀጭኔዎች የራስን ግልገል እየገደሉ ዓይን እያየ ልጅን ለአራዊት ከመቀለብ የዘለለ አይሆንምና እናስተውል! ✍️ለሁሉም አጀንዳ የሐሳብና የአስተያየት እግራችንን እጃችንን ስናነሣ በኃይልና በጉልበት ብቻ አይሁን ✍️ለሐሳብ እግራችንን እጃችንን ስናነሣውና ስንጥለው ማንንም እንዳይጎዳብን እንጠንቀቅ ✍️የብዕርና የሐሳብ እግራችንን እጃችንን በኃይልና በጉልበት ብቻ ሳይሆን በጥንቃቄና በጥበብ እናንሣው ለጠላት ባነሣነው እግራችን የራሳችንን ነገር እንዳንገድል የሐሳብ እጃችንና እግራችን ማንን ማጥቃትና ማንን መጠበቅ እንዳለበት እንምረጥ! https://t.me/Loveerdey

  • "ጸሎት የሌለበት ጾም የሥጋ ድርጊት ነው። ይህም ማለት መንፈሳዊ ሁኔታውንና ጥቅሙን ያጣል ማለት ነው። ጾም ማለት ሥጋን ምግብ በማሳጣት ማገላታት ማለት አይደለም ይህ የጾም አሉታዊ ገጽታ ነውና። አዎንታዊ ገጽታው ለነፍስ የምትመገበውን ምግብ በመስጠት የሚገለጠው ነው። መንፈሳዊ ድርጊቶችን ጸሎትን፣ ተመስጦን፣ መንፈሳዊ ንባባትን፣ መዝሙራትን፣ ዜማዎችን፣ እና ስግደትን የማያካትት ጾም የሚጾሙ ሰዎች ጾማቸው ምንም ጥቅም የማይሰጥ ሸክም ነው የሚሆነው። በእነዚህ ሰዎች ጾምና በሂንዱዎችና በቡዲህስቶች በመናፍቃን ጾም መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው? መንፈስ ቅዱስ በውስጡ የተሳተፈበት መንገድ የት አለ? ጾም ለጸሎት እድሉን ያቀርባል። ምክንያቱም ሆዳችሁ ጠግቦ ከምታቀርቡት አንድ መቶ ጸሎትና ተራራ ከሚያርድ ድምጻችሁ ይልቅ በጾም ውስጥ ሆናችሁ የምታቀርቡት አንድ ጸሎት ተሰሚነት አለው።" አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ

  • አባት ልጁ ከቤት ወጥቶ መኪና እንዳይገጭበት፣ ወድቆ እንዳይሰበርበት፣ ድንገት በአከባቢው የሚያልፉ ከብቶች ገፍተው እንዳይጥሉበት መውጫው በሩን ይዘጋበታል፡፡ ይኼኔ ልጁ በሩ ለምን እንደተዘጋበት አያውቅም፤ ልጅ ነውና፡፡ አባቱ የጠላው መስሎትም ምርር ብሎ ሊያለቅስ ይችላል፡፡ ማልቀስ ብቻ አይደለም፤ ቂምም ሊይዝበት ይችላል፡፡ አባቱ ግን በሩን የዘጋበት ምክንያት ያውቃል፤ ጠልቶት ሳይሆን ይጐዳበታልና ልጁ ቢያለቅስም አይከፍትለትም፡፡ እውነተኛው አባታችን እግዚአብሔርም አንዳንድ ጊዜ የማይጠቅሙን ይልቁንም ክፉኛ ሊጎዱን የሚችሉ በሮችን ይዘጋብናል፡፡ ከእውቀት ከፍለን የምናውቅ ልጆቹ ነንና አባታችን ለምን እንደዘጋብን ለጊዜው አይታወቀንም፤ ብቻ የከለከለን ይመስለናል፡፡ በመሆኑም ቂም ልንይዝበት ልናማርረውም እንችላለን፡፡ እርሱ ግን ይታገሠናል፤ ለእኛ የሚያስባት መልካሚቱን በር እርሱ ያውቃታልና ይከፍትልናል፤ በእኛ እይታ መልካም የምትመስለንን ነገር ግን ክፉይቱን በር ይዘጋብናል፡፡ ቅዱስ አባት ሆይ ስለ ከፈትክልን ብቻ ሳይሆን ስለ ዘጋህብንም በር እናመሰግንሃለን፡፡ አሜን! https://t.me/Loveerdey

  • https://m.me/j/AbZrdj1Haz-8y-hu/

  • 31 янв.1 62622

    ተግሣፅ ዘቅዱስ ኤፍሬም ሕይወትህን በአግባቡ መምራት ትፈልጋለህን? እንግዲያውስ ትሕትናን ተለማመድ፤ ያለ ትሕትና ተገቢውን ሕይወት መምራት አይቻልም፡፡ ሥራህን ሁሉ በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጀምር፡፡ ያን ጊዜ ፍሬዎችህ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይደርሳሉ። ሰው ከትሕትና ከራቀ ከትክክለኛው መንገድ ርቋል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔርን የተወ ሰውን ርኵስ መንፈስ እንደ ሳውል ያስጨንቀዋል። የጠላት ወጥመድ በማር የተቀባ ነው፡፡ በማር ጣዕም የሚማረክ ሰው ሐዘንን ሁሉ በያዘ ወጥመድ ይያዛል። ትሕትናን ውደዱ፤ ያን ጊዜ ከሰይጣን ወጥመድ ውስጥ አትወድቁም፡፡ በትሕትና ክንፍ በበረራችሁ ቁጥር ሁል ጊዜ ከጠላት ወጥመድ በላይ ትሆናላችሁ። ግልፍተኝነት እንደ በሰበሰ ረጅም ዛፍ ነው፤ ቅርጫፎቹ ሁሉ በቀላሉ የሚሰበሩ ናቸው᎓᎓ አንድ ሰው በወጣባቸው ጊዜ ከወጣበት ከፍታ ወዲያውኑ ይወድቃል፡፡ በመልካም ሐሳብ ልቡናው የበራ ሰው ግን ምስጉን ነው፤ ክብሩም ታላቅና ዘላለማዊ ነው። እንግዲህ ራሳችንን ለመቆጣጠር እንጣር ያን ጊዜ ኃጢአታችንን እንረዳለን፡፡ ያን ጊዜም ሁል ጊዜ ራሳችንን ዝቅ እናደርጋለን፤ እንደ እባብ በእብሪት መወጠርን እና ራሳችንን ከፍ ከፍ ከማድረግ እንቆጠባለን፡፡ እንግዲህ ራሳችንን ዝቅ ዝቅ ማድረግን እንውደድ፤ በንጹሕ ልቡና ሆነን ምናልባት የተሰጠንን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በኃጢአት ከማቆሸሽ እንታደግ ይሆናል። መልካም ጸሎት በሳግ እና በዕንባ የታጀበ ነው፤ በተለይ ደግሞ በምሥጢር የሚፈስ ዕንባ፣ በልቡናው ከፍታ ሆኖ የሚጸልይ ጌታውን በፊቱ ያያል። እኛ የምንኖረውና የምንሔደው በእርሱ ፈቃድ ነውና። ልቡናችሁ ከጠነከረ በጌታችን ፊት አልቅሱ እርሱ የዕውቀትን ብርሃን ይገልጥላችኋል፤ ወደ እርሱ የሚወስዳችሁ አዲስ ልብንም ይሰጣችኋል። ንስሓ የገቡና ምሕረት የለመኑ ሰዎች ዕዳቸው ተሰረዘላቸው፤ ነገር ግን ለሠራኸው በደል ምሕረት ስትለምን ወንጀልን እና በደልን፤ በወንድምህም ላይ ቂም መያዝን መተው ይገባሃል። ፍቅር ሳይኖርህ ወደ እግዚአብሔር የምታደርገው ልመና ከተዘጋው በር ውጭ ይቀራል፡፡ የጸሎትን በር የሚከፍት ፍቅር ብቻ ነው፡፡ ወንድምህን ብታስቀይም እግዚአብሐርን ታሳዝናለህ፤ ካንተ ጋር ካለው ከወንድምህ ጋር ሰላምን ከፈጠርህ ግን በሰማይ ካለው ከእግዚአብሔር ጋር ትታረቃለህ፡፡ ወንድምህን በፍቅር ብትቀበለው፣ በደሉንም ይቅር ካልከው እግዚአብሔርን ተቀበልክ፡፡ ስለዚህ በተናደዱ ሰዎች በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅ፤ እንግዲህ የተበሳጩትን በማስደሰት እግዚአብሔርን አስደስተው፣ በታሰሩት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን ጎብኘው፣ በተራቡት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አብላው፤ በታረዙ ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አልብሰው፣ መንገደኛን በመቀበል እግዚአብሔርን በአልጋህ ላይ አስተኛው፤ እግሮቹንም እጠበው፣ በማዕድህም አስቀምጠው፣ እንጀራህንም ከእርሱ ጋር ተካፈል፤ ጽዋህንም ስጠው᎓᎓ እርሱ ታላቅ ፍቅሩን አሳይቶሃልና፤ እርሱ ስለ አንተ ብሎ ትበላው ዘንድ ሥጋውን ቆርሶልሃል፣ ትጠጣው ዘንድም ደሙን አፍስሷል። (ድርሳነ ቅዱስ ኤፍሬም ገጽ 334 - 336  በዲ/ን መዝገቡ ከፍያለው የተተረጎመ)

  • 31 янв.1 06413

    #ጉዞ_ወደ_ፀጋው_ዙፋን አንተ ደካማ ሰው ሆይ ፥ ተነስ! ከተጠመድክበት ስራህ ሸሽተህ ና። ከሚረብሹህ ሃሳቦች ተሸሸግ። የሚጫንህን ጭንቀት ሁሉ አሽቀንጥረው፤ ከምትለፋበት ግብርህ ዞር በል። ለእግዚአብሔር ጥቂት ጊዜ ስጠው። ለአፍታ በእርሱ እረፍት አድርግ። ወደአዕምሮህ ጠሊቅ ስፍራ ግባና ሀሳቦችን ሁሉ ዘግተህ ለእግዚአብሔር ቦታን አዘጋጅ። ፍለጋህን በዚህ አግዝ። በሙሉ ልብህ እግዚአብሔርን "ፊትህን እሻለሁ" በለው።  https://t.me/Loveerdey

  • ➨ አስተውል ፦ ነገ ጎዳና ላይ ስትወጣ እግዚአብሔር ይስጥልኝ ብሎ ለሚያልፍ ሰው እንዲሁም ሲቸገርህ እና ስትወድቅ ፊቱን ለሚያዞርብህ ሰው እነሱ ምን አሉኝ እያልክ ራስህን አታስጨንቅ ፤ ሰው ምንም ብትሰራ መናገሩን አያቆሙም ስለዚህ ሰው ምን ይለኛል ብለህ እየተጨነክ መኖር የሚገባህን ሕይወት ሳትኖር እንዳትሞት ፤ ሞኝ አትሁን ። ተግባባን ጀግኖች ! 🔥❤👍 ቻናሉን_ለወዳጆቻችሁ_ሼር_በማድረግ_እንዲቀላቀሉ_አድርጓቸው። https://t.me/Loveerdey

  • በይ አሚን በይ ልመርቅሸ         😘😘😘 እንደ ፈላው ቆንጆ ቡና☕ ምርጥ ያጋጥምሽ መልከ ቀና 😎 ላግባሸ ብሎ ይላክልሸ ሸምግልና አቦ እፎይ በይ በቃ አግብተሸ💍 ሰልክሸ አርፎ አንችም አርፈሸ ቶሎ ተኝ ዳታ አጥፍተሸ በባልሸ ክንድ ብሎክ ሁነሸ       😁አሚን በይ👍 እስቲ ለ 3 ሴቶች Forward አርጉ እና መልስችውን ስሙ https://t.me/Loveerdey

  • በየ ቀኑ እውነት ተናገር!! ታማኝ ሰው ስለመሆን አለመሆንህ በተጠየቅህ ቁጥር አብዛኛውን ጊዜ "አዎ ነኝ" ነው የምትለው:: ግን እንደገና አስብ! ዛሬን ውሰድ!... "በርግጠኝነት ምን የህል ታማኝ ሆኜ ይሆን" ብለህ ራስህን ጠይቅ:: ጓደኛህ:- "እንዴት ነህ" ብሎ ሲጠይቅህ... በርግጥ ደህና እንደሆንክ ነው የምትነግረው! ተቆጥተህ ቁጣህን ሳትገልፀው ቀርተሃል!! ስለዚህ እውነቱን ለቀኑ ንገር:: እውነት ሌላውን በጣም ይጎደዋል ብለህ ካሰብክ እና የፀጉር አቆራረጥህን እጠላዋለውና ቀይረው ማለት ከፈለክ ለሰውየው አትናገር ለራስህ ያዘው:: ግን እየዋሸህ እንደሆነ እወቅ!! https://t.me/Loveerdey

  • በጭንቀት ጊዜ እንድንረጋጋ የሚያደርጉ 5 መንገዶች ትኩረት የምናደርግበትን ነገር መምረጥ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምን መመጠን፣ የምንሰማውን ዜና መምረጥ ከቅርብ ወዳጆችዎ ጋር የነጋገሩ(ሳይበዛ) ከችግር ይልቅ መፍትሔ ላይ ትኩርት ማድረግ መጽሐፍ በማንብበ አእምርዎን ያፍታቱ https://t.me/Loveerdey

  • 26 янв.1 03042

    ወዳጆቼ አንዲት ጥቂት ነገር ልበላችሁ ድሃው ያበደውን አይቶ ተመስገን አላበድኩም ይላል.. ያበደው ታሞ አልጋ ላይ ሚማቅቀውን አይቶ ተመስገን ይላል.. አልጋላይ ታሞ የተኛዉ የሞተ ሰው ሬሳ አይቶ ተመስገን በሕይወት አለው ይላል። የሞተ ሰው ብቻ ነው የማያመሰግን ስለዝህ ምንም አይነት ሁኔታ ዉስጥ ብትሆኑ ፈገግ ብላችሁአመስግን 😁 https://t.me/Loveerdey

  • አንድ ሳይካትሪስት በ ዉሳኔ እና ድርጊት መሃል ያሉትን ልዩነት ለመግለፅ እንዲህ ሲል ጠየቀ : ለምሳሌ አንድ ዛፍ ላይ ስምንት ወፎች አርፈዋል ከ ስምንቱ ስድስቱ ለመብረር ወሰኑ ስንት ይቀራሉ ብሎ ስጠይቅ ሁሉም አንድ ላይ ሁለት አሉ😊 ፈገግ  አለና አይደለም አላቸው እንዴት ሲሉ አንድ ልጅ ከመሃላቸው ስምንት ነው ሚቀሩት ብሎ መለሰ እንዴት ሲሉት ወፎቹ ለመብረር ወሰኑ እንጂ አልበረሩም አላቸው 👌 https://t.me/Loveerdey

  • 26 янв.62322из fenote_media

    ✨✨✨📚📚📚✨✨✨📚📚📚✨✨✨ ✨✨📚#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ_እንዲህ_አለ✨✨📚 ✨📚📚 "የዚህ ዓለም ኑሮ እንደ እንቅልፍ ነው:: በዚህ ሕይወት የሚሆኑት ሁሉ ሕልም ናቸው:: በሕልምህ ባለጸጋ ብትሆን ምን ጥቅም አለው? በእንቅልፍ ልብ ሆኖ በቅዠት የሚናገር ሰው ስለ ንግግሩ አይፈረድበትም:: እኛ ግን በዚህ የእንቅልፍ ዘመን የምንናገረው ሁሉ የዘላለም ሕይወትን ሊያሳጣን ይችላል" ✨📚📚 "በድህነት እና በረሃብ የሚሰቃዩ ሰዎች እንደ ሠለስቱ ደቂቅ ናቸው:: ከድህነት የበለጠ ምን እሳት አለ? ከረሃብስ የሚበልጥ ምን ነበልባል አለ? ሦስቱ ወጣቶች እሳት ውስጥ ሆነው እንደዘመሩ በመከራ ውስጥ ሆኖ ፈጣሪን የሚያመሰግን ሰው የመከራው እሳት ውኃ ይሆንለታል:: ለድሆች ምጽዋትን የሚሠጥ ሰው ደግሞ ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት የታደገውን የእግዚአብሔር መልአክን ይመስለዋል" ✨📚📚 "አንድ ሰው እኔ ክርስቲያን ነኝ ሲል በአንድ ቃል ዜግነቱንና ቤተሰቡን ሥራውን ጠቅልሎ ተናገረ ማለት ነው:: የሚያምን ሰው ከሰማያዊት ኢየሩሳሌም በቀር ምድራዊ ከተማ የለውም" ✨📚📚 በትንንሽ ነገሮች ማመስገንን ከለመድህ ትንንሽ ነገሮች ብዙ ስለሆኑ ሕይወትህ ምስጋና ይሆናል። ✨✨✨📚📚📚✨✨✨📚📚📚✨✨✨