tgindex
አብርሆት

አብርሆት

Статистика

ሀሳቦች ዛሬ ካለንበት የዳፍንት (የጨለማ) አለም ወደ ነገ ወደ ተሻለው ብርሀን የሚመሩን መርተውም የሚያገናኙን ድልድዬች ናቸው። ፡ ለአስተያየቶ፡ @Bellalsinaa @ThomB23

Последний пост
8 окт. 2024 г.
Последнее чтение
13 авг.
Постов за неделю
0
Всего постов
20
Тип
открытый
Язык
ti
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
2 764
−1 за 2 дн.
Сутки
0
0,00%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
3 249
20 постов
Вовлечённость
117,5%
к подписчикам
Постов в день
0,0
всего 20
Упоминаний
0
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
1/48двое суток
1/72трое суток

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • ሕይወት ለአፍታ አረፍ ብሎ ‘ ምን ልስጣችሁ? ‘ ቢለን፣ የልጅነት ልባችንን የምናስመልስ ብዙዎች ነን።

  • በዚህ አካሄድ አውሮፕላን መግዛት ሳያዋጣ አይቀርም Totally insane! @EliasMeseret

  • ሌላ ሰው "......ሰው መሆን የጊዜ እስረኛ መሆን ነው። 'ጊዜ የዘላለም አሽከር ሲሆን ሰው ደግሞ የጊዜ ባሪያ ነው ። ሰው ጊዜን በደቂቃና በሰዓት : በወራትና በዓመታት ሸንሽኖ : ከግድግዳው ላይ ሰቅሎ በዕጁ ላይ ጠፍሮ ሊገዛው ሊቆጣጠረው ይሞክራል ። ጊዜ ደግሞ ሰውን ከልጅነት ወደ ወጣትነት : ከጉልምስና ወደ እርጅና እያክለፈለፈ ከሞት ደጃፍ ያደርስና መቃብር ይጨምረዋል ። በክረምትና በበጋ : በፀደይና በመጸው እየተመሠለ መልኩን እየቀያየረ ሲመጣና ሲሄድ : ሲዞርና ሲፈራረቅ ... የጊዜ ጉዞ ያዙሪት'ንጅ የወደፊት አይመስልም ። በድል ፈረስ ላይ ተቆናጦ በስኬትና በውድቀት : በቀጠሮና በድንገት : በጥበቃና በጥድፊያ ተጠቅሞ የሠውን ዕጣፈንታ የሚወስን ጊዜ መሆኑን በቀላሉ እንዘነጋለን ። ጊዜን መግዛት ሲባል ራስን እንጅ ጊዜን ማስገዛት አይደለም ። በጊዜ ውስጥ "ትናንት" የትዝታ : "ነገ" ደግሞ የተስፋ ጎተራ ናቸው ።ካመለጠ ትናንት .... ያልመጣ ነገ ይሻላል ። በእጅ ያለ ዛሬ ግን ከሁሉም ይበልጣል ። ዛሬ ሁሌም ያለ እየመሠለ የማይደገም... ተመልሶም የማይመጣ...ላንድ አፍታ ለቅፅበት ታይቶ ዳርቻ ከሌለው የዘላለም ጠፈር ገብቶ የሚሠወር ... በትናንትና በነገ መሀል የተሸነቆረ ነው ። የዛሬ ሚስጢሩና ጉልበቱ ያለው ደግሞ 'አሁን' ላይ ነው ። 'ቅድም' እና 'በሗላ' ግን ያለቦታቸው ዛሬ ውስጥ የተደነቀሩ የትናንትናና የነገ ሽርፍራፊዎች ናቸው። የእድሜ ባለፀጋ የሆኑ ጨቅላ ህፃናት ካልተነካ ቱባ ዕድሜያቸው ላይ ብዙ ዛሬዎች መና ከዋሉ በስተመጨረሻ በፀፀት የተሞላ እርጅና ኩሊ መሆናቸው አይቀርም ። የልጅነት ጨዋታ : የወጣትነት ፍቅር :የጉልምስና ስኬትና የእርጅና ሞገስ በዋናነት የዛሬ ዕድል ፍሬዎች እንጅ የነገ ተስፋ ወይም የትናንት ትዝታ ውጤቶች አይደሉም ። ........." #ሌላ ሰው በዶ/ር ምህረት

  • አንድ ሰዉ ከሀሊል ጂብራን እንዲህ ሲል ጠየቀዉ "ከሰዉ ልጅ በጣም የሚገርመዉ ነገር ምንድነዉ ?" እርሱም እንዲህ አለ ፦ "ሰዎች ልጅነት ይደብራቸዋል ለማድረግ ይቸኩላሉ ከዛ እንደገና ልጅ መሆን ይናፍቃሉ ...ገንዘብ ለመሰብሰብ ጤናቸዉን ያባክናሉ ከዛ ጤናቸዉን ለመመለስ ያወጣሉ ....ስለ ወደፊቱ ይጨነቃሉ የዛሬዉን ይረሳሉ የዛሬዉን አይኖሩም....የወደፊቱን .እንደማይሞቱ ሆነዉ ይኖራሉ። እንዳልኖረ ሆነዉ ይሞታሉ !! #ካህሊል ጅብራን

  • እዚህ ሀገር ስትኖር የታወቁ መስፈርቶች አሉ። አለ አይደል ልክ 2 ሰው የሚይዝ የታክሲ ወንበር ላይ 3ተኛ ሆኖ እንደመቀመጥ አይነት ስሜት አለ አይደል....በሙሉ ቂጥህ መቀመጥ አትችልም ! የመቀመጫህ ግማሹ አካል አየር ላይ ነው። በቃ እዚህ አገር ስትኖር ሙሉ በሙሉ መቀመጫህን አደላድለህ መቀመጥ አትችልም at the same time አይቻልም። ደልቶህ መቀመጥ የምትችለው ወይ ሃገሪቱን ለሚመራው መንግስት ስታሽቃብጥ ነው፤ወይ ደሞ መንግስቱ ራስህ ስትሆን ነው። ……… ሰሞኑን የቲክተኩ ንጉስ ጆን ዳንኤል የሚባለው ልጅ ያልገባው ነገር ቢኖር ይሄ ይመስለኛል። ተቀምጫለሁ ብሎ ነበር የሚያስበው......ግን እሱ መንግስትም አይደለም ፣ መንግስትንም ደግፎ አያሽቃብጥም። (አፈላች : ያው በአንድ ቂጥህ ተቀሙጥ ብለው ለመኑት እንደ ሰፊው ህዝብ : እምቢኝ አሻፈረኝ አለ....ያው ሌላውን ሁሉ የሰማነው ነው የሆነው! ……………......ሲ ያ ሳ ዝ ን..........................

  • "ተራው ሰው እንደ ፖለቲከኞች የሌለውን እውነት ከሬሳችን ላይ፣ ከመውደቃችን ላይ ይለቅማል . . ." #መረቅ

  • ልሞት ስል እ’ምባዬ መጣ ልኖር ስል ሳቄ መጣ ! .... አለ ደራሲው ፂሙን እየነጨ

  • አየህ የምንኖርበት ዓለም ምቹ አይደለችም፡፡ መንፈስህ ቢረጋጋ፣ ገንዘብ ያጥርሃል፡፡ ኪስህ ቢሞላ፣ ጭንቅላትህ ባዶ ይሆናል፡፡ ሃይማኖት ቢኖርህ፣ መንፈሳዊ መሆን ይቸግርሃል፡፡ ቅን ብትሆን፣ ዙሪያህ ያሉ ሰዎች ቅንነትህን ይነግዱበታል፡፡ ክፉ ብትሆን፣ አጠገብህ ሰው አይኖርም፡፡ አይቼ ልለፍ ብትል፣ መዘባበቻ ትሆናለህ፡፡ የመሰለኝን ተናግሬ ልኑር ስትል፣ አጠገብህ የሚኖር የለም፡፡ ራሴን ብቻ ላድምጥ ብትል፣ እብድ ትባላለህ፡፡ ያየሁትን ተናግሬ ልሙት ስትል፣ የምታይበትን አይን ያጠፉልሃል፡፡ ቢሆንም . . . ቢሆንም መኖር ከነብሽቅ ነገሩ ደስ ይላል፡፡ ያለህበትን ኑሮ ተቀበለው፡፡ ራስህን አትዋሽ እውነታውንና ራስህን ተቀብለህ ኑር፡፡ ደሞ ደሞ ከማንም ምንም አትጠብቅ ካልሆነ you are setting yourself up for disappointment. ከልቤ የምነግርህ ነገር ከማንም ምንም አትጠብቅ፡፡ ተስፋህን ሰዎች ላይ የጣልክ ቀን የመቃብር ጉድጓድህን በእጅህ ቆፍርሃል፡፡ ምን መሰለህ እኛ ሰዎች ራስ ወዳድ፣ ስግብግብ፣ ራሳችንን አምላኪዎች ነን፡፡ መጽሀፍ ራሱ "ከመካከላችን አንድም እንኳ ጻድቅ የለም" እንዲል፡፡ ስለዚህም ለማን አባህ ብለህ ትሞታለህ ? ዘር የጨፈጨፉ ደደቦች ደረታቸውን ነፍተው በሚርመሰመሱበት፣ የሰው ላብ እምሽክ ያደረጉ ወደሎች በድሎት በሚኖሩበት፣ የሰው ህልም ያጨለሙ ድንባዣሞች በሚንገዋለሉበት፣ የጠላታቸውን ደም ያፈሰሱ አውሬዎች ደረታቸውን ነፍተው እያየሕ፣ ያመናቸውን ወዳጅ ልብ የሰባበሩ ምሳሌ ቢሶች በሞሉበት ከተማ ለማን አባትህ ብለህ ነው የምትሞተው ? ይልቅ ሙድህ ሲጠፋ ጀለሶችህን ፈልግ፣ በማስተዋል ከራስህ ጋር ተነጋገር፣ ሃይማኖተኛ ከሆንክ ወደ ፈጣሪህ ማደሪያ ገስግስ፣ ጥሩ ሙዚቃ አድምጥ፣ የሚመችህን ነገር አድርግ፣ ከዛሬ የባሱ የመከራ ቀናቶችህን አስብ፡፡ ይሄም ያልፋል፡፡ ደሞም የምንኖርበት ዓለም ለማንም የተመቸ አይደለም፡፡ ለማንስ ተመችታ ታወቅ እና ነው፡፡ ደሞ ዙሪያህ ሺ ደደቦች፣ ጥቂት ጠቢባን እንዳሉ ልብ በል፡፡ ደሞ ደሞ እኮ ብርቱ ወጣት ነህ፡፡ ምናባህ ያልፈሰፍስሃል፡፡ ጠንከር በል፡፡ እቺ በክት ቀን ታልፍና ዛሬን እያነሳህ የምትስቅበት ቀን ይመጣል፡፡ አይዞን ወዳጄ

  • "መጀመሪያ ጉርሻ ምንድን ነው አልኩ? ቀላል ጥያቄ ነበር። መልሱ ግን ሰፊ ነው.... ጉርሻ የሚያቀራርበን ነው። በጉርሻ አይኖቻችን የፈጠሩት ርቀት ይጠፋል። በኋላ እንዳየሁት መጎራረስ ወደ ወሲብ የሚጠጋ ኢትዮጵያዊ ድርጊት ነዉ። በማዕድ ዙሪያ እንዲቀመጥ የተገደደው፣ ተከፋፍሎ ግለሰብ የሆነው ቡድን እና ማህበረሰብ፤ በሚዘረጋው የበላተኛ እጅ ድልድይነት ይቀራረባል። 'አብረን በልተን' ሲባል በውስጡ ከባድ የጉርሻ ይዘት አለ። ጉርሻ አገናኝ አቀራራቢ ድርጊት ነው....... ሌላም ዝርዝር ረድፍ አለው። በርበሬና ሚጥሚጣ በመብላት ሂደት ውስጥ ዜጋ ያልበዋል። በዚህም በእያንዳንዱ እንጀራ ሰበከት ላይ የአብሮ በላተኛችን የወዝ አሻራ ይታተማል። ይህ አስገራሚ የሆነ ግላዊ ማህተም ያለው (እያንዳንዱ ሰው የራሱ ከማንም ግለሰብ የሚለየው የጣት አሻራ ስላለው) የተቀናበረ ድራማ በሚጠጋ 'ማጉረስ' ተብሎ በተሰየመ ድርጊት ማህበራዊ ቅንጅት ይከወናል። በጉርሻ ድርጊት የግል እና የማህበራዊ አላማዎች ሳይጋጬ ይቀርባሉ። (........) ይሄ ሁሉ አማካይ ወደ ሆነው ብልት ወደ አፍ ያመጣናል። ጉርሻ በአፍ መግባት አለበት። የጉርሻ አጉራሽና ጎራሽ የሚረካከቡት ታላቁ ቀዳዳ አፍ ነው። ለሕይወት የሚያስፈልገው ምግብ የሚገባበት፣ ቋንቋ የሚሰራበት ና ሰዎች በራሳቸውና በሌላው መሀል ያለዉን ልዮነት የሚያጠቡት ወይም የሚያሰፉት (ሃሃሃሃ) በአፍ ነው.......... .... አብረው ተቀምጠው ሲበሉ የማይጎራረሱ ሀበሾች ከበዙ ኢትዮጵያ የምትባል እንደሌለች ወይም በመለወጥ ላይ እንዳለች ምልክት ነው" #እቴሜቴ_ሎሚ_ሽታ #አዳም_ረታ

  • ''እዚህች ምድር ላይ ስንኖር በትንሹም ይሁን በትልቁ በየደቂቃው እንለዋወጣለን። ቢታወቀንም ባይታወቀንም ነው እንግዲህ። ቢያንስ ገላችን የበላውን ያንሸራሽራል። ሕዋሳት ይሞታሉ ይወለዳሉ። ቢያንስ አንዲት ፀጉር ትበቅላለች ወይም ትረግፋለች። ፊኛችን ሳያቋረጥ በፈሳሽ ይሞላል። ጊዜው ሲደርስም ይጎላል። ሕይወት እንግዲህ እንዲህ ነው። ይሄ ዑደትና የዝግመት ለውጥ አይበቃንምና ደሞ አንዳንድ ጊዜ እጅግ የሚለውጠን ቀውስ ይመጣብናል። ገላችን፣ አእምሮአችን ይታመማል። እንረበሻለን፣ እንጨነቃለን። ሕይወት እንግዲህ ይሄ ነው። ሰው በግሉ፣ ሕብረተሰብም ተፈጥሮው ይመስሉኛል። ይሄን ደጋግሜ መገንዘቤ፣ ደጋግሜም በነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ ማለፌ ያስተማረኝ ነገር አለ። መረባበሽ ፋይዳ እንደሌለው። የተረጋጋ ታዛቢ፣ የመነኩሴ አመለካከት አለኝ። ከፍ ዝቅ ያለ ነገር ሲያጋጥመኝ በረጉ ዓይኖቼ አያለሁ። በቀዘቀዘ መንፈስና አካል እቀበለዋለሁ። እንደሚለወጥ ስለማውቅ። 'የሚያልፍ ዝናብ አይምታህ ' ሲሉ አዛውንት 'ዝናቡን ፍራው' ማለታቸው አይደለም። ዝናቡን ማወቃቸው ነው። የተወሰነለት ዕድሜ አለው፣ ያውም አጭር ማለታቸው ነው። ሰው ቢያንስ በተስፋ የችግሮቹን ዘመን ያልፋል ማለታቸው ነው። አይመስልህም እንዴ?'' #ይወስዳል_መንገድ_ያመጣል_መንገድ @abrhott abrhott @abrhott

  • ዛሬ ላይ ርካሽ ያልናቸው : ነገ ላይ ውድ ናቸው !

  • " አቧራ የጠገበን ምንጣፍ በዱላ የምትመታው አቧራውን ለማራገፍ እንጂ ምንጣፉን ለመጉዳት አይደለም ። የሰውን ድክመት የምትነግረውም ስህተቱን እንዲያርም እንጂ ሰውዬም በስራው ተስፋ እንዲቆርጥ አይደለም ። " / ቀደምት የአገራችን አበው ፍልስፍና / @abrhott @abrhott

  • ማቴሪያሊዝም ፣ አይዲያሊዝም እና ኦብጀክቲቪዝም... ክፍል ፪ ፨፨፨ ... የአዕምሮ ስራ ደግሞ ማወቅ ብቻ ነው ። ተፈጥሮን መፍጠር ፣ መቀየር ፣ መለወጥ አይችልም ። ከውሃ ጋር ሲገናኝ የማይዝግ ብረትን የመፍጠር ፣ ማለትም የብረትን ተፈጥሮ የመቀየር ችሎታ የለውም - አዕምሮ ። ዘይት ከውሃ ጋር የማይቀላቀል መሆኑን ፣ ዘይት ብረት ላይ ከፈሰሰ የብረቱን ዙርያ እንደሚሸፍን ፣ ውሃና ብረት እንዳይገናኝ እንደሚንከባለል በማወቅ ነው ፣ ዝገትን መከላከል የሚችለው ። ሰው የማወቅ አቅም እንዳለው ተገንዝቦ አቅሙን ከተጠቀመ ፣ የአቶም ክፍሎችን ማጥናት ፣ ፕላኔቶችንና ኮከቦችን መፈተሽ ፣ የአንጎልና የልብ ቀዶ ጥገና ማካሄድ ፣ ግድቦችንና ድልድዮችን መሥራት ፣ አውሮፕላንና ባቡር መፈብረክ ፣ ኢንተርኔት መዘርጋት ፣ የተትረፈረፈ እህል ማምረት ሰማይ ጠቀስ ፎቆችን መገንባትና ሰብዓዊ መብትን የሚያስከብር ሕገ መንግስትን ማርቀቅ ይችላል ። ፧ በአጠቃላይ ተፈጥሮን ለሕይወቱ እንዲጠቅም አድርጎ ለማቀናጀት ( Rearrange ማድረግ ) ብቃት ያለው ታላቅ ጀግና ተፈጥሮ ነው - ሰው ። ለዚህ ሶስት ነገሮች ያስፈልጋሉ ፦ ፩ኛ- የአዕምሮ ችሎታ ማወቅ እንጂ መፍጠር አለመሆኑን መገንዘብ ። ፪ኛ- ማወቅና ዕውቀትን መተግበር በአውቶማቲክ የሚሰሩ ሳይሆን በእያንዳንዱ ሰው የግል ምርጫ (Volition) የሚገኙ መሆናቸውን መረዳት ፫ኛ- ሕይወቱን ለመጥቀም ከፈለገ ፣ ማወቅና መሥራት የእያንዳንዱ ሰው የሞራል ኃላፊነት እንደሆነ መቀበል ናቸው ። ፧ እነዚህን መፃረር ማለት በአይዲያሊዝም እና በማቴሪያሊዝም አስተሳሰብ ራስን ማጥፋት ነው ። በአይዲያሊዝምና በማቴሪያሊዝም መካከል ካለው ልዩነት ይበልጥ አንድነታቸው የጎላ ነው ትላለች - አየን ራንድ ። እውነትን ፣ ትክክልን እና መልካምን ለይቶ የማወቅ አቅምና ኃላፊነት የአዕምሮ መሆኑን ይቃረናሉና ። የሁለቱም ፍልስፍናዎች ፣ በአብዛኛው ማሰብ እና የማሰብ ኃላፊነት ከመሸሽ የሚመጡ የአዕምሮና የስብዕና ዝቅጠቶች ናቸው ፣ እንደ አየን ራንድ ፍልስፍና ። በማቴሪያሊዝም ፍልስፍና ፣ 'የሰው ሃሳብና ድርጊት ልክ እንደ ሮቦት በአካባቢው በሚገኙ ነገሮች ፕሮግራም የሚደረግ ነው ፤ ምርጫ የለውም ' ሲባል እንዲሁ አየር ላይ የተንጠለጠለና ኑሮን የማይነካ ከመሰላችሁ የፍልስፍናው ሰለባ ከመሆን ማምለጥ አይቻልም ። ፧ በሬድዮ እንደምንሰማው ፣ ሴቶች በወንዶች የሚደፈሩት ስሜት የሚያነሳሳ አጭር ቀሚስ ስልሚለብሱ ነው እንጂ በድርጊቱ ፈጻሚዎች ብልሹ ሥነ ምግባር ሳቢያ የሚከሰት አይደለም ፣.. ወንጀል የፈጸመው ጎረምሳ ፣ በአጭር ቀሚስና በሥራ አጥነት ፣ በመደቡ ወይዛዝርት በገበሬነት ተሳብቦለት ከተጠያቂነት ነፃ ይወጣል ። ከወንጀል የራቀው ሰውዬ ደግሞ በዘሩ ፣ በቀለሙ ፣ በሀብቱ ፣ ( ቡርዣና ንዑስ ከበርቴ ፣ ጥገኛ ነጋዴ እየተባለ ) ተመካኝቶ ተከሳሽ ይሆናል ። ሰው ለራሱ ሃሳብና ድርጊት ተጠያቂ አይደለም ተብሏል ። በቀኝ ጎንህ ካልተነሳህ ትነጫነጫለህ ፣ መዳፍህ ካሳከከህ ሰዎች ገንዘብ ይሰጡሃል ፤ ዓይንህ ከተርገበገበ ለብዙ ጊዜ የተለየህ ሰው ይመጣል ፣ ሰማዩ ከቀላ ጦርነት ይነሳል ፣ ሚዳቆ መንገድህን ካቋረጠች አደጋ ይደርስብሃል..ይሄ ሁሉ ፣ የእያንዳንዱ ሰው ሃሳብና ድርጊት ከአዕምሮ ነጻ ምርጫ የሚመነጭ መሆኑን ከመካድና ግዑዝ ነገሮችን ወሳኝ ከማድረግ የሚመጣ አስተሳሰብ ነው ። ፧ በእርግጥ ማቴሪያሊስቶች በራሳቸው እግር ራሳቸውን የሚጠልፉ ናቸው ። ማቴሪያሊስቱ 'ሊበራል ዲሞክራሲ በኢንዱትሪ ለገፉ ሀገሮች ብቻ የሚስማማ ነው ፣ ለኢትየያ አይሆንም ።... ይቀጥላል... ስንት ሰው በንባብ እየተከተለን ነው? ( 👍 ) @abrhott @abrhott @abrhott

  • ማቴሪያሊዝም ፣ አይዲያሊዝም እና ኦብጀክቲቪዝም... ክፍል ፩ ፨፨፨ ማቴሪያሊስቶች ምን ይላሉ...? ሰው ልክ እንደ ሮቦት(Robot) ነው ። ሰው ሲባል 'ሃሳቡ' ና ድርጊቱ በግዑዝ ነገሮች የሚወሰን ስለሆነ የመምረጥ አቅም ( Volition - free will ) የሌለው ፍጥረት ነው ይላሉ ማቴሪያሊስቶች ። ሰው አይቶ፣ አስቦ፣ መዝኖ እውነተኛ ድምዳሜና ቲዎሪ ላይ የሚደርስ ይመስለዋል እንጂ፣ ሁሉም ነገሩ ድርጊቱ ጭምር ከቁጥጥሩ ውጪ ነው ። በአካባቢው የሚገኙ ነገሮች ፕሮግራም ወይም ኮንዲሽን ያደርጉታል ። አዕምሮን መጠቀምና ማወቅ ብሎ ነገር የለም ። መነጋገርም በምክንያታዊ ትንታኔ መግባባትም አይችልም ሁሉም ሰው ኮንዲሽን በተደረገው መሰረት ስለሚንቀሳቀስ ። ፧ አይዲያሊስቶች ምን ይላሉ...? በአይዲያሊዝም ፍልስፍና መሰረት በአካባቢያችን የምናያቸውና የምንዳስሳቸው ነገሮች በሙሉ በአዕምሮ ወይም በሃሳብ የተፈጠሩ ናቸው ። 'ሃብት በሃብት አደርግሃለሁ' የሚል ጠንቋይ ከዚህ ወገን ይመደባል ። እሱ ስላሰበ ስለተመኘ ወይም ስለፈለገ ብቻ በአውቶማቲክ ቪላው፣ መኪናው፣ ገንዘብ ከች ይላል ። ከፈለገም ያጠፋቸዋል ሊያደኸይህ ሲፈልግ ። ግዑዝ ነገሮች እንደፈለገው ከድንጋይ ወደ ዳቦ ከብረት ወደ ወርቅ የሚቀይራቸው የአዕምሮ ተገዥ ናቸው ። በእሱ ሃሳብ አማካኝነት ይፈጠራሉ፣ ይጠፋሉ ። ስለዚህ አዕምሮን መጠቀም፣ ማሰብና ማወቅ አያስፈልግም ነገሮች በምኞት የሚቀየሩ ከሆኑና ቋሚ ተፈጥሮ ከሌላቸው ማወቅ ትርጉም የለውምና ። ፧ ኦብጀክቲቪስቶች ምን ይላሉ...? አሜሪካዊቷ ፈላስፋ አየን ራንድ ከላይ የተነሱትን የሁለቱን ፍልስፍናዎች ስህተት እና የሚያስከትሉትን አደጋ በመተንተን ትክክለኛ ፍልስፍና አቅርባለች ። ያም ኦብጀክቲቪዝም ይባላል ።..በዚህ እሳቤ ውስጥስ ምን አይነት እይታዎች አሉ...? " ተፈጥሮ በማንም የአዕምሮ ምኞት አይለወጥም - አይዲያሊስቶች እንደሚሉት ሳይሆን ። አዕምሮ አካባቢውን በማስተዋል ተፈጥሮአቸውን የማወቅ አቅም አለው፤ አቅሙን የመጠቀምና ያለመጠቀም ምርጫም የራሱ ብቻ ነው ። ነፃ ምርጫ (ሶሊሽን) አለው - ማቴሪያሊስቶች እንደሚሉት ሮቦት አይደለም ። ፧ የሚኖረን ነገር ሁሉ(Existence)፣ የራሱ የሆነ የማይቀየር ተፈጥሮ(Identity) ነው ። ብረት ሁልጊዜ ብረት ነው - ከውሃ ጋር ሲገናኝ ይዝጋል ፣ በተወሰነ መጠን ካርቦንና ነሃስ ሲጨመርበት ይጠነክራል፣ 1500 ዲግሪ ሴንቲ ግራድ በሆነ ሙቀት ይቀልጣል ፤ ኃይል ሲጫነው ወደ ቆርቆሮነት ይለወጣል ። ወይም ሽቦ ይሆናል ወዘተ... ። ብረት እስካለ ድረስ ዝንተ ዓለም ተፈጥሮው ይኸው ነው ። እንጨት ፣ ውሃ ፣ ድንጋይ ፣ እስካሉ ድረስ የማይቀየሩ ተፈጥሮ ናቸው - በምኞት የማይቀየሩ ባህርያት ። To be is to be something ትለዋለች አይን ራንድ ። ሲገለበጥ ተፈጥሮ የሌለው ተፈጥሮ የለም እንደማለት ይሆናል ። መሆን ማለት ፣ የሆነ ነገር መሆን ነው ። የአዕምሮ ስራ ደግሞ ማወቅ ብቻ ነው ። ተፈጥሮን መፍጠር ፣ መቀየር ፣ መለወጥ አይችልም ።... ይቀጥላል በንባብ እየተከተሉን ነው እንግዲያውስ ( 👍 ) @abrhott @abrhott @abrhott

  • Two traps you need to avoid: Caring what they think Thinking that they care

  • የፈላስፋው ጥመት... ፨፨፨ የጠርጣሪነት ፍልስፍና (scepticism) ጀማሪ እንደሆነ የሚታመንለት የጥንቱ ፈላስፋ ፊሮ አንድ ቀን ጥበብን ያካፍላቸው ዘንድ ወደጋበዙት ሰዎች በማለዳ አመራ። በቦታው ሲደርስ ቁጥሩ እጅግ የበዛ ሰው ተሰብስቦ ሲጠብቀው ተመለከተና ወደተዘጋጀለት የከፍታ ቦታ በዕርጋታ ወጥቶ ቆመ። ፊሮ ትምህርቱን ከመጀመሩ በፊት ጥያቄ ወረወረ፦ <<ዛሬ እዚህ የተሰበሰባችሁት ከእኔ ልትማሩ ነው?>> ተማሪዎቹ በአንድ ድምፅ አዎንታቸውን ገለፁ። <<እንግዲያውስ ስለምን እንደማስተምር ታውቃላችሁ ማለት ነዋ?>> አለ ፊሮ። <<ኧረ ምንም አናውቅም>> አሉ ተማሪዎቹ አሁንም በአንድ ድምፅ። <<ስለምን እንደማስተምር ካላወቃችሁማ ዝም ብዬ ማውራት አልፈልግም>> አለና ከመድረኩ ወርዶ ወደ ቤቱ አመራ። በነጋታው አሁንም በዚያው ቦታ ህዝቡ ተሰብስቦ ይጠብቀው ጀመር። ፊሮም መጣና በእርጋታ ወደ መድረኩ ወጣ። <<ዛሬስ ስለምን እንደማስተምር አውቃችኋልና?>> በማለት ጠየቀ። የተሰበሰበው ህዝብ በአንድ ቃል አዎንታቸውን ገለፁ። ፊሮም <<ካወቃችሁትማ ወደ ቤቴ ልሂድ....>> በማለት ከከፍታው ላይ ወረደ። በሚቀጥለው ቀን ወደ ቦታው ሲያመራ አሁንም ህዝቡ ተሰብስቦ እየጠበቀው ነው። የዚያን ቀን ግን ህዝቡ መልሳቸውን አዘጋጅተው ነበር የጠበቁት። ፊሮም ወደ ከፍታው ከወጣ በኋላ፦<<ዛሬስ ስለምን እንደማስተምር ታውቃላችሁ..?>> አለ። ህዝቡም፦<<ግማሾቻችን እናውቃለን፤ግማሾቻችን ደግሞ አናውቅም...>> አሉት። ፊሮም፦<<እንግዲያውስ ግማሾቻችሁ የምታውቁት፤ ለግማሾቹ የማያውቁት ንገሯቸው!..>> ምንጭ ፦ ጥበብ ከጲላጦስ ፨፨፨ ፨ አሁን በእናንተ አረዳድ በፈላስፋው ላይ ነው ወይስ በተከታዮቹ ላይ ነው የሚፈረደው...?

  • በረራ ሃሳብ... #ዛሬ በማለዳ ወደስራ ለመሄድ ስዋከብ....ታክሲ 🤷‍♂እንደለመድነው ይሆናል። በስንት ጥበቃና የለሆሳስ ፀሎት አንድ ታክሲ መጣችና ጫነችን። የተሳፈርነው "ኡፎይ" ስንል ቀሪው ተጠባባቂ የኛኑ ( ያልተቋረጠ ጥበቃና ታክሲ እንዲመጣ በልቡ ለአምላኩ ይፀልያል) እኛ ግን እሱን ሀሳብ እዛው ታክሲው ተራ ላይ አራግፈን በሌላ ባህረ ሀሳብ ተጉዘን ቀጣዩን ተግባር ማብሰልሰል ጀምረናል.... ስለስራ ስለትዳር ስለልጆች ስለራስ አስተዳደር... ስለወደፊት... እረ እንደውም ምን ማሰብ ራሱ እንዳለበት የማያውቅም ሊኖር ይችላል። ወደ ጉዳዬ ስመለስ.... ብቻ ግን እኔና መሠሎቼ ታክሲ ላይ ነን.... እኔ እየናወዝኩ ነው። ...የሀሳብ ማዕበል እያናወጠን ጀልባዬ ላለመስመጥ እየተፍገመገመች.... #በሀሳብ ከአንዱ ወደሌላው ተላትሜ ስመላለስ እንደድንገት ታክሲው ቆመና ከአቅሙ በላይ ሰው መጫን ጀመረ.... ውስጥ ያለነው በሙሉ ማጉረምረም ጀመርን። ረዳቱ "ምቾተቢስ" መሆናችን ቢገባው... #"እስቲ ጠጋ ጠጋ በሉ፣ንፋስ እንዳይገባ፣ ጠጋ ጠጋ በሉ በመሀላችን ንፋስ ካለ ብርድ ይገባል)! የሚል ለሰሚ የሚቀል ትንሽም ፈገግ የሚያደርግ! ለአዳማጭ ግን ከዛ የላቀ ሀሳብና መልዕክትን አያየሰዞ ወደስራው ተመለሰ። 🤔 እውነት አይመስላችሁም!? ምናለ ብንጠጋጋ፣ በታክሲ ብቻ አይደለም። በሁሉ ነገራችን ምናለ ጠጋ ጠጋ ብንባባል! ቢያንስኮ ርቀን ከምናስተውለው የተሻለ እይታን ቀረብ ስንል ምልከታን ያጠራል። አለንህ አለውልሽ አለውልህ !!! ብንባባል ምናለ? ደልቶ ባይደላንም ሌላው እንዲኖር እድልም በመጠጋጋት ቦታም ብንሰጥ ምናለ? 🤔ባለመጠጋታችን በመሐል ክፍተት አለ። ያ ክፍተት መጥፎ ሆኖ አይደለም ግን ሌላውን የሚያኖር ከሆነ ምናለ ብንጠቀምበት!? ፍቅራችን ቢደረጅ ብንተሳሰብ ..... ክፍተቱን በመሀላችን ለመጥፎ የሚጠቀም በሽ ነው። ለመከፋፈል ለመለያየት ለመገነጣጠል ....ብዙ ለብዙ ሚጠቀምበት ሞልቷል። ቀድመን ጠጋ በማለት በፍቅር ተዋቅረን እጅ ለጅ ተያይዘን መንገዱን እንዝጋበትስቲ 💕 # አስተውለን ሳይሆን ተነግሮን እንኳ የማንረዳበት(የማንረዳዳበት) የማንደማመጥበት ጊዜ ላይ ነን! ይሄን ነው የተረዳውት። እናስተውል!!! #የዛሬው መልእክት "እግዜር ያፈቅረን ዘንዳ እንፋቀር ..፣ በመሀላችን ክፍተትን እናጥብብ" ነው "ጠጋ ጠጋ በሉ ፣ በመሐላችን ክፍተት ካለ ብርድ ይገባል"....

  • #ትዝብት 2 ያለኹት ሸራተን ነው(Office Bar) ለምን : እንዴት የሚለውን ጥያቄ ተውት! ብቻ... Dawit Tsige በሚያምር ድምፁ "እትቱ በረደኝ" እያለ ነው ጎርደን ታዟል : እየተጨበሰ ነው እና በፍራቻ ብዛት ደፋ ያለ አንገቴን በጨብሲ ምክንያት ቀና አርጌ መላ ገባውን ስቃኘው... ወዝ ያስጠላችኋል ወገን! ከእኔ ቀጥሎ ዘፋኙ ዳዊት ፅጌ ብቻ ነው ሌጣ ድሃ🫤 (በርግጥ እሱ የድምጥ ሃብታም ነው : እኔ አለኹ ባዶ ቂጤን የምወዛወዝ) ወገን ሃብታም በሽሽ ነው ስላችኹ😊

  • #ትዝብት አንድ የከተማ ህዝብ ማመላለሻ ሃይገር የተባለው ባስ ድንገት ፍሬን ይበጥስና : በሹፌሩ ግሩም ጥረት ብዙ ንብረት እና ሰው ላይ ጉዳት ሳያደርስ ከግምብ ጋር ተጋጭቶ ቆመ! ባጋጣሚ የአንድ እግረኛ የሆነ ሰው ላይ ከመኪናው ለማምለጥ እዮረጠ ሳለ አንድኛው እግሩ ላይ ጉዳት ደርሶበት ተኝቷል። እና በዚህ ማሀል የብዙ የሰው ትርምሶች የወደቀውን ሰው ብዙ የሰው አይኖች በትዝብት ማየት ጀመሩ። እስካሁን ወደ ሆስፒታል እንዳልተወሰደ እያሰባችኹ😐 እንደምንም ተጨቃጭቀን ወደ ሆስፒታል ለመውሰድ እየተዘጋጀን እያለ...ጀርባዬን የሆነ ወፈር ያለ እጅ ቸብ ቸብ አረገኝ። ዞር ብዬ "ሽቅብ እያየኹት ምንድን ነው ስለው...ቅንድቡን ወደ ግንባሩ ከፍ እያረገ በጎረነነ ድምፅ "ጀለሴ እሱ ብቻ ነው የተጎዳው " አለኝ አይኑን ወደ ልጁ እያጉረጠረጠ! (አንድ ብቻ መሆኑ አንሶበት መሆኑ ነው እንግዲህ: ሞትን እና ጉዳት የመለማመድ ጉዳቱ ይሄ አይደል) አየኹት☹️... አየኝ🫤 ተ በ ዳ ብዬ አገጩን " ልለው አስቤ ሁለት ሰው ሆስፒታል ይዞ መሄድ ከጥቅሙ ጉዳቱ ስለሚብስ ተውኩት!(ደሞ እኮ ረጅም እና ወፍራም ነው) .....

  • ▶ የ ጅ ራ ፍ ን ቅ ሳ ት ━━━━━━ ✍ ኤፍሬም ስዩም 🎧 @abrhott

አብርሆት — tgindex