tgindex
የኢትዮጵያ ስነ-ፁሑፍ Ethiopian literature

የኢትዮጵያ ስነ-ፁሑፍ Ethiopian literature

Статистика

አሀዱ ብለን ከጀምበር መውጣት ጋር ፈንጥቀን፤ አብረን የህይወት ስንክሳርን ልንፈትሽ የሀገር ሁነቶችን በስነ-ተውህቦ ከሽነን ልንዳስስ ፦ ስነ-ፁሑፍን፣ ታሪካችን፣ አሁናው ክስተቶችን፣ የወንጀል ተረኮች፣ ገድሎች፣ ስነ-ግጥሞች፣ የጀብድ ታሪኮችን በፁሁፍ ከትበንና በስነምስል አዋህደን እናደርሳለን። የመንገዳችን ተካፋይ የሀሳባችን ተጋሪ ትሆኑ ዘንድ በክብር ጋበዝን።

Последний пост
29 июл.
Последнее чтение
14 авг.
Постов за неделю
0
Всего постов
20
Тип
открытый
Язык
ti
Категория
Новости и СМИ (по похожим)
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
2 023
−3 за 1 дн.
Сутки
−1
−0,05%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
728
20 постов
Вовлечённость
36,0%
к подписчикам
Постов в день
0,0
всего 20
Упоминаний
0
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
173
1/48двое суток
198
1/72трое суток
213

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • 📌 ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፤ የሀገር ፍቅር እና የእምነት ጽናት ተምሳሌት! ከዛሬ 90 ዓመት በፊት (ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም) በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ፈጽሞ የማይረሳ ታላቅ ታሪክ ተፈጸመ። አንጋፋው የሃይማኖት አባት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ለሀገራቸው ነፃነትና ለእምነታቸው ያላቸውን ጽናት በደማቸው ያረጋገጡበት ታሪካዊ ዕለት ነው! ·         ታሪካዊ አመጣጥ፦ በ1921 ዓ.ም በግብፁ ፓትሪያርክ ጵጵስና ከተቀቡት አራት የመጀመሪያዎቹ ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት አንዱ ሲሆኑ፣ የምስራቅ ኢትዮጵያ (የወሎ) ጳጳስ ሆነው አገልግለዋል። ·         የአርበኝነት ተጋድሎ፦ ፋሺስት ጣሊያን ሀገራችንን በወረረ ጊዜ ከወራሪው ጎን ሳይሆን ከአርበኞች ጋር በመሆን ጦሩን ይባርኩ እና ያበረቱ ነበር። ·         ጽናት እና ተጋድሎ፦ የፋሺስት ጣሊያን እንደራሴ የነበረው ሮዶልፎ ግራዚያኒ አቡነ ጴጥሮስን አስይዞ "ህዝቡ ለጣሊያን እንዲገዛ አስተምር" ቢላቸውም እሳቸው ግን ለሞት አልበረከኩም። ·         ታሪካዊው ውግዘት፦ ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም አደባባይ ላይ፦ "የኢትዮጵያ ህዝብ ለጠላት እንዳይገዛ አውግዣለሁ፤ የኢትዮጵያ መሬትም ጠላትን እንዳትቀበል የተረገመች ትሁን!" በማለት የጀግንነት እና የሀገር ፍቅር አቋማቸውን በግልጽ አበሰሩ። ወዲያውኑም በፋሺስት ወታደሮች በጥይት ተደብድበው የሰማዕትነትን ጽዋ ጠጡ። ዛሬ በአዲስ አበባ ፒያሳ ላይ የቆመው ሐውልታቸው የዚህ ታላቅ ጽናት እና የህይወት መስዋዕትነት ህያው ምስክር ነው። የሰማዕቱ አባታችን በረከት እና የሀገር ፍቅር አርአያነት ከሁላችን ጋር ይሁን! 🇪🇹 #አቡነጴጥሮስ #የኢትዮጵያታሪክ #ሰማዕትነት #የሀገርፍቅር #AbunePetros #EthiopianHistory https://youtu.be/puRvWhQXM2Y

  • "አድዋ - የጥቁር ሕዝብ የነፃነት ፋና!" 🇪🇹🔥 ጣሊያን በዘመናዊ መሣሪያ ታጥቃ ስትመጣ፣ አባቶቻችን በምን ዓይነት ስልት አሸነፏት? ጀግንነታቸውስ ምን ይመስል ነበር? ከሚኒሊክና ጣይቱ ጀርባ ሆነው ዓለምን ያስደመመ ታሪክ የሠሩትን 12ቱን የጦር ጀነራሎች ታሪክ ይዘንላችሁ መጥተናል። ከራስ አሉላ እስከ ፊታውራሪ ገበየሁ... እነዚህ ጀግኖች ለዛሬይቱ ኢትዮጵያ የከፈሉት መስዋዕትነት ሊረሳ አይገባም! ሙሉ ቪዲዮውን አሁኑኑ ይመልከቱ 👇 https://youtu.be/cuUuDdc_-6E ክብር ለጀግኖች አባቶቻችን! ✊💚💛❤️

  • ባሕር የሌላት ሀገር የባሕር ኃይል? | የኢትዮጵያ አስገራሚው የባሕር ኃይል ታሪክ https://youtu.be/beEJ6blBsFM

  • видео или голосовое, без подписи

  • የካንት ተቺዎች የስርዓቱን ጥንካሬ እና ደካማነት ያጋልጣሉ። የሱ ፍልስፍና ሳይንስን፣ ሞራልን እና ውበትን ያስጠብቃል ግን የመጨረሻውን እውነታ ሊታወቅ የማይችል አድርጎ በመተው ዋጋ ነው። የሱ ሥነ-ምግባር ክብርን በራስ ገዝነት ላይ መሠረት ያደረገ ቢሆንም ግን የግትርነት አደጋ ያመጣል። ምድቦቹ ልምድን ያብራራሉ ግን ታሪክ እና ባህልን ሊዘነጉ ይችላሉ። የጀመረው ክርክር አልተዘጋም፤ ምክንያትን፣ ልምድን፣ ነፃነትንና እውነትን ሚዛናዊ ለማድረግ የቀጠለው ትግል አካል ነው። ✓ ካንት በዛሬው ዓለም ውስጥ ያለው ዋጋ የካንት ፍልስፍና እንደ ታሪካዊ ቅርስ ሳይሆን በዘመናዊ አጣብቂኞች ውስጥ ለማሰብ እንደ ማዕቀፍ ህያው ሆኖ ይኖራል። ለራስገዝነት፣ ገደብ እና ክብር ያለው ፅኑ ፍላጎት ሳይንስን፣ ፖለቲካን እና ባህልን እንዴት እንደምንቀርባቸው መቅረጹን ቀጥሏል። 1. ሳይንስ እና የእውቀት ገደቦች በውሂብ እና አልጎሪዝም ዘመን የካንት የምክንያት ገደቦች ማስጠንቀቂያ ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ጠቃሚ ነው። ፌኖሜናዎችን በሚያስደንቅ ትክክለኛነት ሞዴል ማድረግ እንችላለን ነገር ግን አሁንም ሳይንስ ሊመልስ ያልቻላቸው ጥያቄዎች ያጋጥሙናል፡ ንቃተ ህሊና ምንድን ነው? ነፃነት ምንድን ነው? የሰው ልጅ ሕይወት ዋጋ ምንድን ነው? ካንት ሁሉም እውነቶች ተጨባጭ እንዳልሆኑ እና የእውቀት ሁኔታዎች መገመት ሳይሆን መፈተሽ እንዳለባቸው ያስታውሰናል። 2. ስነምግባር እና የሰው ልጅ ክብር በካንት የሞራል ፍልስፍና ክብር መሠረት ያደረገው በራስገዝነት ላይ ነው። ይህ መርህ የሰብአዊ መብት ንግግሮችን፣ የህግ ማዕቀፎችን እና የዲሞክራሲ ሃሳቦችን መሰረት ያደረገ ነው። ስለፍትህ፣ እኩልነት እና ነፃነት በሚደረጉ ክርክሮች ላይ የካንት ካቲጎሪካል ኢምፔራቲቭ የማዕዘን ድንጋይ ሆኖ ይቆያል፡ እያንዳንዱን ሰው እንደ ፍጻሜ እንጂ እንደ አማራጭ ብቻ አይመልከት። 3. ፖለቲካ እና ተጠያቂነት ካንት በምክንያት እና ራስ ገዝነት ላይ ያለው አጽንዖት አዉቶሪታሪያኒዝምን እና ፕሉላሪዝምን ይፈታተናል። ሕጎች ሁለንተናዊ እንዲሆኑ፣ ሃይል እንዲጸድቅ እና ዜጎች እንደ ምክንያታዊ አባል እንዲታዩ ይጠይቃል። በኢትዮጵያም ሆነ በሌላው ዓለም ይህ መርህ ለተጠያቂነትና ግልጽነት ቦታ በመስጠት እና ምክንያታዊ ክርክርን በማክበር የታዛዥነት እና ተዋረድ ትውፊቶችን ይፈትናል። 4. ባህል እና ውበት ካንት በአስቴቲክስ ላይ ያቀረበው ነጸብራቅ በኪነጥበብ እና ስነ-ጽሁፍ ላይ ተጽእኖ ማሳደሩን ቀጥሏል። የውበት ፍርድ ግላዊ ሆኖም ግን ሁለንተናዊነትን ይፈልጋል የሚለው ሃሳቡ ኪነጥበብ ለምን የጋራ ነጸብራቅን እየጋበዘ እንዴት በጥልቁ እንደሚያነካን ያብራራል። በተበታተኑ ማንነቶች እና ተፎካካሪ ትረካዎች ዓለም ውስጥ የካንት ውበት ወደ አንጻራዊነት ሳይወድቁ ስለ'ጋራ ስሜት ለማሰብ መንገድ ይሰጣል። ዛሬ ባለው ዓለም ውስጥ ካንት ቅርስ ሳይሆን ፈተና ነው። በሂሳዊ መንገድ እንድናስብ፣ ገደቦችን እንድናከብር እና ነጻነታችን በምክንያት ላይ የተመሰረተ እንዲሆን ይጠይቀናል። ፍልስፍናው ቀላል መልስ አይሰጥም፤ ነገር ግን ስለ እውቀት፣ ሞራላዊነት እና የሰው ልጅ ሁናቴ የተሻሉ ጥያቄዎችን ለመጠየቅ ማዕቀፍ ያቀርባል። ✓ ማጠቃለያ የካንት ሂሳዊ ፍልስፍና በሰው ልጅ አስተሳሰብ ውስጥ ካሉት ታላላቅ የለውጥ ነጥቦች አንዱ ሆኖ ቆሟል። ዝም ብሎ ከራሽናሊዝም እና ከኢምፔሪሲዝም መካከል አልመረጠም፤ እውቀት የሚመነጨው ከሁለቱ አስፈላጊ መስተጋብር መሆኑን በማሳየት ክርክሩን ቀይሮታል። ልምድ ጥሬ ዕቃውን ያቀርባል ምክንያት ደግሞ ቅርጹን ያቀርባል። ሳይንስ የሚቻል የሆነው አእምሮ በራሱ የሚያጋጥመንን ዓለም ስለሚያዋቅር ነው። በተመሳሳይ ጊዜ ካንት ድንበሮችንም አዘጋጅቷል። ነገሮችን በራሳቸው እንዳሉ ማወቅ አንችልም; ልናውቃቸው የምንችለው ለእኛ እንደሚታዩት ብቻ ነው። ይህ ትህትና ድክመት ሳይሆን ጥንካሬ ነው፡ ለነጻነት፣ ለሞራል እና ለእምነት ቦታ እየሰጠ ፍልስፍናን ከቅዠት ይጠብቃል። ስነ ምግባሩ ክብርን በራስ ገዝነት ላይ መሠረት ያደረገ፣ የውበት ምርምሩ ዓለም ሁለንተናዊ እንደሆነ ይጠቁማል እና ሂሳዊ ዘዴው የፍልስፍናን ትርጉም ቀይሯል። የካንት ትሩፋት የተዘጋ ስርዓት ሳይሆን ፈተና ነው። ስለ እውቀት ሁኔታዎች በጥሞና እንድናስብ፣ የአስተሳሰብ ወሰንን እንድናከብር እና የሰውን ልጅ ክብር በነጻነት ላይ እንድንገነባ ይጠይቀናል። ሳይንስ እርግጠኝነትን በሚፈልግበት፣ ፖለቲካ ተጠያቂነትን በሚፈልግበት እና ባሕል በግላዊነት እና ሁለንተናዊነት መካከል ካለው ውጥረት ጋር በሚታገልበት ቦታ ሁሉ ፍልስፍናው ህያው ሆኖ ይኖራል። የካንት አብዮት የፍልስፍና መጨረሻ ሳይሆን አዲስ ጅማሮ ነበር። እውነት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚሰጥ ሳይሆን በምክንያትና በልምድ፣ በነፃነት እና በአስፈላጊነት፣ በትህትና እና በተስፋ መስተጋብር መፈለግ እንዳለበት ያሳስበናል። ቀዳማዊ ፍልስፍና

  • የካንት ትችት ገንቢ ብቻ ሳይሆን ገዳቢም ነበር። ምክንያት ስለ ነፍስ፣ ዩኒቨርስ ወይም አምላክ በመጠየቅ ከልምድ ለመሻገር መሞከሩ የማይቀር መሆኑን ተከራክሯል። ነገር ግን እንዲህ ያሉ ጥያቄዎች ወደ ተቃርኖዎች ወይም እሱ “አንቲኖሚዎች” ብሎ ወደጠራቸው ይመራሉ። ለምሳሌ፡- ዩኒቨርስ ውሱን ነው ወይስ ወሰን አልባ? ሁለቱም መልሶች ሊያከራክሩ ይችላሉ ግን ሁለቱም ሊረጋገጡ አይችሉም። ካንት ግምታዊ ሜታፊዚክስ መገደብ አለበት ሲል ደምድሟል። የኖሜና ዓለምን ማወቅ አንችልም። ሆኖም ይህ ገደብ ነፃ የሚያወጣ ነው፡ ነፃነት፣ ሞራል እና እምነት በግምታዊ ማስረጃዎች ላይ ሳይሆን በሰው ድርጊት ፍላጎቶች ላይ ሊመሰረቱ ለሚችሉበት ተግባራዊ ምክንያት ቦታ ይፈጥራል። • ሂሳዊ ሚዛን እነዚህ መርሆች (ፌኖሜና እና ኖሜና፣ synthetic a priori judgment፣ የመረዳት ምድቦች እና የምክንያት ወሰኖች) የካንትን ሂሳዊ ፍልስፍና እምብርት ይፈጥራሉ። የሳይንስን እርግጠኝነት ይጠብቃሉ፣ የሜታፊዚክስ ቅዠቶችን ያጋልጣሉ፣ እና ለስነምግባር እና የውበት ምርምር አዲስ መሰረት ይከፍታሉ። የካንት አብዮት በራሽናሊዝም እና ኢምፔሪሲዝም መካከል ድርድር ሳይሆን የሁለቱም ሽግግር ነበር። እውቀት በምክንያት ብቻ ወይም በልምድ ብቻ ሳይሆን በሁለቱ አስፈላጊ መስተጋብር የሚገኝ መሆኑን አሳይቷል። ✓ ስኬቶች እና ትሩፋቶች የካንት ፍልስፍና ንድፈ ሃሳባዊ ልምምድ ብቻ አልነበረም። ጠቅላላ የሰውን ልጅ የአስተሳሰብ መስኮች ቀርጿል። የሱ ስኬት የእውቀት ወሰንን እያጋለጠ የእውቀት መቻልን ማረጋገጥ ነበር እና ትሩፋቱ ፍልስፍናን፣ ፖለቲካን እና ባህልን እየቀረጸ ነው። 1. ሳይንስን መጠበቅ ካንት የሁምን ጥርጣሬ ተሻግሮ የሳይንስን እርግጠኝነት አስጠብቋል። መንስኤያዊነት፣ ቦታ እና ጊዜ ከልምድ ከመነሳት ይልቅ የልምድ ሁኔታዎች መሆናቸውን በማሳየት ሳይንስ ለምን ሁለንተናዊ እና አስፈላጊ ሃሳቦችን ማቅረብ እንደሚችል አብራርቷል። ፊዚክስ የልማዶች ስብስብ ሳይሆን በሰዎች የግንዛቤ መዋቅሮች ላይ የተመሠረተ ነው። ይህ ለሳይንስ ህጋዊነትን እና ገደቦችን ሰጥቶታል፡ ፌኖሜናን በእርግጠኝነት መግለጽ ይችላል፤ ነገር ግን ከነሱ አልፎ ወደ መጨረሻው/ከፍተኛው እውነታ መድረስ አይችልም። 2. ስነምግባር እና ነፃነት የካንት Critique of Pure Reason ሂሳዊ ዘዴውን ወደ ሞራል አዝልቆታል። ንድፈ ሃሳባዊ ምክንያት የተገደበ ከሆነ ተግባራዊ ምክንያት አዲስ ጎራ ይከፍታል። ነፃነት፣ ግዴታ እና የሞራል ህግ ከልምድ ሳይሆን ከምክንያት የሁለንተናዊነት ፍላጎት የሚገኘ ነው። ዝነኛው “ካቲጎሪካል ኢምፔራቲቭ” እንደ ሁለንተናዊ ህጎች ልንፈጽማቸው በሚችሉ መርሆዎች ላይ ብቻ እርምጃ እንድንወስድ አጥብቆ ያስጠነቅቃል። ይህ ሞራልን ከአንፃራዊነት የጠበቀ እና የሰው ልጆችን ክብር በራስ ገዝነት ላይ የመሠረተ ነው። 3. አስቴቲክስ እና ፍርድ Critique of Judgment ውስጥ ካንት ውበት እና ነፍስን ዳሷል። የውበት ፍርድ ግላዊ ሆኖም ግን ሁለንተናዊነትን ይናገራል፡ አንድን ነገር ውብ ስንል ምንም እንኳን ፍርዱ በጽንሰ ሃሳብ ላይ የተመሰረተ ባይሆንም ሌሎች እንዲስማሙ እንጠብቃለን። ይህ ግንዛቤ ምክንያት እና ስሜት የሚገናኙበትን ቦታ በመፍጠር በኪነጥበብ፣ በስነ-ጽሁፍ እና በባህል ፍልስፍና ላይ ተጽእኖ አሳድሯል። 4. ዘመናዊው ትሩፋት የካንት ሂሳዊ ፍልስፍና በFitchte፣ ሼሊንግ እና ሂግል ላይ ተጽዕኖ በማሳደር ለጀርመን አይዲያሊዝም መሰረት ሆኗል። ነፃነትን እና ክብርን በምክንያት ላይ በመመስረት ዘመናዊ የሊበራል አስተሳሰብን ቀርጿል። በኢፒስቲሞሎጂ፣ ስነምግባር እና ወቅታዊ የፖለቲካ ንድፈ ሃሳቦች ላይ የሚደረጉ ክርክሮች ላይም ተጽዕኖ አሳድሯል። ዛሬም እንኳን ስለ ሳይንስ ወሰን፣ ስለ ሞራል ተፈጥሮ ወይም ስለ ውበት ሚና የሚደረጉ ውይይቶች ብዙውን ጊዜ ተመልሰው ከካንት ሂሳዊ ማዕቀፍ ይመዘዛሉ። የካንት ስኬት ፍልስፍናን መለወጥ ነበር። በአስተሳሰብ ታሪክ ውስጥ ሌላ ስርዓት አልጨመረም ይልቅም ፍልስፍና ምን ሊሆን እንደሚችል ደግሞ ገልጿል። ትሩፋቱ ሂሳዊ መንፈስ ነው፡ የምክንያት ወሰንን ለማክበር እና ነጻነት እና ክብርን ራስ ገዝነት ላይ ለመመስረት የእውቀት ሁኔታዎችን መመርመር። ✓ ትችቶች እና ተቃራኒ ነጥቦች የካንት ሂሳዊ ፍልስፍና አብዮታዊ ነበር፤ ግን ሙግቱን አላቆመም። ምክንያትን እና ልምድን ለማመጣጠን ያደረገው ሙከራ አድናቆትን አነሳስቷል፤ ነገር ግን ተቃውሞም አስነስቷል። በኋላ ላይ የመጡ አሳቢዎች ስርዓቱ በጣም ገዳቢ፣ በጣም ረቂቅ ወይም በጣም ጥንቃቄ የተሞላበት ነው ብለው ተከራክረዋል። ሶስት ዋና ዋና የትችት መስመሮች ጎልተው ይታያሉ። 1. ሂግል እና አይዲያሊስት ምላሽ ሂግል በፌኖሜና እና ኖሜና መካከል ያለውን የካንትን ጥብቅ ክፍፍል ውድቅ አድርጓል። ለካንት ነገሮችን በራሳቸው እንዳሉ ማወቅ ፈጽሞ አንችልም፤ የምናውቀው በኮግኒሽን የተቀረጸውን መልክ ብቻ ነው። ሂግል ይህንን የድፍረት ውድቀት አድርጎ ተመልክቶታል። ፍልስፍና በመልክ ላይ ካቆመ የፍፁም እውነት ፍለጋን ይተዋል። ሂግል በምትኩ ምክንያት በዲያሌክቲካል እድገት በታሪክ እንደሚገለጥ እና ፍፁም የሆነው እንደ ቋሚ ነገር ሳይሆን እንደ ሂደት ሊታወቅ እንደሚችል ተከራክሯል። ካንት ገደብ ሲያወጣ ሂግል ገደቦቹን ለማሸነፍ ፈልጓል። 2. ኒቼ እና የሞራል ትችት ኒቼ የካንትን የሞራል ፍልስፍና አጥቅቷል። ካቲጎራካል ኢምፔራቲቭ በሁለንተናዊነት ፍላጎቱ ለኒቼ የተደበቀ የክርስቲያናዊ ሞራል ዓይነት ግትር፣ ሕይወትን የሚክድ እና ፈጠራ ጠል ሆኖ ታይቶታል። ሞራል በረቂቅ ምክንያት ሊመሠረት እንደማይችል ነገር ግን የሃይል፣ ደመ ነፍስ እና ባህል መግለጫ ሆኖ መረዳት እንዳለበት ተከራክረዋል። ለኒቼ የካንት ስነምግባር እውነተኛ ነጻነት የራስን እሴቶች በመፍጠር ላይ ሆኖ ሳለ የሰውን ነፃነት ወደ ታዛዥነት ቀንሷል። 3. ወቅታዊ ፈተናዎች በሃያኛው ክፍለ ዘመን የካንት ትሩፋት የታደሰም የተሞገተም ነበር። ∆ ፌኖሜኖሎጂ (ሃሰርል፣ ሄይድገር) ካንት በረቂቅ ምድቦች ላይ አብዝቶ ያተኮረ እና በሚኖር ልምድ ላይ በቂ ትኩረት ያልሰጠ ነው በማለት ተችቷል። በንቃተ ህሊና ውስጥ እንደሚገለጡበት የፌኖሜና ብልጽግና ለመመለስ ፈልገዋል። ∆ የትንታኔ ፍልስፍና የካንትን synthetic a priori judgment በእውነት አስፈላጊ መሆናቸውን ወይም ወደ ቋንቋዊ ስምምነቶች ወድቀው እንደሆነ በመጠየቅ ሞግቷል። ∆ የድህረ ዘመናዊ አሳቢዎች (ፎክዋልት፣ ዴሪዳ) የካንትን ሁለንተናዊ ሃሳብ በመቃወም እውቀት እና ሞራል ሁሌም በታሪክ፣ በኃይል እና በቋንቋ የሚቀረጹ ናቸው ሲሉ ተከራክረዋል። 4. ዘላቂው ውጥረት እነዚህ ትችቶች ቢኖሩም የካንት ሂሳዋ ፍልስፍና የማጣቀሻ ነጥብ ሆኖ ይቆያል። ወሰኑ የሚቃወሙት እንኳ ብዙውን ጊዜ ራሳቸውን በሱ ላይ ይገልጻሉ። የሂግል ዲያሌክቲክ፣ የኒቼ ጄኒኦሎጂ፣ የፌኖሜኖሎጂ ወደ ልምድ መመለስ እና የድህረ ዘመናዊነት የሁለንተናዊ ነገሮች ጥርጣሬ ሁሉም ከካንት ጋር ለምልልስ ብቅ ይላሉ። የእውቀት ሁኔታዎችን፣ የምክንያት ውሱንነት እና የሰው ልጅ ነፃነትን ክብር ለመፈተሽ ያለው ፅኑ አቋም ዛሬም ፍልስፍናን እየቀረጸ ነው።

  • የካንት ሂሳዊ ፍልስፍና ኢማኑኤል ካንት (1724-1804) ወደ ፍልስፍና የገባው በችግር ወቅት ነው። ራሽናሊዝም በምክንያት ብቻ እርግጠኝነትን ቃል ገብቷል ነገር ግን ከህይወት የመራቅ እና የመገለልን አደጋ አምጥቷል። ኢምፔሪዝም እውቀትን በልምድ ላይ መስርቶ ነበር ነገር ግን በመንስኤያዊነት፣ በራስ እና አልፎ ተርፎም የእውቀት መቻል ዙሪያ ወደ ጥርጣሬ መርቷል። የካንት ፕሮጀክት ይህንን ግጭት መፍታት ነበር። መፍትሄው አብዮታዊ ነበር፡- እውቀት በምክንያት ብቻ ወይም በልምድ ብቻ ሳይሆን በሁለቱ መስተጋብር የሚገኝ ነው። ልምድ የእውቀትን ጥሬ ዕቃ ያቀርባል ነገር ግን አእምሮ ያንን ጥሬ ዕቃ በራሱ መዋቅር ይቀርጻል። ቦታ፣ ጊዜ እና መንስኤያዊነት ከአለም የምንማራቸው ሳይሆኑ ቀድሞውኑ ዓለምን ለመረዳት የሚያስችሉ ሁኔታዎች ናቸው። ካንት ይህንን በፍልስፍና “የኮፐርኒካን አብዮት” ብሎ ጠርቶታል። ኮፐርኒከስ ማዕከሉን ከምድር ወደ ፀሐይ በማዞር ሰማያትን እንዳብራራ ካንትም ማዕከሉን ከቁስ ወደ አእምሮ በማሸጋገር እውቀትን አስረድቷል። ዓለምን እንዳለ/እንደሚታየው አንቀበልም ይልቅም በራሳችን የግንዛቤ መዋቅሮች መነፅር በኩል ነው ዓለምን የምንለማመደው። ይህ ሂሳዊ ፍልስፍና (ክሪቲካል ፊሎሶፊ) ሜታፊዚክስን፣ ስነምግባርን እና የውበት ምርምርን (አስቴቲክስ) ለውጧል። ማወቅ በምንችለው ነገር ላይ ገደቦችን አስቀምጧል ነገር ግን የሳይንስ፣ ሞራል እና ነጻነት መቻልንም አረጋግጧል። የካንት ስራ በራሽናሊዝም እና ኢምፔሪሲዝም መካከል ድርድር ሳይሆን የሁለቱም ሽግግር ነው። ✓ አመጣጥ እና ታሪካዊ አውድ የካንትን ፍልስፍና ለማስታረቅ ከፈለገው የሁለቱ ወጎች ዳራ ውጪ ለመረዳት አይቻልም። በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ራሽናሊዝም እና ኢምፔሪዝም አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ደርሰው ነበር። • የራሽናሊዝም ውርስ ዴካርትስ፣ ስፒኖዛ እና ሊብኒዝ በምክንያት ላይ የተመሰረቱ ሰፋፊ ስርዓቶችን ገንብተዋል። አንዳንድ እውነቶች (ሂሳባዊ፣ ሎጂካል፣ ሜታፊዚካል) ከተሞክሮ ነፃ ሆነው ሊገኙ እንደሚችሉ አስረድተዋል። ራዕያቸው በጂኦሜትሪ ግልጽነት እውቀትን መገንባት ነበር። ነገር ግን ከህያው የልምድ አለም ተነጥለው ወደ ረቂቅነት ገቡ። • የኤምፔሪሲስት ፈተና ሎክ፣ በርክሌይ እና ሁም ሁሉም እውቀት የሚጀምረው በስሜት ህዋሳት እንደሆነ ሞግተዋል። በምልከታ፣ በሙከራ እና በግምት ገደቦች ላይ አፅንዖት ሰጥተዋል። ሆኖም የሁም አክራሪ ጥርጣሬ የዚህን መንገድ አደጋ አጋልጧል፡ እውቀት እይታ ብቻ ከሆነ፣ መንስኤያዊነት፣ ራስ እና ሳይንስ ወደ ልምድ እና ፕሮባቢሊቲ ይወድቃሉ። ኢምፔሪሲዝም ወደ ጽንፉ ሲገፋ ለማስጠበቅ የሚፈልገውን እርግጠኝነት ያፈርሳል። • የካንት ግንዛቤ ካንት ራሱ ሁም “ከዶግማዊ እንቅልፌ ቀሰቀሰኝ” ሲል አምኗል። ራሽናሊዝም በንጹህ ምክንያት ላይ ያለው መተማመን ዘለቄታ እንደሌለው ተገንዝቧል ነገር ግን የኢምፔሪሲዝም ጥርጣሬ እውቀትን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት እንደሚያሰጋውም ተመልክቷል። የሱ መፍትሄ አንዱን ወገን መምረጥ ሳይሆን ሙግቱን ማሸጋገር ነበር። • ሂሳዊ እጥፋት ካንት እውቀት የሚመነጨው ከሁለት አካላት መስተጋብር ነው ይላል፡- • ስሜት/ ሴንሲቢሊቲ የልምድ ጥሬ ዕቃን ያቀርባል፤ የምንመለከተውን፣ የምንሰማውን እና የሚሰማንን ማለት ነው። • መረዳት ጽንሰ-ሀሳቦችን እና ምድቦችን ያቀርባል፤ እንደ ቦታ፣ ጊዜ፣ እና መንስኤያዊነት፤ ጥሬውን ዕቃ መዋቅር ይሰጡታል። ይህ የካንት “የኮፐርኒካን አብዮት” ነበር፡ ኮፐርኒከስ ማዕከሉን ከመሬት ወደ ፀሀይ በማዛወር ሰማያትን እንደገለፀው ካንት ማዕከሉን ከቁስ ወደ አእምሮ በማዛወር እውቀትን አስረዳ። ዓለምን ፓሲቭሊ አንቀበልም ይልቅም በግንዛቤያችን ሁኔታዎች ውስጥ በንቃት እንቀርጸዋለን። • ታሪካዊ ተጽእኖ የካንት Critique of Pure Reason (1781) የለውጥ ነጥብን አሳይቷል። ነገሮች በራሳቸው እንዳሉ (ኖሜና) ለማወቅ ከአቅማችን በላይ መሆናቸውን እውቅና በመስጠት ልናውቃቸው የምንችላቸው ላይ ወይም ነገሮች ለኛ እንደሚታዩት(ፌኖሜና) ላይ ገደብ አስቀምጧል። ይህ ሂሳዊ አቋም የሳይንስን እርግጠኝነት ጠብቋል፣ የሜታፊዚክስን ወሰን አጋልጧል፣ እና ለስነምግባር እና የውበት ምርምር አዲስ መንገድ ከፍቷል። ✓ የካንት ሂሳዊ ፍልስፍና ዋና መርሆዎች የካንት ፍልስፍና ብዙውን ጊዜ "ሂሳዊ" ተብሎ ይጠራል ምክንያቱም የእውቀት ስርዓትን ብቻ ሳይሆን የሚገነባው እውቀትን የሚቻል የሚያደርጉትን ሁኔታዎችም ይመረምራል። Critique of Pure Reason ምክንያትን አለመቀበል ሳይሆን ሰፋ ያለ ትችት ነው። አፕሮቹ በአራት መርሆዎች ይገልጻል። 1. ፌኖሜና እና ኖሜና ካንት በፌኖሜና (ነገሮች ለእኛ እንደሚታዩት) እና ኖሜና (ነገሮች በራሳቸው እንዳሉት) መካከል መስመር አስምሯል። የኖሜና አለምን በቀጥታ ማወቅ አንችልም። እውቀታችን በአዕምሯችን ቅርጾች ተዋቅሮ በእይታ ብቻ የተገደበ ነው። ይህ ልዩነት ድንበር ያበጃል፡ ሳይንስ የፌኖሜናን ዓለም በእርግጠኝነት መግለጽ ይችላል ነገር ግን ስለ የመጨረሻው/ከፍተኛው እውነታ ያሉ የሜታፊዚካል ሃሳቦች ከአቅማችን በላይ ናቸው። ይህ አክራሪ እርምጃ ነበር። ፍልስፍናን እያሰከነ የሳይንስን ትክክለኛነት አስጠብቋል። እንዲሁም ሜታፊዚክስንም አሻሽሏል፡ ስለ እውነታው የመጨረሻ/ከፍተኛ ተፈጥሮ ከመገመት ይልቅ ፍልስፍና ልምድ የሚችልበትን ሁኔታዎች መመርመር አለበት። 2. Synthetic a priori judgment ካንት ማዕከላዊ ጥያቄ ጠይቋል:- እውቀት እንዴት አስፈላጊ እና መረጃ ሰጪ ሊሆን ይችላል? ሙሉ በሙሉ በትንታኔ የሚገኙ እውነቶች አስፈላጊ ናቸው ነገር ግን ምንም አዲስ ነገር አይነግሩንም። ሙሉ በሙሉ ኢምፔሪካል እውነቶች ደግሞ መረጃ ሰጭ ናቸው ግን ጊዜያዊም ናቸው። ካንት ሳይንስ በሶስተኛው ዓይነት ፍርድ ላይ የተመሰረተ ነው ሲል ተከራክሯል፡- Synthetic a priori. Synthetic a priori judgment አስፈላጊ እና መረጃ ሰጪ ነው። ለምሳሌ "እያንዳንዱ ክስተት መንስኤ አለው" የሚለው ሃሳብ ከልምድ የተገኘ አይደለም ሆኖም ግን ሁሉንም ልምዶች ያዋቅራል። ሒሳብ እና ፊዚክስ እንደዚህ ባሉ ፍርዶች ላይ ይመረኮዛሉ። የሚቻልም ነው ምክንያቱም አእምሮ ራሱ ልምዶችን ለመረዳት የሚረዱ ቅርጾችን (ቦታን፣ ጊዜን፣ መንስኤያዊነትን) ያበረክታል። 3. የመረዳት ምድቦች ካንት አእምሮ እንደ አንድነት፣ ብዙነት፣ መንስኤያዊነት እና አስፈላጊነት ባሉ ምድቦች አማካኝነት ልምድን በንቃት እንደሚያደራጅ ተከራክሯል። እነዚህ ከዓለም የምንማራቸው ሳይሆኑ ዓለም እንደ አንድ ስርዓት ሙሉ ሆኖ እንዲታይ የሚያደርጉ ሁኔታዎች ናቸው። እነሱ ከሌሉ ልምድ የተመሰቃቀለ የእይታ ፍሰት ይሆናል። ይህ መርህ ፍልስፍናን ለውጧል። አእምሮን ኢምፔሪሲስቶች እንዳደረጉት እንደ ፓሲቭ የእይታዎች ተቀባይ ከማየት ይልቅ ካንት እውቀትን በመገንባት ረገድ ንቁ ተሳታፊ አድርጎ ተመልክቶታል። የምናውቀው ዓለም በኛ የግንዛቤ መዋቅሮች የተቀረጸው ዓለም ነው። 4. የምክንያት ገደቦች

  • https://youtu.be/Rg847CbswMI

  • የኢትዮጵያ ስነ-ፁሑፍ Ethiopian literature pinned «ከቁሳዊ ወደ ብሔራዊ ማንነት የተሸጋገረው ግድብ፤ ሎሬት ፀጋዬ የተነበዩት አባይ በረከቱ ሲፈተሽ #ጥበብ #ኪነት #አ... https://youtube.com/watch?v=ZGnKcpl_JB0&si=QH9wK8OQf6ZIQa89»

  • ከቁሳዊ ወደ ብሔራዊ ማንነት የተሸጋገረው ግድብ፤ ሎሬት ፀጋዬ የተነበዩት አባይ በረከቱ ሲፈተሽ #ጥበብ #ኪነት #አ... https://youtube.com/watch?v=ZGnKcpl_JB0&si=QH9wK8OQf6ZIQa89

  • ታላቁን ሕዳሴ ግድብ ጉዞ የዘከረ ዘጋቢ ፊልም

  • ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ጉዞ፤ ከህልም እስከ እውን! ዘጋቢ ፊልም #bigdam #ethiopianbigdam https://youtube.com/watch?v=UVqkKLK4B3s&si=kFr8SMf9uJ_sLfbO

  • https://youtu.be/tKVAkuKMNxI

  • የኢትዮጵያ ስነ-ፁሑፍ Ethiopian literature pinned «ደጃዝማች በላይ ዘለቀ በፋሽስት ዘመን ጎጃም ውስጥ ሲንቀሳቀሱ ከነበሩ አራት የአርበኛ መሪዎች መካከል አንዱ ነው። እየተደጋገመ የሚወሳው የበላይ ዘለቀ ስም ብቻ ስለሆነ የሌሎቹ የጎጃም አርበኛ መሪዎች ስምና ስራ በተለይ በወጣቱ ትውልድ ዘንድ አይታወቅም። ሶስቱ የጎጃም ታላላቅ አርበኛ መሪዎች ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ፣ ደጃዝማች ነጋሽ በዛብህና ራስ ኃይሉ በለው ናቸው። በነዚህ አርበኞች ስር እልቆ ቢስ ስመጥር…»

  • видео или голосовое, без подписи

  • ሃገራችን ኢትዮጵያ በየዘርፉ ድኩም የሆነችበት ዋናው ምክንያት ለሳይንስ የሰጠችው አናሳ ትኩርት ዋነኛው ይመስለኛል በግሌ። ለእዚህ ደግሞ ትብታቡ የበዛ እጅግ ብዙ ምክንያት ቢኖርም በመግቢያዬ እንዳወሳሁት ዋናው ሳይንስን የማስተማሪያው ቋንቋ ተደራሽነት ውስንነት አንዱና ዋናኛው ነው። እንዲህ ከሳይንስ የሚያቀራርቡን መጽሃፍትን ስናገኝ በሽሚያ ብናነብ ብናስነብብ ከችግሩ ትንሽ መቀነስ ይችለናል ስል አስባለሁ። ይህን በዝግጅቱ የተዋጣለት ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ የፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ መጽሃፍ እንድናነብ በመጋብዝ ላብቃ ። ሰናይ ጊዜ!! Reviewer : Hab Camus is an associate editor at Think Ethiopia

  • መንግስታት አሳሾቻቸውን ወደተለያዩ ክፍለ አለማት አንቀሳቀሱ ። በውጤቱም ልዩ ልዩ ማእድኖች ተገኙ ። በቅድመ ኢንዱስትሪ አብዮት የነበሩቱ ውስን የሃይል ምንጮች ከአብዮቱ በኋላ ተትረፈረፉ። አልሙኒየምን ታይታኒየምን እንደጥሬ እቃ ግበአትነት መጠቀም ተጀመረ። በፊት ስለመኖራቸው ስንኳ አይታወቁም ነበር። አሁን ግን ኢንዱስትሪውን ያሾሩት ገቡ። በግዙፍ ማሽኖች የሚታገዘው የሰው ህይዎትም ምርታማ ሆነ። በእንዲህ ያለው የሰው ልጅ ጉዞ ሃይማኖትን አለማንሳት አይቻልም። ጥንት ገና ሆሞሳፒያን በዋሻ ሳለ ግምሽ አካሉ የሰው ግማሽ አካሉ የአንበሳ ምስል ቀርፆ እንደ አንድ ህልው አካል ይመለከተው ነበር። እንዲህ ያሉ በእውን ልንዳብሳቸው ልናያቸው የማንችል ነገሮችን አሉ ብሎ የማመን ዝንባሌ የሰው ልጅ ብቻ እንደሆነ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ በመጽሃፉ ይነግረናል። ሌሎች እንስሳዎች በስሜት ህዋሳቸው ከሚደርሱበት እና ከሚጨበጠው በላይ ሌላ ነገር አለ ብለው እንደማያስቡም አያይዞ ያወሳል። ድሮ በዋሻ የተጀምረው እምነት ከ << አኒሚዝም>> (Animism) አንስቶ ዘመናችን እስከደረሱበት አብርሃማዊና ሌሎች የምስራቁ አለም ሃይማኖቱች የታሪክ ዳራውን ሲቀያይር ኖሯል። የ <<አኒሚዝም>> እምነት ሁሉም አካላት ነብስ አላቸው ብሎ የሚያምን እና እንስሣትንም ለማረድ ይቅርታ ጠይቆ እስከማረድ የሚያደርስ ነበር።በጉን " ርቦኝ ልበላህ ስለሆነ ይቅርታ አድርግልኝ።" እንደማለት አይነት። ከ አኒሚዝም ቀጥሎ በሕብረ- አማልክት ማመን( polytheism) በግሪክና በሮም ተስፋፍቶ ነበር። የዝናብ አምላክ፣ የጨረቃ አምላክ ፣ የፍቅር ፣ የጥላቻ አምላክ እያሉ ብዙ አማልክታት ነበሯቸው። ይህ አይነቱ እምነት በአንድ አምላክ በማመን(monotheism) የተተካው በአንድ አምላክ አማኞች ከእኔ ውጭ እውነተኛ ሃይማኖት የለም በሚል ጠንካራ ስብከት እንደሆነ መጽሃፉ ያነሳሳል። በዚህም ሳቢያ በውጭም ሆነ በእኛይቱ ሃገር ኢትዮጵያ ብዙ የሃይማኖት ጦርነቶች ተነስተው አሰቃቂ እልቂቶች አልፈዋል። በኢትዮጵያ እንደምሳሌ ከሚነሱት ውስጥ አጼ ሱስንየስ የካቶሊክን ሃይማኖት ተቀብለው ከነባሩ ኦርቶዶክስ ሃይማኖተኛ ጋር የገቡት ግጭት አንዱ ነው። ሃይማኖቶች ለዘመናዊው ሰው ለሆሞሳፒያን ምን ጥቅም ነበራቸው ሲባል ፥ በማህበረስብ ውስጥ ከፍተኛ ትብብርን በመፍጠር መንግስታትን አጠንክረዋል፣ ለአንድ አላማ የሚቆሙ በባህል በቋንቋ የሚለያዩ ህዝቦችን አቀራርበዋል፣ አስተባብረዋል። በዚህም በመተባበር ከሌሎች እንስሳት በላይ እንዲቀመጥ አስችለውታል። ከዚህ ባሻገር እነኚሁ ልዩ ልዩ ሃይማኖቶች ለብዙ ማህበረሰቦች አለምን የማያ ብቸኛው መነጸርም በመሆን አገልግለዋል። ስለዝናብ አመጣጥ ፣ ስለድርቅ አመጣጥ፣ ስለበሽታዎች መንስኤ ግምት በመስጠት አወቅነው ያሉቱን ለምእመኑ ሲያካፍሉ ኖረዋል። ዛሬ ላይ ደግሞ ሳይንስ ስለብዙው ነገር የራሱን የማጥኛ ዘዴ ተከትሎ ምድሪቷን ብሎም ህዋውን እያሰሰ ይገኛል። የሃይማኖትንም ቀንበር አላልቶለታል ብለንም ማሰብ እንችላለን። ግን...ግን ዛሬ ላይ ከምን ደረሰን ?! "በዘመናችን በባህርይ (ኩነት) ዙሪያ ያጠነጠኑ ብዙ ሳይንሳዊ ግንዛቤዎችን ለምሳሌ ስለ << ፍቅር>>፣ <<ሩህሩህነት>>፣ የእንስሳት << ግለኝነት ባህርይ>> ወዘት ግንዛቤ አዳብረናል። ፍቅር እና ሃዘን ማሰብ ማሰላሰል ተስፋ ምኞት ወዘተ የሰው ልጅ ዋናኛ እና ብቸኛ ባህርያት ናቸው ወይስ ሌሎች እንሳስት እነኝህን ባህሪያት ከሰው ልጅ ጋራ ይጋራሉ?" የሚሉት ጥያዌች ተነስተው አይ! እነኚህ ባህሪያት የሰው ልጅ ብቻ አይደሉም ሌሎች እንስሳትም ይጋሩናል የሚል ድምዳሜ ላይ ተደርሷል። እንዴት ለሚለው በዘመኑ በርካታ ሙክርቶች( experiments) ተሰርተዋል። በመጽሃፉም ለአስረጅነት ይረዳ ዘንድ የተወሰኑት በግልጽ ሁኔታ ተብራርተዋል። ሌላው የዘመናችን መልክ በቴክኖሎጂ ያሳየነው አስደናቂ እምርታ ነው ። "የዘመናችን ዋና ዋና ቴክኖሎጂዎች የባዮቴክኖሎጂ ምህንድና( biological enginering) እና አልጎሪዝምን መሰረት ያደርጉት የመረጃ ቴክኖሎጂ( information technology) እና ሰው ሰራሽ አእምሮ( artificial intelligence) ናቸው።"(ገጽ 163) ባዮቴክሎጂው የተሻሻሉ ምግቦችን ሰጥቶናል። ያሉበት የአየር ንብረት ሳይበግራቸው ብዙ ትርፍን የሚያሰገኙ ሰብሎች በዚሁ ምህንድና የተበረከቱ ናቸው። "በተጨማሪም ራስን ለመተካት ወሲባዊ ግንኙነት የማያስፈልግበት ዘመን ላይ ተደርሷል።" ከወንዱ ነባዘሩን እና ከሴቷ እንቁላልን በመውሰድ በሌላ ሴት ማህጸን ጽንሱን ማሳድግ ተችሏል። " ይባስ ብሎ በሳይንስ ከአካል አንድ ነጠላ ህዋስ፣ ወስዶ ሙሉ ህያው አካል ለማግኘት ተችሏል።" ( ገጽ 163) ለዚሁ ምሳሌ የምትሆነው በስኮትላድ የተሰራችዋ Dolly የተሰኘች በግ ናት።<< ሳይቦርግ>> (Cyborg) ሌላው የዘመናችን ድንቅ ክስተት ነው። " ህያው አካል ላይ ህይዎት አልባ አካል እየተቀጠለ ፣ አዲስ አይነት ህያው አካል መሰል የቴክኖሎጂ ውጤቶች እየታዩ ነው።" ይኸውም በተፈጥሮና በሰው ሰራሽ አደጋ አካላቸው ለጎደለባቸው ሰዎች ጥሩ መፍትሄን አቅርቧል። የተቀጠለው አካል ከአንጎል ትእዛዝ ስለሚቀበል ተግባሩን እንደነባሩ ህያው አካል ማቀላጠፍ ይችላል። ድንቅ በርከት አልታከለልንም ታዲያ ጓዶች?! ግሩም እንጂ!! ሰው ሰራሽ አእምሮም በልጽጎ እኛን በቼዝ ጨዋታ የሚረቱ ሮቦቶች ተሰሩ። ህክምናን ከሰው ልጅ በተሻለ የሚከውኑ ሮቦቶችም ተስርተው ለወደፊት ጥሩ ተስፋን አሰንቀዉናል። ዛሬ ላይ ይህ ከሆነ ነገስ?... ሳይንስ ዛሬ ከዚህ ከደረሰ ነገስ ሲባል ነገም ይኸው ሰው ሰራሽ አእምሮ በከፍተኛ ልህቀት እንደሚቀጥል ይገመታል። አንድ የመረጃ ቋት ለመገንባትም ታልሟል። ቴክኖሎጂው ህክምናውን አሁን ካለበት በላይ አዘምኖት የሰው ልጅ ካንሰርን መሰል የህልዉናን ተገዳዳሪ በሽቶች እስከወዲያኛው ሊያጠፋ አቅዷል። ይህን ያስችላል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት ቴክኖሎጂም <<ናኖ ቴክኖሎጂ>> ( Nano technlogy) ይሰኛል ። ጥቃቅን ሮቦቶች(robots) በመላ ሰውነት ውስጥ በመስፈር ካንስር አምጭ ህዋሶችን አፍርከድሜ ያስበላሉ እንዲሁም እርጅናን የሚያመጡ ህዋሶችን እየቀለበሱ(እያደሱ) ከአደጋ በስተቀረ የእርጅና ሞትን ያስቀራሉ ተብሎ ይታሰባል። 2050 ላይም እውን ይሆናል ተብሎ ተተንብዩኣል። እነኚህ ሁሉ ዝማኔዎች ሲመጡ ግን ከስጋት ውጭ አይደሉም ። ሰው ሰራሽ እእምሮ የሰውን ልጅ ስራ ከነጠቀ ምን ልንሆን ነው?! የሚል ስጋት አንዱ ነው ። ሌላው ይኸው የሰው ሰራሽ አእምሮ ስሜት አልባ የእውቀት ክምችት ስለሆነ የሰውን ልጅ ቢያጠፋውስ ወይም ባሪያ ቢያደርገውስ የሚሉ ስጋቶችም አብረው ይነሳሉ። አይ የለም የለም!የሰው ልጅ እስከሰራቸው ድረስ ከሰው ልጅ ቁጥጥር ውጭ የሚሆኑበት እድል አይኖርም ቢኖርም እራሱ የሰው ልጅ መፍትሄ ያብጅለታል የሚሉም በአንድ ወገን አልጠፉም። እስኪ የሚሆነውን እናይ ዘንድ የከርሞ ሰው ያድርገን እያለን የነገን መልክ ለማየት በጉጉት እንጠብቃለን።

  • የመጽሐፉ ርእስ:- ከየት ወደ የት? ደራሲ:- ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ዘውግ:-ሳይንስ የህትመት ዘመን:- 2011 ዓ.ም Rating : TBA (ከትናንት እስከ ነገ ) እንደ መንደርደሪያ.... አንድ ክፍለዘመን የተሻገረ የዘመናዊ ትምህርት ታሪክ ቢኖረንም ሳይንስ ደጃችን እስካሁን አልቆረቆረችም እስክንል ድርስ ማህበረሰባችን ለሳይንስ ባዳ እንደሆነ ነው። በአካዳሚው ዙሪያ ያሉት ስንኳ በቅጡ ዘልቋቸዋል ወይ የሚለውም ብዙ የጠራ ነገር የለውም። ለዚህ ሁኔታ እንደምክንያት ከሚጠቀሱት መሃል የትምህርት ስርዓቱ የሚዘወርበት ቋንቋ ሃገር በቀል አለመሆኑ በዋናነት እና በጉልህነት ይወሳል። ይኸውም በተራው ሳይንስ በአካዳሚው ካሉት ወይም ካለፉት ሰዎች በዘለለ ማህበረሰቡን በስፋት እንዳይደርሰው እራሱን የቻለ ትልቅ ደንቃራ ሆኖ ቆይቷል፣ እየቀጠለም ነው። ይህን ሁኔታ ተገንዝበው ለሃገራቸው እና ለፈለቁበት ወገናቸው ከፍተኛ የመቆርቆር ስሜትና ሃላፊነት ተሰምቷቸው ሳይንስን ለማኸዘብ(የህዝብ ለማድረግ) የተንቀሳቀሱልን ውስን ሰዎች አልጠፉም። ከእነዚህም መሃል ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ይህን 'ከየት ወደ የት ?' ን ጨምሮ በርከት ያሉ መጽሃፍትን በተላያዩ ጊዜያት አበርክተውልናል። 'ወረርሽኝ' እና 'የህያው ፈለግ'ለዚሁ ሳይንስን የማኸዘብ አላማ ከተጻፉት መሃል ተጠቃሾች ናቸው። አንዳንድ ጥያቄዎች ዘዎትር በየትውልዱ ሲጠየቁ ይኖራሉ። ከነዚህም መሃል ከየት መጣን ወዴትስ እንሄዳለን የሚል ጥያቄ ልሽሸው ቢሉ ስንኳ አንዲት ጋት የማያራምድ ውልፍት የማያሰኝ የጎን ውጋታችን ይመስላል። ልባችን እንዲረጋ ትናንትናችን ማወቅ እንዲሁም ስለነገ የጠራ ትልም ይኖረን ዘንድ እንሻለን። የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ እንዲሉ ፥ ሁለቱም ዛሬያችን ላይ ተመላልሰው ይታሰባሉ። ታዲያ ለዚህ አንገብጋቢ ጥያቄ መልስ አለን የሚሉ ልዩ ልዩ ሃይማኖቶች ቢኖሩም ሳይንስ ደግሞ የራሱን መልስ ይዞ በአንድ ጎራ ይሰለፋል። ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላም በአማርኛ ቋንቋችን ነገሩን ሊያስዳሱስን 'ከየት ወደ የት?' ን እንካችሁ ብለውናል። ከየት ነን ግን እኛ ሰዎች?!... ከየት መጣን ሲባል በአብዛኛው የህያውነት ጅማሮን አምታተው የተረዱ ሰዎች ሳይንስ ሰዎችን ከዝንጀሮ መጣችሁ እንደሚለን በመናገር ሳይንሱን ባልዋለበት የሚያውሉ በርካታ ግለሰቦች ሞልተዋል። ነገሩ የሚደንቀው መስኩ በጎለበተበት የውጭው አለምም ይህ ነገር መናፈሱ ነው። ከመደነቅም አልፎ ትዝብትን የሚያጭርብን ግን ሳይንሱን በበቂ ሳይገነዘቡ ሊያበሻቅጡት በሚጥሩ ሰዎች እንዲህ ያለው ሸውራራ አተያይ መሰንቀሩ ነው። የመጽሃፉ የመጀመሪያ ክፍል ምእራፍ አንድ ይህን የሰውን ልጅ አመጣጥ ይተነትናል። በሃተታውም ከላይ የጠቀስኩትን ጠነን ያለ አተያይ ያጠራልናል። " አሁን ምድርን የሚጋሩን ዝንጀሮዎች ጋራ የምንጋራ የዘረ ሃረግ ነው፣ ራቅ ያለ ዝምድና ነው ያለን።" ሲል ጀምሮ እንዲህ ይቀጥላል። " የሰው ልጅ ዋናው የዘር ግንድ ፕራይሜትስ(primates) በመባል ይታወቃሉ። እነሱም በሁለት መለስተኛ የዘር ግንዶች ይከፈላሉ <<ፕሮሲሚያን>> (Prosimians) እና <<አንትሮፖይድ>> (Anthropoids) ፕራይሜትስ በመባል ይታወቃሉ።( ገጽ 3) ታዲያ እኛ ከዝንጀሮዎች ጋር የምንጋራው አንትሮፖይድ የተባለውን የዘረ ሃረግ ነው ። ለዚህም ነው ብንራራቅም ዘመዳሞች ነው የምንለው። ዋናው ሃሳብ እኛ የሰው ልጆች ከዝንጀሮ ወደ ሰው ስንቀየር የኖርን አይደለንም። በዝግመተ ለውጥ እሳቤም እንዲህ ያለ ትንታኔ የለም። የሆነው ሆነናስ እንዲያው ለመሆኑ ህይዎትስ እንዴት ተጀመረ ?! ይህ ነው ቀዳሚው ጥያቄ ወደ ዝግመተ ለውጥ ሃቲት ከመገባቱ በፊት። ምድር ከአራት ቢሊዮን አመታት የዘለለ እድሜ ቢኖራትም ህያው አካል በምድር የታየው ግን ከ 3.2 ቢሊዮን አመታት ገደማ በፊት ነበር። ከምድር እውን መሆን በኋላ ወደ አንድ ቢሊዮን አመት ዘግይቶ እንደማለት ነው። "ግኡዝ ሞሊኪዪሎች በጨዋማ ውሃ(ውቂያኖስ) ውስጥ በተካሄዱ ውስብስብ ኬሚካው ግንኙነቶች(መስታጋብሮች) መሃል በአጋጣሚ በሞሊኪዪሎች ውህደት ህያው የሆኑ አካላት በምድር ላይ እንደተከሰቱ ይገመታል።" ታዲያ ይህ ግምት በበሬ ወለድ አይነት አሉባልታ ሳይሆን በማስረጃ የተደገፈ ነው። ምንድን ይህ ማስረጃ?!... ህያው አካላት ተከሰቱበት በተባለው ዘመን የምድር ከባቢ አየር በካርቦንዳይ ኦክሳይድ(CO2)፣ ሃይድሮጅን ሰልፋይድ(H2S) እና ሰልፈር ዳይኦክሳይድ(SO2) የተሞላ ነበር።እነዚህን የአየር ውህዶች መብረቅ ሲመታቸው ለህይዎት አስቻይ የሆኑ አሚኖ-አሲዶች(aminoacids) ተፈጠሩ። መብረቅ ከፈተኛ የኮረንቲ ሃይል እንዳለው ይታወቃል።በዘመናችንም ላብራቶሪ እኒህን ከላይ የተጠቀሱትን ሞሊኪዪሎች በያዘ የአየር ድብልቅ ውስጥ ከፍተኛ የኮረንቲ ሃይል ሲለቀቅ ተመሳሳዩ ውጤት ስለተገኘ የተቀመረውን መላምት(hypothesis) አጠናክሮታል። እንዲህ የተጀመረው ህያውነት በረዥም ዘመናት የልውጠት ሂደት አልፎ በቅርጽም በባህሪም የተላይዩ ህያዋንን አስገኘ። እኛም እንደ አንዱ ሆንን። ዘመናዊ የሰው ልጅ ሆሞሳፒያን (Homo sapiens) ቅሪት በዛሬይቱ ኢትዮጵያ አፋር ተገኝቷል ። ከሱ የቀድሙት ሆሞ ሃቢልስም ሆነ ሌሎች ቅሪቶች በዚህችው ምድር ተገኝተዋል። ዝነኛዋ 'ድንቅነሽ' ም ለዚሁ ምስክር ናት። ለኢትዮጵያም የሰው ዘር መገኛ ያስባላትን ቅጽል አስገኝተውላታል። ይህ ምስኪን ፍራፍሬ ቃራሚ እና ስር ማሽ የሰው ዘር እንዴት አለሙን ተቀጣጠረ ?! ሌሎቹን እንሳሰዎች በእጁ በእግሩ ታግሎ እየጣለ እዚህ ደረሰ እንዳይባል ጡንቻው ኮስማና ነው። ከእሱ እጅግ የላቁ ባለ ስለት ጥርስና ባለፈርጣማ ጡንቻ አውሬዎች በቁጥር ብዙ ነበሩ። ታዲያ በምን "ተአምር" አሸነፈቸው የተባለ እንደሆነ መልሱ እሳት ነው ። እሳትን ማንደድ የቻለ ለት የሰው ዘር አለሙን በእጁ አገባ። ከፊታቸው ይቆም ዘንድ ይበረከረብ የነበረው የሰው ዘር ከእሩቅ በእሳት ይለበልባቸው ጀመር። ለጥርሱ አልታኘክ ይሉ የነበሩትን ስጋዎች በእሳት ሙክክ አድርጎ አብስሎ ይግጣቸው ገባ። በዚያም አለሙን ቀጨ። በእሳት ጉልበቱ ተማማኖ በአንድ አካባቢ በአዳኝነት እና ቃራሚነት ይኖር የነበረው ሰው ከኮግኒቲቭ አብዮት ( Cognitive Revolution) በኋላ አለምን ለማድረስ ከ 45,000 አመት በፊት አውስታራሊያን ወረረ። ይህ አብዪት እውን የሆነው የሰው ዘር ማመዛዘንና ማስታዋልን ከተረዳ በኋላ ነበር። አላማወቁ ምቾት የሚነሳው ታታሪ ሰው ተገኘ። መንገዱም ከአያቶቹ ብዙ ማይልስ ራቀ። ይህ እየበሰለ የመጣው የሰው ዘር ግብርናን ከጀመረ በኋላ ሰፈራን ለመደ( የለም የለም! ሰፈራ ከግብርና አብዬት በፊትም ነበር የሚሉ ወገኖችም አሉ። በመጽሃፉ የሁለቱንም መከራከሪያ እናገኛለን። ) ውስኑ ሰፈራም ቀስ በቀስ ወደጎሳ ጎሳውም ወደመንግስታት ተለወጠ። መንግስታት ሲፈጠሩ የድሮው አይነት በቃል እና ፊደላት የተወሰነው ቋንቋ የኑሮን ውስብስብነት ሊቋቋመው አልቻለም ።በመሆኑም ቁጥር ተፈጠረ። ወትሮም በጽህፈት ቋንቋ ኑሮውን ሲያሰልጥ የነበረው ማህበር አሁን ደግሞ በቁጥር ሌላ እርምጃን አከለ። የፊደላት ጽህፈቱም ቁጥርን የመጠቀሙም ግኝት እውን እንዲሆን ያስቻለው የመንግስታቱ ውስብስብ አወቃቀር መሆኑን ልብ ይሏል። ግብርናውን እያቀላጠፈ በምግብ እራሱን እያትረፈረፍ የነጎደው ሆሞሳፒያን የኢንዱስትሪ አብዮትን( Industrial Revolution) ያስጀምር ዘንድ የተወሰኑ ሺህ አመታትን ሊታገስ ግድ ብሎት ነበር። ለዚህ አብዮት ዋናኛ መነሻው አሰሳ ነበር።

  • የኢትዮጵያ ስነ-ፁሑፍ Ethiopian literature pinned «Ethiopia: ኢትዮጵያ እና የባሕር በር፤ አሰብ ወደብን አስመልክቶ የመሪዎች ምን አሉ? ssabEthiopia ... https://youtube.com/watch?v=QovLA8OHEDY&si=xE-PRAlElM9kc5vu»

  • ደጃዝማች በላይ ዘለቀ በፋሽስት ዘመን ጎጃም ውስጥ ሲንቀሳቀሱ ከነበሩ አራት የአርበኛ መሪዎች መካከል አንዱ ነው። እየተደጋገመ የሚወሳው የበላይ ዘለቀ ስም ብቻ ስለሆነ የሌሎቹ የጎጃም አርበኛ መሪዎች ስምና ስራ በተለይ በወጣቱ ትውልድ ዘንድ አይታወቅም። ሶስቱ የጎጃም ታላላቅ አርበኛ መሪዎች ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ፣ ደጃዝማች ነጋሽ በዛብህና ራስ ኃይሉ በለው ናቸው። በነዚህ አርበኞች ስር እልቆ ቢስ ስመጥር አርበኞች ነበሩ። የዛሬው ቀን በላይ ዘለቀ የተሰጠውን ምህረት ባለመጠቀሙና የወቅቱ አቃቢ ሕግ የነበሩት አርበኛው ደጃዝማች ታከለ ወለደ ሐዋርያት ያቀረቡበትን ክስ መከላከል ባለመቻሉ ፍርድ ቤት በስቅላት እንዲቀጣ የወሰነበትና የተሰቀለበት እለት በመሆኑ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ በትውልድ ሐረጉ ዙሪያ የሚስተጋባውን ውዥንብር ያጠራ ዘጋቢ ፊልም እንሆ። https://youtu.be/7xr9yJpZJLQ?list=PLpczBs3c1LgEqAx3DDMDN1YePZTOYXdmF

የኢትዮጵያ ስነ-ፁሑፍ Ethiopian literature — tgindex