የኛ ግጥም 😍😄❤🥰🥺
Статистикаእንኳን ደና መጡ🙏 በዚህ ቻናል #ግጥሞች #ቀልዶች እንዲሁም ሀገርኛ ወጎችን አዝናኝ መረጃዎችን በለዛ እናገኛለን ለማንኛውም አስተያየት እንዲሁም ስራዎን ማቅረብ ከፈለጉ ወይም cross ከፈለጉ በዚህ ያናግሩኝ 👉 @berii34 እዚህ ለይ ደሞ👇 @ethiopianye👈join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ for any comment👉 @berii34
- Последний пост
- 29 июн.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 22
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- —
- 1/48двое суток
- —
- 1/72трое суток
- —
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
የውድቀቴን መንገድ ሸርሽራ በመውደድ ያቀናችኝ ንግስት ... የሰጠችኝ ክብር አቤት አቤት ሲያምር {ልክ እንዳንቺ ማርያም} መኖር እንድጠላ መንፈሴን አድክሞ ማጣት አንቆኝ ሲዞር ክንዱን አፈርጥሞ የምሆነው ጠፍቶኝ ተንበርክኬ ሳዝን ሳትለኝ ደካማ ቀና አረገችኝ ቀንበሬን ተሸክማ! እምቅ የእንባ ጠል ጉንጬን ሲንጠለጠል ኅዘን በደቆሰው ልስልስ ስስ አንጀቷ ዕንባዬን ያበሰው አቤት ሲያምር ጣቷ {ልክ እንዳንቺ ማርያም} እኔነት እስካጣ ፍቅር ሸሽቶኝ በሮ ብቸኝነት ሚስማር ሲያደማኝ ቸንክሮ የማረገው ጠፍቶኝ ሞቴን እየናፈቅኩ ሳዘጋጅ መስቀሌን ትንፋሽ ለገሰችኝ ዳብሳ ሰንበር ቁስሌን የጅራፍ ሹል ትርትራት የልቤ ስውር ስብራት አድቅቆ ሲጥለኝ ... እንዲሆን ለነፍሷ ስሞ ሳቅ ያሳየኝ አቤት ሲያምር ጥርሷ {ልክ እንዳንቺ ማርያም} ስትችልበት ማዘን ስታውቅበት ማቀፍ ብሶት አስዘርግፎ በሰላም ማሳረፍ {ልክ እንዳንቺ ማርያም} ስትችልበት ጸሎት ስታውቅበት ማውራት ጨለማን ገርስሶ በፈገግታ ማብራት {ልክ እንዳንቺ ማርያም} ስትችልበት ማከም ስታውቅበት ማዳን ፍቅር በልብ ሰጥቶ መለገስ ማር ኪዳን #ኤልዳን
https://t.me/ke_kaloche1
አለቀለት ያሉት (በእውቀቱ ስዩም) ከጅረት አጠገብ ፥ቆሞ የኖረ ዛፍ መብረቅ ገነደሰው አሁን ድልድይ ሁኖ፥ ያሸጋግራል ሰው :: “አለቀለት” ያሉት፤ ተልኮው መች አልቆ ቆሞ የጠቀመ፥ መላ አያጣም ወድቆ፤ @ethiopianye
ናፍቆቴ እናቴ አንቺ የኔ ኩራት እናቴ.... የፍቅር ማሰሮ እናቴ ልበልሽ የናፍቆት እሮሮ ትዝይለኛል ያኔ ጠረንሽ ሲገባ ባፍንጫየ ዘልቆ አሁን ይሸተኛል ከጎኔ እርቆ እናቴ ልበልሽ መጠሪያ ባይኖርሽ ናፍቆትሽ ይበቃል ከጉያሽ መዋሉ እኔን ይጎደኛል ፈገግታሽ መጉደሉ ትዝ ይለኛል ሳቅሽ ጭንቀት ተሸክሞ ሀዘን ተጫጭኖት ያላወኩት ነገር በሀሳብ አፍኖት ትዝ ይለኛል አይንሽ በስስት እያየኝ ሳይነቀል ላፍታ ሰቅሎ ሲክበኝ ከላዩ ከፍታ የኔ የኔ ብየ ዜማ አላወጣው ለምን እንዳትይኝ አንዴ ልበልሽ እኔ ወድሻለው አዚህ ተቀምጨ ሳቅሽን አሸታለው ጠረንሽ ልዩ ነው አስከዛሬ ስኖር ሁኘ በምድር ላይ ካንቺ የምትበልጥ አሎጣችም ፀሀይ እውነት ከምሬ ነው ጨረቃ ብትወጣ ብርሀን ብትሰጠኝ ከሳቅሽ አውጥታ መቸ ልትሰደኝ እኔ ወድሻለሁ እናፍቅሻለሁ እጠብቅሻለሁ ባካል ብንራራቅ ድምፅሽ ይሰማኛል ለሊት አስነስቶ በብርድ ያሞቀኛል ከምበላው ምግብ ከውሀ አብልጦ እንባሽን ማየቱ ይጥለኛል ቆርጦ ውበትሽ ልክ የለው ባይኖቸ የማይሽ አደለም አፍጥጨ በፎቶ ሳይቀረኝ አልጠግብሽ መጥጨ የኔ እናት ነሽ አንቺ ዝቅ አትበይ በርቺ ሀዘንሽን ተፋቺ ጠሎትሽን ደብቺ ከሳቄ ቀንሶ ለሳቅሽ ይገበር ከድሜየ ጨምሮ ለእድሜሽ ይጨመር ይጨመር ይጨመር አሁንም ይጨመር እግሬ መዳፍ ይሁን ባጭሩ ይቀንጨር ላንቺ ብቻ ልኑር እናቴ እናቴ ሁልጊዜ ልበልሽ እንባሽን ጠርጌ በሳቅ ላብስልሽ በልቤ አትሜ ዘወትር ላኑርሽ እናቴ እናቴ እሱ ይጠብቅሽ እናቴ❤❤❤❤ ✍🏾ሀሊድ
አግብተሻል ወይስ አላገባሽም አግብተሽ ከሆነም ደግ ካልሆነም ይጠቅምሻልና እነዚህን ሶስት ነጥቦች መቸም ቢሆን አትዘንጊያቸው፦ 1,ስለባልሽ ችግር መቼም ቢሆን ለባልሽ ቤተሰቦች አታማክሪ...ባብዛኛው እነሱ ከርሱ ጎን እንጂ ካንቺ ጎን አይቆሙም። 2,ባልሽ የሚረብሽሽ፣ የማያስደስትሽ፣ የሚበድልሽ ከሆነ ለቤተሰቦችሽ መቼም እንዳትነግሪያቸው...ምክንያቱም አንቺ ረስተሽው ህይወትሽን ስትቀጥይ እነሱ ይቅር አይሉትም። 3,የቤትሽን እና የትዳርሽን ጉዳይ በፍጡም ለሴት ጓደኛሽ አትንገሪ...አንቺ ትተሽው ስትሄጅ እርሷ እንደ ጤፍ ትዘራልሻለች Amharic_audio_book
видео или голосовое, без подписи
እድሜ ይስጣት ለእሷ ሆኜ ቀርቻለሁ የህመም ጎተራ እረስቶኛል ዘመድ ከወጣሁ ቆየሁኝ ከሰውነት ተራ ያለማንገራገር ሞተች ቢሉኝ እንኳን ከንፍሮ ልዘግን እገባለሁ ድንኳን ስራዋን ለማያውቅ ነገሬ ቢመርም አርባዋን በልቼ... “ለአመቱ ያድርሰን!" ማለቴ አይቀርም በእውነተኛ ታሪክ ላይ ያልተመሰረተ! ✍️ ሚኪ @ethiopianye
እንዴት ነው ነገሩ? #ኑረዲን_ኢሳ እንዴት ነው ነገሩ? ብንሄድ ብንሄድ ጎዳናው አያልቅም ፣ ሽቅብ ብናንጋጥጥ ጀንበር አትጠልቅም ፣ ጊዜ ቆሟል መሰል አይነቃነቅም ፣ ጋሪያችን ይሮጣል እኛ አንንፏቀቅም ። እንዴት ነው ነገሩ? ዒሻራ 📚 27 - 1 - 95 ዓ.ም @ethiopianye
✍️@ediwub @ethiopianye
አንዱ ለአገሩ ፤ አንዱ ለ'ርስቱ ፤ አንዱ ለልጁ ፤ አንዱ ለሚስቱ ፤ ጥይት ወልውሎ ፤ ጎራዴ ስሎ ፤ በዱር በገደል ይከታከታል ፤ ሲሻው ይገድላል ፤ ሲሻው ይሞታል ። እኔ ግን ወዲህ . . . ወይ አገር የለኝ ፤ ወይ ርስት የለኝ ፤ ወይ ልጅ አልወለድኩ ፤ ሚስት አላደለኝ ፤ ጎራዴ ሳልስል ፤ ጥይት ሳልገዛ ፤ በተኛሁበት ሀሳብ ገደለኝ ። #ቴውድሮስ_ካሳ @ethiopianye
ሁለት ልጃገረዶች (©አዳም ረታ) ከ'ከሰማይ የወረደ ፍርፍር ' ቅዳሜ ቅዳሜ ማታ በዙረቴ የማልደርስበት የከተማችን ክፍል የለም ። ሳምንት ወይ አስራ አምስት ቀን ሙሉ ከቤት ሳልወጣ እቆይና እመሽግና አንድ ቅዳሜ መርጬ ከወጣሁ ግን የምመለሰው ተበለሻሽቼ ነው ። በደንቤ ሳምንት ሁለት ሳምንት ሙሉ ከቤት አልወጣም ....... ከእሁድ እስከ ዓርብ ። ብዙ ጊዜ ቅዳሜ ግን ከምሽቱ አስራ አንድ ሰዓት ጀምሮ እግሮቼ የማያርፉበት የከተማዋ ክፍል የለም። ከፒያሳ በሜክሲኮ አደባባይ አድርጎ ቄራ። በፒያሳ በሐብተጊዮርጊስ ድልድይ አድርጎ በመርካቶ በሰባተኛ እስከ ልደታ። እንደ አውሬ ነው የሚያደርገኝ። በዚያን ዕለት የማውቀውን ማንንም ሰው መገናኘት አልፈልግም ። በሕይወቴ ወጥ ውስጥ ትንንሽ የእብደት ቅርንፉድ የልክስክስነት ኮረሪማ የባለጌነት ነጭ ሽንኩርት የደደብነት ጥቁር አዝሙድ ...... የመሳሰለ ልጭምርባት እፈልጋለሁ ። እነዚህ ቅመሞች ያሉበትን ሐጢያታዊ ማታና ምሽት ከሰዎች ጋር ልኖራት ግን አልፈልግም ። ይኽቺን አይነት እብደት ከሚያውቁት ሰው ጋር ሆነው ሲሰሯት ትቀጥናለች ። ትዕዝብት ፣ ትችት ፣ 'ይቅርብህ' 'ጥሩ አይደለም' 'ይደብራል' የተሰኙ ቃላቶችና የሚከስቱዋቸው ስሜቶች ይወረወሩብኛል ። በቂ ነፃነት የለውም ። ያቺ የእብደት ቀኔ የፍፁም ነፃነት ቀኔ ናት። አዲስአባ . . . የቅዳሜ አዲስአባ የእኔ ጦሮ ሜዳ ናት ። ፊታውራሪ እኔ ፣ ተራ ወታደሩ እኔ ። አዛዥ እኔ ነኝ ታዛዥ እኔ ። የግሌም ካርኒቫል ነው። @ethiopianye
መፍትሔ በር መስኮት ዘግተህ ፣ ቀዳዳዎች ደፍነህ ፣ የለኮስከው ሻማ "በራ !" ፣ "ጠፋ!" ካለ ፤ ጠርጥር ! ቤት ያፈራው ንፋስ ከጎጆህ እንዳለ ? ©በረከት በላይነህ @ethiopianye
видео или голосовое, без подписи
ወርቅ እና ዝምታ ዝምታ ወርቅ ነው የምትሉት ፈሊጥ ውዳሴ አላዋቂ ከሊቅ እስከ ደቂቅ አርምሞን ለማድቀቅ የምታቦኩት ሊጥ ኩፍ ብሎላቹ በአፋቹ ሰፌድ ተጋግሮ የወጣው የታል እንጀራቹ #ብሩህ @ethiopianye
ጥርሷ ሰዋሪ ሳቋ ነዳፊ ፤ ከንፈሯ ገዳይ ዐይኗ ገራፊ ፤ ፀጉሯ ሐመልማል ልብሷ ደመና ፤ ገላዋ አበባ ቃናዋ ናና ፤ ልክ እንደ ሰንደል ልክ እንደ ብርጉድ ፤ የቀመሷት ለት የምታስብል ጉድ ! ከሰማይ በቀር የምድር አፈር የማይመጥናት ፤ ከመለዓክ በቀር በሳር በቅጠል የማይመስሏት ፤ ልጅማ ልጅ ናት ! ጨረቃ ኮኮብ የሚሰግዱላት አበቦች ከዱር የሚያረግዱላት ፤ የሚገድሉላት የሚሞቱላት ከአንቺ ጋ አድሬ ሲነጋ ልሙት የሚዘፍኑላት ፤ ልጅማ ልጅ ናት ! ሲሻት በምድር ሲሻት በሰማይ የምታበራ ፤ ነፍስ የምታስት ስትስቅ ስትኮራ ፤ እንኳን ለአዘቦት ለክት ለዓመት ባል የሚሸሽጓት ፤ እንኳን በፀሐይ ሌት በጨረቃ በሩቅ የሚያውቋት ፤ ልጅማ ልጅ ናት ! እንኳን ቁሞ ሃጅ ሙቶ የተኛን ታሳብዳለች ፤ እንኳን የሰው ዘር ባህሩን ወንዙን ታስረግዳለች ፤ ከፍቅር በቀር ሌላ አይችላትም ፤ ከራሷ በቀር የቱም አበባ አይመጥናትም ፤ የምድር ዕንቁ ናት የምድር አበባ ፤ እንዲሁ ታይታ ዐይን የምትገባ ፤ እንዲሁ ታይታ ቀን ታፈካለች ፤ በዐይኖቿ ብቻ ውኃን ወደ ወይን ትቀይራለች ፤ ለባህር ዛጎል ለሰማይ ኮኮብ ለምድር አደይ ናት ፤ እንኳንስ ቁሜ ስሞት ከጎኔ ትብቀል የሚሏት ፤ ልጅማ ልጅ ናት ከአንድ እኔ በቀር ሌላ የሰው ዘር የማይመጥናት ። ቴዎድሮስ ካሳ @ethiopianye
በምን ይገለጻል፥ የትውልዴ አበሣ ከመንበርከክ ብዛት ፥ መራመድ የረሣ ያልፋል ተለጉሞ ያልፋል ተከርችሞ የጉልበቱን ኮቴ፥ ምድር ላይ አትሞ። #ብሩህ @ethiopianye
ቲማቲም ወርውሮ ትናንትና አንድ ሰው አንዱን ጓደኛውን ግንባሩን ገመሰው ደነገጥኩ አይቼ ሲዠቀዠቅ ደሙ በጣሳ ውስጥ ነበር ለካስ ቲማቲሙ። #ብሩህ @ethiopianye
ካየኽኝ ብሩህ ዓለም ***** ላይሰናስል ሳዳውር፤ ላይጠረቃ ሳጋብስ፤ አለሁ እንዳጋሰስ። ላይከትም ከአቦል ጀምሬ፣ በረካ አልባ ቡን ሳንቃርር፣ የማይፈፀም ሩጫ ገጥሜ፣ በባእዳን ውርጭ ጠይሜ፣ ስኳትን ቅስሜን ቀልሜ “ቃል” ላይወጣኝ ተለጉሜ፣ “ኖሯል” ካሉ ፥ ይኸው አለሁ። የቅኔ ቆሌዬ በኖ፤ ዲዳነት ቋንቋዬ ሆኖ፤ ደስታ ጣእሙ ጠፍቶ፤ በአልጫ ኑሮ ተተክቶ፤ ከተማ ሳለሁ ድብርት፤ ከአሸን መሃል ብቸኝነት፤ ምን ትል ይሆን የኔ አባት! ያየህ እንደው ድንገት ተዚ እዛ ስቧከት። #ብሩህ @ethiopianye
እናቴ 🥰 . . . ቢጨላልም ንጋት ቀኗ፤ ሲደካክም ወገብ ጎኗ፤ ማጀት ቤቷ ቢጎድልባት፤ ስቃይ ችግር ቢደቁሳት፤ በሀዘን ጊዜ በደስታዋ፤ አይከደን ሁሌም ጥርስዋ፤ ብትከፋ ምን ቢያደማት፤ ፈገግታ ነዉ የሚቀድማት። ...................................... #በዔደን_ታደሰ @ediwub @ethiopianye
የታቦር ደብር ብሩህ ዓለም *** ክርስቶስን መኖር ሊታዘብ ተገኝ ያረገው ኤልያስ፣ #ያምላክን ፊት ጉጉት ሙሴንም ጎትቶ ጀርባውን ሊያሳየው አነቃው ከመንፈስ። ይህ ደብረ ታቦር ነው፣ ሊመሰክር ሲዋጅ አምላክ ሲል ልጄ ነው። ዘመናችን የት ነው መቼ ነው መንቂያችን፣ ሺ ታቦር አለፈ ነውራችን በሀላል እየለፈለፈ። #ብሩህ_ዓለም @ethiopianye