፭ኛ ዓመት ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ [ 2015 ዓ.ም ባች ]
Статистикаበኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤት ማደራጃ እና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን አ.አ ማዕከል አምስት ኪሎ ግቢ ጉባኤ። ለማንኛውም መንፈሳዊ እና Academic ጥያቄ እንዲሁም በግቢ ውስጥ ለሚገጥማችሁ ችግር በእነዚህ ስልክ ቁጥሮች ደውሉ፤ +2519 36 74 7516 አቤኔዘር አዱኛ( @abenelec ) +2519 29 70 3755 እፁብድንቅ አወቀ
- Последний пост
- 11 авг.
- Последнее чтение
- 13 авг.
- Постов за неделю
- 1
- Всего постов
- 21
- Тип
- открытый
- Язык
- am
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 59
- 1/48двое суток
- 67
- 1/72трое суток
- 72
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
አሜን እግዚአብሔር ይባርከነ ለአግብርቲሁ በሰላም፤ ሥርየተ ይኩነነ ዘተመጦነ ሥጋከ ወደመከ፤ አብሐነ በመንፈስ ንኪድ ኵሎ ኃይሎ ለጸላዒ፤ በረከተ እዴከ ቅድስት እንተ ምልእተ ምሕረት ኪያሃ ንሴፎ ኲልነ፤ እምኵሉ ምግባረ እኩይ አግኅሠነ ወውስተ ኵሉ ምግባረ ሠናይ ደምረነ፤ ቡሩክ ዘወሀበነ ሥጋሁ ቅዱሰ ወደሞ ክቡረ። አሜን እግዚአብሔር እኛን ባሮቹን በሰላም ይባርከን:: የተቀበልነው ሥጋህና ደምህ ለሥርየት ይሁነን:: የጠላትን ኀይል ሁሉ በመንፈስ እንረግጥ ዘንድ አሠልጥነን∶: ምሕረትን የተመላች ክብርት የምትሆን የእጅህን በረከት ሁላችን ተስፋ እናደርጋለን ከክፉ ሥራ ሁሉ አርቀን በበጎውም ሥራ ሁሉ አንድ አድርገን:: ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙንም የሰጠን ቡሩክ ነው:: ♦️መጽሐፈ ቅዳሴ ✨በሥጋ ወደሙ ከብራችሁ የክርስቶስ ሙሽሮች የሆናችሁ ሁሉ እንኳን ለዚህ አበቃችሁ!!! በሂደት ላይ ያለንንም ለዚህ ክብር ያብቃን🙏 📍ሁለተኛው ዙር የምሥጢር ቀናችን ቀጣይ ሳምንት ረቡዕ ነሐሴ 12 ስለሚሆን እራሳችንን እናዘጋጅ። ረድኤተ እግዚአብሔር አይለየን! ንስሐ ንዑስ ክፍል ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ
Channel name was changed to «፭ኛ ዓመት ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ [ 2015 ዓ.ም ባች ]»
"በትረ አሮን እንተ ሠረፀት ዘእንበለ ተክል።ወኢሰቀይዋ ማየከማሃ አንቲኒ አ ወላዲተ ክርስቶስ አምላክነ ዘበአማን - ሳይተክሏት የበቀለች፤ ውሃ ሳያጠጧት የለመለመች፣ ያበበች፣ ያፈራች የአሮን በትር ነበረች። አምላካችንን የወለድሽልን አንቺም እንደርሷ ነሽ፤ " እንዴት የአንድ ሰው ልጆች ክህነት ከምስፍና ተሾመው ሲገዙ ይኖራሉን ብለው መሳፍንቱ ደቂቀ ሮቤል በሙሴ ላይ ካህናቱ ደቂቀ ቀዓት በአሮን ላይ ተነሱ ። እኛስ የበኩር የሮቤል ልጆች አይደለንም ፤ እኛስ የሌዊ ልጆች አይደለንም ብለው በጠላትነት ተነሥተዋል። ከዚህ በኋላ ሁላችን በአንድነት ስንይዝ ጊዜ የምቀኝነት እንደሆነ ሕዝቡ ያውቁብናል፤ አስቀድመን እኛ በሙሴ ዳኝነት አሮንን ይዘን ክህነቱን በእኛ እጅ ካደረግነው፤ በኃላ በኛ ዳኝነት ይዛችሁ ምስፍናውን እጅ ታደርጋላችሁ አሏቸው። ከዚህ በኋላ ሄደው ሙሴን ሹመት በተርታ ሥጋ በገበታ ነው፤ እኛስ ከሌዊ ተወልደን የለምን፤ እኛንም ሹሙን አሉት። እርሱም አሮን ከእግዚአብሔር አግኝቶ ተሾሟል፤ እናንተም ከእግዚአብሔር አግኝታችሁ ተሾሙ አላቸዉ፤ ይህም ለወንድሙ ማደላቱ አይደለም ብለው ከሁለት መቶ የሚበዙ ካህናት ማዕጠንተ ብረታቸውን አሰርተው ልብሰ ተክህኖ ለብሰው ሊያጥኑ ገቡ፤ ሲገቡ ሙሴና አሮን ከደብተራ ኦሪት ቆመው ቢያዩአቸው ገረመሟቸው። ከዚህ በኋላ ገብተው ሲያጥኑ ጢሰ ቅታሬው ቢነካቸው ልብሳቸውን ሳይነካ ሰውነታቸውን እንደ ተለበለበ ግንድ አድርጓቸዋል፤ ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት በልብሳቸው እያጎናጸፍህ አውጥተህ አፍስሳቸው ብሎታል፤ ያንን ግን ወተቀደሳ ማዕጠንታቲሆሙ በነፍሳቲሆሙ እንዲል፤ ለቤተ መቅደስ ዕቃ አድርገው ብሎታል። ዳታንና አቤሮንን ከነ ቤተሰባቸው ከነ ከብታቸው ከነ ድንኳናቸው ምድር ተከፍታ አስጥማቸዋለች፤ ቆሬም ምክር ሊያጸና ሄዶ በአንድ ሰጥሞ ቀርቷል። ከዚህ በኋላ ይህ ሁሉ ኃጢአታችንን እያዘከሩ የሚያስፈጁን እነዚህ አይደሉምን ብለው ሊወግሯቸው ድንጋይ ድንጋያቸውን አንስተው ቢሄዱባቸው ሸሽተው ከደብተራ ኦሪት ገቡ። ዓምደ ብርሃን ተተከለ ጌታቸው ወጣ ብለው ተመልሰዋል። ከዚህ በኋላ አሮን እስከ መቼ ድረስ እንዲህ እያልህ ትኖራለህ፤ ክህነት ከቤትህ እንደሚወጣ ምልክት አሳይሃለሁና፤ ወንድምህ ሙሴ የአሥራሁለቱን ነገድ በትራቸውን ሰብስቦ በቀዳማይ ሰዓት ሌሊት አግብቶ ከቤተ መቅደስ በቀዳማይ ሰዓት መዓልት ያውጣው፤ አለው። የአሥራሁለቱን ነገድ በትር ሰብስቦ አሮንም የአባቱ የሌዊ በትር ነበረች፤ ያችን አምጥቷል። በቀዳማይ ሰዓት ሌሊት አግብቶ በቀዳማይ ሰዓት መዓልት ቢያወጣው የአሮን በትር ሳይተክሏት ውኃ ሳይጠጧት ለምልማ አብባ አፍርታ ተገኝታለች፤ አሥራሁለት በኵረ ሎሚ አፍርታ ተገኝታለች። እንደዚህም ሁሉ እመቤታችን ከቤተ መቅደስ አሥራሁለት ዓመት ኖራ፣ ጌታን ፀንሳ ተገኝታለችና። ከእሑድ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ የተወሰደ
"የምሥጢር ቀን" — 2 ቀን ብቻ ቀረው! ⏳✨ "የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም።" (ዮሐ 6፥35) ለመጀመሪያው ዙር የምሥጢር ቀን 2 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! 📅 ማክሰኞ ነሐሴ 5 #የምሥጢር_ቀን #5_ኪሎ_ግቢ_ጉባኤ
“ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።” ዮሐንስ 6፥54 ለመጀመሪያው ዙር የምሥጢር ቀን 3 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! 📅 ማክሰኞ ነሐሴ 5 ንስሐ ንዑስ ክፍል ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ
የነሐሴ ፩ ምስባክ "ወእነግር ስምዐከ በቅድመ ነገሥት ወኢይትኀፈር ። ወአነብብ ትእዛዘከ ዘአፍቀርኩ ጥቀ። ወአነሥእ ዕደውየ ኀበ ትእዛዝከ ዘአፍቀርኩ"። መዝ 118፥46-47 መዝሙር 118 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴⁶ በነገሥታት ፊት ምስክርህን እናገራለሁ፥ አላፍርምም፤ ⁴⁷ እጅግም በወደድኋቸው በትእዛዛትህ ደስ ይለኛል። ⁴⁸ እጆቼንም ወደ ወደድኋቸው ወደ ትእዛዛትህ አነሣለሁ፤ ሥርዓትህንም አሰላስላሁ። ምንባባት 1ኛ ጢሞ 5፥1-11 1ኛ ዮሐ 5፥1-6፣ የሐዋ ሥራ 5፥26-34 ዮሐ 19፥38 - ፍ.ም ቅዳሴ ቅዳሴ ዘእግዝእትነ ማርያም የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። እንኳን ለጾመ ፍልሰታ በሰላም አደረሰን። የበረከት ጾም ያድርግልን።
ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና። ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ። ዮሐንስ 6፥54 📍የንስሐ ወር :- 4ኛ ሳምንት ንስሐ ንዑስ ክፍል ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ
ቊርባን ምን ማለት ነው? 🔅ቊርባን፦ ቃሉ ከሱርስት የተወሰደ ሲሆን፣ መስዋዕት ማለት ነው። እንዲሁም ቊርባን ሙሉ ትርጉሙ ለአምላክ የሚቀርብ መንፈሳዊ መባዕ ፣ ስጦታ፣ አምኃ፣ ማለት ነው። አንድም ሥጋውና ደሙ የተሰጠን በነፃ ያለ ዋጋ በችሮታ ነውና ቁርባን ስጦታ ይባላል። 🔅ምሥጢረ ቁርባን ክርስቶስ ስለ እኛ ኃጢአት በመስቀል ላይ መሥዋዕት ሆኖ በሥጋው በመሞቱ የዓለምን ኃጢአት ያስወገደበት፥ የዘላለም ሕይወትን ያስገኘበት የመዳናችን መሠረት፥ የጸጋችን ሁሉ ምንጭ የሆነውን የቅዱስ ሥጋውንና የክቡር ደሙን የማዳን ስራ የምንማርበት ታላቁ የሃይማኖታችን ትምህርት ነው። ማንኛውንም ጥያቄ ካላችሁ እኛን ማግኘት ትችላላችሁ፦ 👉 ዲ/ን ኅሩይ 0939776522 | @hiruy19 👉 እሱባለው +251908685959 | @Pet_6King ንስሐ ንዑስ ክፍል ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ
በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። 1 ዮሐንስ 1፥9 ውድ የግቢ ጉባኤ ቤተሰቦች ከሐምሌ 6 ጀምሮ የተጀመረው የንስሐ ወር ተጋምሷል። "እስካሁን የንስሐ አባት የሌለን አባት በመያዝ፣ ያለን ደግሞ ወደ አባቶቻችን በመቅረብና በመናዘዝ ሕይወታችንን እናድስ።" 📍የንስሐ ወር :- 3ኛ ሳምንት ንስሐ ንዑስ ክፍል ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ
አቤል ይባላል የግቢ ጉባኤያችን አባልና የ12ኛ ክፍል ተማሪ ነው። አሁን ግን እንደምትመለከቱት አደጋ አጋጥሞት የእኛን እርዳታ ይፈልጋልና የምንችለውን ያህል ከላይ በተጠቀሱት አካውንቶች በመላክ እናግዘው። ማጋራትም እርዳታ ነውና ይህን ፖስት ለምናውቃቸው ሰዎች በማድረስ እነርሱም እንዲያግዙ እናድርግ
ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፤ #ክረምትን_በትምህርት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ የምክክር ንዑስ ክፍል በOnline የሚሰጥ የዕቅበተ እምነት ሥልጠና በዚህ ክረምት ሊጀምር ነው። የትምህርቱ ዓላማም ሃይማኖታችንን አውቀን እምነታችንን እንድንገነባ እና ያሉብንን የተለያዩ ጥያቄዎች በአግባቡ መመለስ እንድንችል አቅም መፍጠር ነው። "ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ" - 1ኛ ጴጥሮስ 3፥15 በሥልጠናውም ከሚሰጡ ትምህርቶች መካከል፡ 🔸 የፈጣሪ መኖር ማስረጃዎች 🔸 እዉነተኛዋ ቤተክርስትያን ኦርቶዶክስ መሆኗን ማረጋገጫዎች 🔸 መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ፥ እምነት ብቻ፥ ወዘተ. የሚሉት የprotestantism ትምህርቶች ችግር ምንድን ነው? 🔸 በነገረ ማርያም እና በነገረ ቅዱሳን ላይ የሚነሱ ጥያቄዎች 🔸 ድኅነት ምንድን ነው? ለመዳን ምን ያስፈልጋል? እነዚህና የተለያዩ ጉዳዮች ይካተታሉ። ስልጠናው የሚሰጠው በታላላቅ መምህራን ሲሆን ለሰላጣኞችም ተጨማሪ መማሪያ ማቴሪያሎችና ቪድዮዎች የሚላኩ ይሆናል። ስለሆነም ይኽን ሥልጠና መሳተፍ የምትፈልጉ ከታች ያለውን goggle form በመሙላት መመዝገብ ትችላላችሁ። https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScBMPmCEhCz2SFi0zBoJuC1cIu59Ycej_oTAHMJmi4tiMqxWg/viewform?usp=header ምክክር ንዑስ ክፍል ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ
без подписи
без подписи
ዛሬ እሑድ ሰኔ 14 ምሽት 11:30 📍ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 3ኛ ፎቅ ልዩ የተመራቂ ተማሪዎች የእራት እና የምስጋና መርሐ ግብር
📍ልዩ የተመራቂ ተማሪዎች የእራት እና የምስጋና መርሐ ግብር .... ደረሰ ደረሰ ... 📆 የ2018 ዓ.ም የተመራቂዎች የእራት እና የምስጋና መርሐ ግብር ነገ እሑድ ሰኔ 14 ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ... ትኬቱን ቆርጠዋል .... ? እስከ ነገ እሑድ ቀን 6 ሰዓት ድረስ ትኬትዎን ገዝተው ይያዙ፤ በእነዚህ ስልኮች ይደውሉ፤ ወይም በቴሌግራም username ይጻፉልን፤ @habib_georgis 0989860118 @buhe19 +251972777045 @natinael96 +251946100695 @malk_iel +251946162878 @SenanTesfaye +251915761537 @Natalaam +251967255318 ሊያመልጠን የማይገባ "በጎ ዕድል" ሉቃ 10 ፣ 42
የተወደዳችሁ ምሩቃን የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን ቆያችሁ? ✡️ አንድ ብሎ አስጀምሮን ለዓመቱ ማብቂያ ያደረሰን የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ስሙ የተመሰገነ ይሁን። + የመማሪያ ጊዜያችን አብቅቶ ምን ያህል እንደተረዳን የምንገመገምበት የመውጫ ፈተና ጊዜ ከፊታችን መጥቷል። በዚህችም ወቅት ረድኤተ እግዚአብሔርን በመሻት ወደላይ እናንጋጥ። በህይወቴ ሁሉ በትምህርት ጊዜዬም ያልተለየኸኝ አምላክ ሆይ ዛሬም ከጎኔ እንድትሆን እሻለሁ በማለት በፍቅርና በትህትና ስርዓት እንዲህ ብለን እንማጸነው: አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ: "በችግርህ ጊዜ ጥራኝ ፤ አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ" ብለህ የአንተን መጠጊያነት መፈለግን ስላስተማርከኝ አመሰግንሃለሁ! ✝️ አሁንም ጌታ ሆይ በዚህ የፈተና ሰዓት ጥበብና ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እማጸንሃለሁ። ይህን ፈተና በሰላም አልፍ ዘንድ ጸጋን ሞገስንም ስጠኝ። አቤቱ ፈተናውን በምሰራ ጊዜ ጥልቅ የሆነ ሰላምህንና በረከትህን አድለኝ። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ውጤት በሚሰጡኝ ጊዜ በመምህራኖቼ ዓይን መወደድን ትሰጠኝና ልቡናቸውንም ታለሰልስልኝ ዘንድም እለምንሃለሁ። ✝️ የከበርከው ጌታ እኔ ኃጢአተኛ ነኝ ዓመቱን ሙሉ አንተን ደስ አላሰኘሁም፤ ውስጤንም ጭምር፤ ነገር ግን ከልቤ ደንዳናነትና ከኃጢአቶቼ የተነሳ ሳይሆን ከምህረትህ እና ከርኅራኄህ የተነሳ እንድትረዳኝ እለምንሃለሁ። ✝️ ጌታ ሆይ "ለምኑ ይሰጣችሁዋል፣ እሹ ታገኛላችሁ፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል" ብለሃልና እነሆኝ እኔ ልጅህ እየለመንኩህ ነው፤ የምህረት ደጅህን እያንኳኳሁኝም ነው። "ወደ እኔ የሚመጣውን ከቶ ከእኔ አላወጣውም" ብለሃልና ጸሎቴን አትናቅ። ለእኔና ለወንድሞቼ ለእህቶቼም ሁሉ ቸርነትህን አድርግ። ስለዚህም በቅድስተ ቅዱሳን በድንግል እናትህ ግሩማን ክቡራን በሚሆኑ መላዕክትህ ደማቸውን ስላንተ ስላፈሰሱ ሰማዕታት በምድር በመልካም ስለተጋደሉ ጻድቃን ስለቅዱስ መስቀልህም ስትል ስማን‼️ "አቡነ ቄርሎስ ሣድሳዊ" እንግዲህስ ይህን ካልን፤ እኛም የበኩላችንን ከተጋን እግዚአብሔርን የህይወታችን መታመኛ አድርገናልና ምን ያስፈራናል። በስኬት የምንወጣው ፈተና ይሁንልን። እመብርሃን የሰላም ካባን የመረጋጋት ዘውድ የስኬት አክሊልንም ታቀዳጀን ‼️ ቅዱስ ሚካኤል በረድኤቱ ከጎናችን ይሁን!!! መልካም ፈተና ለሙውጫ ፍተና(Exit exam) ተፈታኞች በሙሉ ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! ፭ ኪሎ ግቢ ጉባኤ
እሑድ አይቀርም!!! ትኬትዎን በእጅዎ ይዘዋል?😋
📍ልዩ የተመራቂ ተማሪዎች የእራት እና የምስጋና መርሐ ግብር 📌 የ2017 ዓ.ም ተመራቂዎች መርሐ ግብር በጥቂቱ ይህን ይመስል ነበር ፤ 📆 የ2018 ዓ.ም የተመራቂዎች የእራት እና የምስጋና መርሐ ግብር ደግሞ እሑድ ሰኔ 14 ከምሽቱ 11:30 ጀምሮ ይካሄዳል፤ ትኬቱን ቆርጠው ቦታዎን ይዘዋል? ካልያዙ ቀድመው ቦታዎን ይያዙ... በእነዚህ ስልኮች ይደውሉ፤ ወይም በቴሌግራም username ይጻፉልን፤ @habib_georgis 0989860118 @buhe19 +251972777045 @natinael96 +251946100695 @malk_iel +251946162878 @SenanTesfaye +251915761537 @Natalaam +251967255318 ሊያመልጠን የማይገባ "በጎ ዕድል" ሉቃ 10 ፣ 42
“ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ።” መዝ. 118፥26 ልዩ የዝማሬ እና የእራት መርሐ ግብር 📍 እሑድ ሰኔ 14 ምሽት ከ11:30 ጀምሮ 📍 በማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 3ኛ ፎቅ አዳራሽ የተመራቂ ተማሪዎች የመጨረሻ መርሐግብር .... በመርሐግብሩም ዝማሬ እራት (የፆም ብፌ) photo ሹት (unlimited) የመርሐ ግብሩን ትኬት ከዚህ በታች ባሉት Telegram Username እና ስልክ በመደወል ቀድማችሁ ቦታዎን ይያዙ፤ @habibgeorgis 0989860118 @buhe19 +251972777045 @natinael96 +251946100695 @malk_iel +251946162878 @SenanTesfaye +251915761537 @Natalaam +251967255318 ሊያመልጠን የማይገባ "በጎ ዕድል" ሉቃ 10 ፣ 42
📍ልዩ የተመራቂ ተማሪዎች የእራት እና የምስጋና መርሐ ግብር 📆 በቅርብ ቀን...