- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 2
- Всего постов
- 22
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Криптовалюты (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 231
- 1/48двое суток
- 264
- 1/72трое суток
- 285
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
“አንዳችሁ አላመነም ‘እምነቱ ሙሉ አይሆንም’ እኔ እሱ ዘንድ ከልጆቹ ከወላጆቹ ከሰዎች በጠቅላላ ይበልጥ ተወዳጅ እስክሆን ድረስ።” የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) SHARE 👉 @NURU_TURKII
“በጁምዓ ቀንና በጁምዓ ሌሊት በኔ ላይ ሰለዋትን አብዙ።” የአላህ መልእክተኛ ﷺ SHARE 👉 @NURU_TURKII
SHARE 👉 @NURU_TURKII
“ከቀናችሁ ሁሉ በላጩ የጁምዓ ቀን ነው። በዚህ ቀን በኔ ላይ ሰለዋት ማውረድ አብዙ። ሰለዋታችሁ ለኔ ይቀርብልኛልና።” ረሱል (ﷺ) SHARE 👉 @NURU_TURKII
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ከስግደቶች አላህ ዘንድ በላጩ የዕለተ ጁሙዓን ሱብሂ ሶላት በጀማዐሕ መስገድ ነው።» ሶሂሁል ጃሚዕ 1119) #ሰሉአለነቢይ SHARE 👉 @NURU_TURKII
ለ አንድ ባሪያ ምርጡ ቀን ማለት፤ወደ አላህ ከልቡ የተመለሰበት ቀን ነው። ኢብኑል ጀውዚ SHARE 👉 @NURU_TURKII
“በጁምዓ ቀንና በጁምዓ ሌሊት በኔ ላይ ሰለዋትን አብዙ።” የአላህ መልእክተኛ ﷺ SHARE 👉 @NURU_TURKII
без подписи
“ከቀናችሁ ሁሉ በላጩ የጁምዓ ቀን ነው። በዚህ ቀን በኔ ላይ ሰለዋት ማውረድ አብዙ። ሰለዋታችሁ ለኔ ይቀርብልኛልና።” ረሱል (ﷺ) SHARE 👉 @NURU_TURKII
“በትንሳዔ ዕለት የስራ መዝገቡ አስደስቶት መመልከትን የወደደ እስቲግፋር ማድረግ ያብዛ።” ረሱል (ﷺ) ሰሉ አለ ነብይ SHARE 👉 @NURU_TURKII
“ሌሊት መስገድን አስቦ ወደ ፍራሹ የሄደ ከዚያም እስከ ንጋት ዓይኑ ያሸነፈችው ያሰበውን አላህ ይፅፍለታል፤ እንቅልፉም ከጌታው ዘንድ ሶደቃ ይሆንለታል” የአላህ መልእክተኛ ﷺ SHARE 👉 @NURU_TURKII
“በጁምዓ ቀንና በጁምዓ ሌሊት በኔ ላይ ሰለዋትን አብዙ።” የአላህ መልእክተኛ ﷺ SHARE 👉 @NURU_TURKII
“አንድ ባሪያ ወንጀል በሚፈፅምበት ወቅት ውዱእ በትክክል ያድርግ፡፡ ከዚያም ሁለት ረከዓዎችን ይስገድና አላህን ምህረት ይማፀን፡፡ አላህ ምህረትን ይለግሰዋል፡፡” ረሱል (ﷺ) SHARE 👉 @NURU_TURKII
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ከስግደቶች አላህ ዘንድ በላጩ የዕለተ ጁሙዓን ሱብሂ ሶላት በጀማዐሕ መስገድ ነው።» ሶሂሁል ጃሚዕ 1119) #ሰሉአለነቢይ SHARE 👉 @NURU_TURKII
“በጁምዓ ቀንና በጁምዓ ሌሊት በኔ ላይ ሰለዋትን አብዙ።” የአላህ መልእክተኛ ﷺ SHARE 👉 @NURU_TURKII
የዓሹራእ ጾም ትሩፋት (ፈድል) ✅✅✅✅✅✅✅✅ የአቡ ቀታዳህ አል-አንሷሪ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ሐዲስ: حديث أبي قتادة الأنصاري رضي الله عنه: أن النبي صلى الله عليه وسلم سُئل عن صيام يوم عاشوراء، فقال: "يُكَفِّرُ السَّنَةَ المَاضِيَةَ" (رواه مسلم). ከአቢቀታዳ አል-አንሷሪ (ረ.ዐ) እንደተላለፈው የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) ስለ አሹራ (የሙሐረም ወር 10ኛ ቀን) ጾም ተጠየቁ፡፡ “የአሹራ ቀን ጾም ያለፈውን ዓመት ወንጀል ያስምራል፡፡” ሲሉ መለሱ፡፡ (ሶሒሕ አል-ሙስሊም)፡፡ ሙስሊሞችም ሙሳና ተከታዮቹ በፊርዐውን ላይ ድል የተቀዳጁበትንና ነጻነታቸውን ያወጁበትን ቀን በጾም ያስታውሱታል፡፡ ታሪኩንም በማውሳት ይማማሩታል፡፡ የሙሳና ተከታዮቹ ድል የነርሱም ድል በመሆኑ፡፡ በአምባገነኑ ፊርዐውን ውድቀትም ይደሰታሉ፡፡ ምክንያቱም ፊርዐውን የአምባገነኖች ሁሉ ተምሳሌት ነውና፡፡ SHARE 👉 @NURU_TURKII
የድሉ ቀን ሲታወስ 🌰🌰🌰🌰🌰 የአሹራ ፆም የሚውለው በነገ ሀሙስ ነው። 🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮🏮 ፈርዖን የአምባገነኖች ተምሳሌት ከተሰኘው የአሕመዲን ጀበል መጽሐፍ የተወሰደ) 🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆 ሙሴና ተከታዮቹ በፈርዖንና ወገኖቹ ላይ ድል የተቀዳጁበት ቀን ታላቅና ታሪካዊ ቀን ነው፡፡ ምክንያቱም የዘመናት ባርነት በነጻነት የተቀየረበት፤ በዳያቸውን ድል የነሱበትና ፈርዖን ከነአጋሮቹ የተንኮታኮተበት ዕለት ነው፡፡ በመሆኑም የድሉ ቀንና ታሪክ ሁሌም ሊታወስ ይገባዋል፡፡ ቀጣዩ ትውልድም ታሪኩን በጥሞና እንዲያውቅና እንዲማርበት ማስታወስ ግድ ይላል፡፡ በመሆኑም እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ገለጻ አምላክ ሙሴን እንዲህ ብሎታል፦ “ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን ‘ዘወትር ሲታወስ እንዲኖር የዚህን ድል ታሪክ ጻፈው፤’ አለው፡፡” (ዘጸአት 17÷ 14) በፈርዖን ላይ የተቀዳጁትን ድል ለማስታወስ አምላክ ሁለት የበዓል ሥነ-ሥርዓቶችን እንደደነገገ መጽሐፍ ቅዱስ ይጠቅሳል፡፡ አንደኛው የፋሲካ መስዋዕት የሚደረግበት በዓል ሲሆን ይህም ቀን ፈርዖንን ለማንበርከክ የግብጻውያን የበኩር ልጆች የተገደሉበት (በዚያ) ሌሊት ነበር፡፡ ይህንኑ ሥርዓት ለእስራኤላውያን ቀጣይ ትውልድ ጭምር በቋሚነት እንዲቀጥል አምላክ ማዘዙን መጽሐፍ ቅዱስ ይጠቅሳል፡፡ እንዲህም ይላል፦ “ልጆቻችሁ ‘ይህ ሥርዓት ምንድን ነው’? ብለው በሚጠይቁአችሁ ጊዜ÷ እናንተም እንዲህ ብላችሁ ትመልሱላቸዋላችሁ፤ ‘ይህ እግዚአብሔርን ለማክበር የሚደረግ የፋሲካ መሥዋዕት ነው፤ እግዚአብሔር በግብጽ ምድር የእስራኤላውያን መኖሪያ ቤቶች አልፎ በመሄድ ግብጻውያንን ሲገድል እኛን አድኖናል፡፡’” (ዘጸአት 12÷26-27) እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ገለጻ ይህ የድል ታሪክ በቀጣይ ትውልዶች ጭምር የተቀደሰ ተደርጐ ይታወሳል፡፡ ይህንኑ መጽሐፉ እንዲህ በማለት ይገልጻል፦ “እግዚአብሔር ሕዝቡን እየጠበቀ ከግብጽ ምድር ባወጣቸው ዕለት ጊዜው ሌሊት ነበር፤ ያም ሌሊት እስራኤላውያን በመጠባበቅ ተግተው የሚያድሩበት ለሚመጣው ትውልድ ሁሉ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ ሌሊት ነው፡፡” (ዘጸአት 12÷ 42) ሌላኛው ከነጻነቱ ድል ጋር ተያይዞ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጠቀሰው “የቂጣ በዓል” ነው፡፡ ይህ በዓል በዓመቱ የመጀመሪያ ወር ላይ የሚከበር ሲሆን ሰባት ቀናት ያክል እርሾ የሌለው ቂጣ የሚበላበት ነው፡፡ በሰባተኛው ቀንም የቂጣ በዓል ይደረጋል፡፡ ይህ የሚደረገው ከግብጽ የባርነት ሕይወት ነጻነት እንዲቀዳጁ አምላክ ያደረገላቸውን እገዛ ለማስታወስ ነው፡፡ ይህንኑ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይገልጸዋል፦ “ሙሴም ለሕዝቡ እንዲህ አለ፦ ‘ይህ ቀን በባርነት ስትገዙ የኖራችሁበትን የግብጽን ምድር ለቃችሁ የወጣችሁበት ስለሆነ ይህን ቀን አስታወሱ፤ እግዚአብሔር በታላቅ ኃይሉ በመታደግ ያወጣችሁ በዚህ ቀን ነው፤’” (ዘጸአት 13÷3) ስለቂጣ በዓል አከባበርም መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይገልጻል፦ “በማርና በወተት ወደበለፀገችው ወደዚያች ለም ምድር በሚያገባችሁ ጊዜ በዓመቱ መጀመሪያ ወር ላይ ይህን በዓል ታከብሩታላችሁ፡፡ ሰባት ቀን ሙሉ እርሾ የሌለበት ቂጣ ትበላላችሁ፤ በሰባተኛውም ቀን ለእግዚአብሔር ክብር በዓል ታደርጋላችሁ፡፡ እስከ ሰባት ቀን ድረስ ያልቦካ እንጀራ ትበላላችሁ፤ እርሾም ሆነ የቦካ እንጀራ ከቶ በምድራችሁ አይገኝ፡፡ በዓሉም በሚከበርበት ጊዜ ይህን ሁሉ የምታደርጉት ከግብጽ በወጣችሁበት ጊዜ እግዚአብሔር ያደረገላችሁን መልካም ነገር ሁሉ ለማስታወስ መሆኑን ለልጆቻችሁ ተርኩላቸው፡፡ ይህም በዓል በእጃችሁ እንደታሰረ ምልክትና በግንባራችሁ እንዳለ ማስታወሻ ይሆንላችኋል፤ እግዚአብሔር በታላቅ ኃይሉ ከግብጽ ስላወጣችሁም የእግዚአብሔር ሕግ ዘወትር ከአንደበታችሁ ሳይለይ በቃላችሁ እንድትደግሙትና እንድታጠኑት ያስታውሳችኋል፡፡ ስለዚህ ይህን በዓል በየዓመቱ በተመደበለት ጊዜ የማክበር ሥርዓት ይሁንላችሁ፡፡” (ዘጸአት 13÷5-10) በዚህ መልኩ የድሉ ቀን እየታወሰ እንዲቀጥል መጽሐፉ ደንግጓል፡፡ ሙሳ (ዐ.ሰ) እና ተከታዮቹ ከፊርዐውን ጭቆናና ግፍ ነጻ የወጡበት ዕለት በኢስላምም ዘወትር ይታወሳል፡፡ ይህች ቀን ፊርዐውንና አጋሮቹ በባሕር የሰጠሙባት ዕለት ናት፡፡ በመሆኑም ይህች ታሪካዊ ዕለት በመሆኗም ሁሌም ልትታወስ ይገባታል፡፡ ይህችው ቀን በዚያው ዕለት አላህ በቁርኣን “ዛሬ” ብሎ የጠቀሳት ቀን ነች፡፡ በዚህችው ቀን ሙሳና ተከታዮቹ ለአምላካቸው የምስጋና ጾም እየጾሙ ዕለቷን ያስታውሱ ነበር፡፡ አምባገነኑን ፊርዐውንን አላህ በባሕር ሲያሰጥመው እንዲህ ነበር ያለው፦ فَٱلۡيَوۡمَ نُنَجِّيكَ بِبَدَنِكَ لِتَكُونَ لِمَنۡ خَلۡفَكَ ءَايَةٗۚ وَإِنَّ كَثِيرٗا مِّنَ ٱلنَّاسِ عَنۡ ءَايَٰتِنَا لَغَٰفِلُونَ — سورة يونس (10:92) “ዛሬ÷ ከአንተ በኋላ ለሚመጡ (ትውልዶች) ተአምር ትሆን ዘንድ አካልህን እናድናለን፡፡ ግና ብዙዎች ሰዎች ተአምራቶቻችንን ይዘነጋሉ፡፡” (ዩኑስ÷ 92) እንደ ኢስላማዊ መዛግብት ገለጻ ሙሳንና ተከታዮቹን አላህ ነጻ ያወጣበትና እንዲሁም “ዛሬ” ሲል አላህ የጠቀሳት ዕለት በኢስላማዊ አቆጣጠር በመጀመሪያ ወር (ሙሐረም) 10ኛ ቀን ነች፡፡ ከኢብኑ ዐብ-ባስ (ረ.ዐ) እንደተላለፈው ነቢዩ ሙሳና ተከታዮቹ ዕለቷን በጾም ያሳልፉ ነበር፡፡ የአላህ መልዕክተኛ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ወደ መዲና ከተማ ባቀኑበት ጊዜ ዕለቷን አይሁዶች ሲጾሙ አገኙ፡፡ የሚጾሙበትንም ምክንያት ጠየቋቸው፡፡ እንዲህ በማለትም መለሱላቸው፦ “ይህ ታላቅ ቀን ነው፡፡ አላህ ሙሳንና ተከታዮቹን ያዳነው በዚህ ቀን ነው፡፡ የፊርዖንንም ቤተሰቦች ያሰመጠበት ዕለት ነው፡፡ ሙሳም አላህን ለማመስገን ዕለቱን ይጾም ነበር”፡፡ መልዕክተኛውም (ሰ.ዐ.ወ) “እኔ ከአይሁዶች ይበልጥ ለሙሳ የቀረብኩ ነኝ፡፡” በማለት ዕለቱን ይጾሙ ጀመር፡፡ ተከታዮቻቸውንም እለቱን እንዲጾሙ አዘዙ፡፡(ሶሒሕ አል-ቡኻሪ፣ጥሪዝ 4፣ ሐዲሥ ቁጥር 1130፣ ገጽ 795) ሙስሊሞችም ሁለቱ የአላህ መልዕክተኞች (ሙሳና ሙሐመድ) ሁለት ሺህ ዓመታት ገደማ ቢራራቁም የሙሳ ድል የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ድል ነውና ዕለቱን በጾም አሳለፉ፡፡ ተከታዮቻቸውንም የድሉን ቀን በጾም እንዲያስታውሱ አዘዙ፡፡ ተከታዮቻቸው ዕለቱን (ሙሐረም 10ኛ ቀንን) እንዲጾሙ ያዘዙት እንዲህ በማለት ነበር፦ “ከነርሱ (ከአይሁዶቹ) ይልቅ ለሙሳ የምትቀርቡ እናንተ ናችሁ፡፡ እናም ዕለቱን ጹሙ፡፡”(ኢብኑ ከሢር፣ ተፍሲር አል-ቁርኣኑል ዐዚም፣ ጥራዝ 2፣ ገጽ 915) ይህ ሙስሊሞች የሚጾሙት ፆምም “የአሹራ ቀን ጾም” ተብሎ ይታወቃል፡፡ ዕለቱንም የሙሳንና የፊርዐውንን የትግል ታሪክ እያስታወሱ÷ ከታሪኩ በመማር የሙሳ ድል የነርሱም ድል እንደሆነ እያሰቡ ይጾማሉ፡፡ የፊርዐውን ውድቀትም የሁሉም እኩያንና መሰል አምባገነኖች ውድቅት እንዲሆን እየተመኙ፤ አላህ ሙሳንም እንደረዳ ሁሉ እነርሱንም እንዲረዳ ይማጸናሉ፡፡ ኢስላም እንደሚያስተምረው ዕለቱንም በጾም ማሳለፉ እጅግ ተወዳጅና ከፍተኛ ምንዳ የሚያስገኝ የአምልኮ ተግባር ነው፡፡
“በጁምዓ ቀንና በጁምዓ ሌሊት በኔ ላይ ሰለዋትን አብዙ።” የአላህ መልእክተኛ ﷺ SHARE 👉 @NURU_TURKII
እንኳን ለኢስላማዊው ዘመን አቆጣጠር አዲስ አመት በሰላም አደረሰን! መጪው አመት የደስታ፣ የስኬት እንዲሁም የበረካ እንዲሆን እንመኛለን! ኡስታዝ ኑሩ ቱርኪ Ustaz Nuru Turki
እንኳን ለ1448ኛው ዓመተ‐ሒጅራ ኢስላማዊ የዘመን መለወጫ በሰላም አደረሰን። መጪውን ዘመን አላህ በበረካ የተሞላ፣ የሻትነው ኸይር ሁሉ የሚሳካበት፣ በኢማን የምንታደስበት፣ ከወንጀል የምንርቅበት፣ የአላህን ውዴታ የምናገኝበት ይሁንልን። አሚን