ትኩስ የስራ ማስታወቂያዎች
Статистикаትኩስ የስራ ማስታወቂያ በየቀኑ የሚወጡ የስራ ማስታወቂያዎች ምንጭ ነው! መልዕክት ካለውዎት በዚህ ይላኩልን፡ @tikusjobsadmin #tikusjobs #EthiopiaJobs #AddisAbabaJobs #JobVacancyEthiopia #JobOpportunitiesEthiopia #EthiopianEmployment #EthiopianJobs #AddisJobs #EthioJob #JobAlertEthiopia
- Последний пост
- 3 июн.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 24
- Тип
- открытый
- Язык
- ilo
- Категория
- Криптовалюты (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- —
- 1/48двое суток
- —
- 1/72трое суток
- —
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
💻 በቴክኖሎጂ ወገኖቻችንን እንፈልግ! ትናንት በምሥራቅ አርሲ በአሰኮ ወረዳ የተከሰተውን አሳዛኝ ሁኔታ ተከትሎ፣ የጠፉ ወገኖቻችንን ከቤተሰቦቻቸው ጋር የሚያገናኝ ቀላል የቴሌግራም ቦት (Bot) በዲጂታል ባለሙያዎቻችን አዘጋጅተናል። በአሁኑ ሰዓት በርካታ የደረሱበት ያልታወቁ ሰዎች በመኖራቸው፣ ይህ መድረክ መረጃዎችን በአንድ ቦታ ሰብስቦ በፍጥነት ለማገናኘት ይጠቅማል። የቦቱ ሊንክ፦ @arsifinderbot እንዴት መጠቀም ይቻላል? ሊንኩን ተጭነው በመግባት Start የሚለውን ይጫኑ። ቤተሰብ የሚፈልጉ ከሆነ "ቤተሰብ ፈላጊ ነኝ" የሚለውን ቁልፍ ተጭነው ፎርሙን ይሙሉ Telegram በራስ-ሰር ይመራዎታል። ስለ ጠፉ ወይም ስላሉ ወገኖች ማንኛውም መረጃ ካለዎት "መረጃ አለኝ" የሚለውን ተጭነው ያጋሩን። ለስራ ፈላጊ ወጣቶች ጥሪ፦ በቦቱ የሚመጡ መረጃዎችን በፈቃደኝነት ለመለየት፣ ለማጣራት (Data Verification) እና ለተጨነቁ ቤተሰቦች በስልክ ደውሎ መረጃውን ለማድረስ የምትፈልጉ ተመራቂዎች በውስጥ መስመር አግኙን። እባክዎ ይህ መልዕክት ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ የዜግነት ድርሻዎን ይወጡ። እውቀታችን ለወገናችን ድምፅ ይሁን!
ክቡራን ተከታተዮቻችን፤ ገጻችን የስራ ማስታወቂያዎችን እና የቴክኖሎጂ መረጃዎችን የሚያጋራ ቢሆንም፣ በምሥራቅ አርሲ አሰኮ ወረዳ በንፁሃን ወገኖቻችን ላይ የደረሰው አሰቃቂ ጭፍጨፋ እና መፈናቀል እጅግ አሳዝኖናል። እንደ አንድ የቴክኖሎጂ ባለሙያ/ማህበረሰብ፣ ከተጎዱት መካከል ከ280 በላይ የጠፉ ሰዎችን ለመፈለግ እና ለመርዳት የሚያግዝ የዲጂታል መድረክ (የፍለጋ ቦት/ድረ-ገጽ) በነፃ ለማልማት እያሰብን ነው። በዚህ አካባቢ ያላችሁ ወይም ታማኝ መረጃ ማድረስ የምትችሉ ወገኖች በውስጥ መስመር (Inbox) እንድታግዙን በትህትና እንጠይቃለን። ለሟቾች ፈጣሪ ገነትን ያውርሳቸው! ለዘመድ አዝማድ መጽናናትን እንመኛለን።
"እኔ እኮ ተምሬያለሁ፣ ታዲያ ስራ ለምን አላገኘሁም?!" ከዩኒቨርሲቲ ተመርቀው ስራ አጥተው ቤት መቀመጥ የብዙዎቻችን መራራ ህመም ሆኗል። ነገር ግን ማንም የማይነግረን እውነተኛው ምክንያት ምንድን ነው? ችግሩ የስራ መታጣቱ ነው ወይስ የእኛ አደገኛ አስተሳሰብ? ለአናጺው አንቶኒዮ የተነገረው ምስጢርስ ምን ነበር? 📌 በድረ-ገጻችን ላይ ብዙዎችን ያስቆጣውን፣ ያከራከረውን እና እውነተኛውን መፍትሄ ያመላከተውን አዲስ ጽሑፍ አሁኑኑ ያንብቡ። የእርስዎንም አስተያየት በኮሜንት ያጋሩን! 👇 ሊንኩን ተጭነው ሙሉውን ያንብቡ፡ 🌐 https://l1nq.com/k4al9u3
‼️ የስራ ማስታወቂያ ‼️ 🏢 የድርጅቱ ስም = ትዊንክል የልጆች መጫወቻ 📌 አድራሻ = መገናኛ፣ ከደራርቱ ታወር ጀርባ፣ ቱሪስት ሳይት 40/60 ኮንዶሚኒየም 💼 የስራ መደብ = የመጫወቻ ስፍራ ሁለገብ ሰራተኛ (ደንበኞችን መቀበልና ልጆችን እንዴት እንደሚጫዎቱ መርዳት) 🎓 ትምህርት = አያስፈልግም 🗓 የስራ ልምድ = በአገልግሎት ሰጪ ድርጅት 1 ዓመት የስራ ልምድ ከልጆችን ጋር መጫወት እና መንከባከብ የምትወድ የስራ ሰዓት ጠዋት 3:00 - ማታ 2:00 🚻 ፆታ = ሴት 🚻 እድሜ 18 እስከ 25 አመት 🕒 የስራ አይነት = ሙሉ ቀን 👥 የሚፈለጉ ሰራተኞች ብዛት = 1 💰 ደመወዝ = በስምምነት 📩 ለማመልከት = በስልክ 0923563371 ወይም 0944121769 ይደውሉ 📞 የመገናኛ መረጃ = 0923563371 ወይም 0944121769 / anagawd@yahoo.com የንግድ ፈቃድ ያልው ነጋዴ ወይም የግል ወይም የመንግስት ሰራትኛ ተያዥ ያላት ሰፈሯ: መገናኛ፡ ጉርድ ሾላ፡ ሾላ፡ ሀያ አራት፡ ሀያ አራት ወይም ለስራ ቦታው ቅርብ ለሆነች ብቻ
የሥራ ማስታወቂያ የሴቫስቶፖል ሸማቾች የሕብረት ሥራ ማሕበር ብቁ እና ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች ከዚህ በታች በተጠቀሰው ክፍት የስራ መደብ ላይ አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ተፈላጊውን መስፈርት የምታሟሉ አመልካቾች እንድታመለክቱ እንጋብዛለን። 1. የስራ መደብ፡ ሥራ አስኪያጅ (Manager) 2. ብዛት: 1 3. የቅጥር ሁኔታ: በኮንትራት 4. የሥራ ቦታ: ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ 5. ተፈላጊ ችሎታዎችና መስፈርቶች: Ø የትምህርት ዝግጅት፡ በቢዝነስ አስተዳደር፣ በግብይት፣ በማኔጅመንት፣ በሆቴል ማኔጅመንት፣ ወይም በተዛማጅ የቢዝነስ መስክ ዲግሪ ያለው/ያላት። Ø የሥራው ዓላማ: የድርጅቱን ዕለታዊ ሥራዎች በብቃት ማስተዳደር፣ ሰራተኞችን መምራትና ማስተባበር፣ የአገልግሎት ጥራትን ማረጋገጥ እና የድርጅቱን ግቦች ማሳካት። Ø የስራ ልምድ፡ · በተመሳሳይ የሥራ መደብ ላይ ቢያንስ 1 ዓመት የተረጋገጠ የሥራ አመራር ልምድ ያለው/ያላት። በተለይም በሆቴል አስተዳደር፣ በካፌ እና ተያያዥ መስኮች የስራ ልምድ ያለው ይመረጣል። · የሰዎች አመራርና ማደራጀት ብቃት ያለው/ያላት። · የፋይናንስ አስተዳደር እና የበጀት ቁጥጥር እውቀት ያለው/ያላት። · የደንበኞች አገልግሎት ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ግንዛቤ ያለው/ያላት። · የችግር አፈታት እና ውሳኔ የመስጠት ችሎታ ያለው/ያላት። · በኮምፒውተር አጠቃቀም (በተለይም Microsoft Office) ጥሩ ችሎታ ያለው/ያላት። · ግንኙነት የመፍጠር እና ቡድንን የማነሳሳት ክህሎት ያለው/ያላት። 6. ደመወዝ: በስምምነት ሆኖ ማራኪ ጥቅማ ጥቅሞች ያሉት። 7. ለማመልከት የሚያስፈልጉ ነገሮች: · የትምህርት ማስረጃዎች ዋናው እና ኮፒ። · የስራ ልምድ የሚያሳይ ደብዳቤ። · ሌሎች ጠቃሚ ማስረጃዎች ( ካሉ) 8. የማመልከቻ ቀን: ከ18/09/2018 ዓ/ም እስከ 26/09/2018 ዓ/ም 9. የማመልከቻ ቦታ፡ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ፣ የማህበሩ ቢሮ ( ሴቫ የስታፍ ላውንጅ)፤ ማስታወሻ: አመልካቾች የትምህርትና የስራ ልምድ ማስረጃቸውን የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ይዘው መቅረብ ይጠበቅባቸዋል። ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።
የስራ ማስታወቂያ
ኤስ ኤም ኃ/የተ/የግ/ማህበር ቀጥሎ የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟላ ሠራተኛን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡ የስራ መደብ: ጁንየር የቢሮ ረዳት እና አስተባባሪ (Junior Office Assistant & Coordinator) የቅጥር ሁኔታ፡ ኮንትራት ሆኖ እንደሁኔታው የሚራዘም የት/ት ደረጃ፡ በማርኬቲንግ፣ በሴክሬተሪያል ሳይንስ ወይም በተዛማጅ መስኮች ዲፕሎማ ወይም ዲግሪ ያላት የሥራ ልምድ፡ 0 ዓመትና ከዚያ በላይ ጾታ፡ ሴት ዋና ዋና የስራ ኃላፊነቶች - የቢሮ ስራዎች፡ ከባለሙያዎች የሚላኩ ፋይሎችን እና የንድፍ ስራዎችን ፕሪንት ማድረግ፣ ሰነዶችን በስርዓት መያዝ እና ደንበኞችን ማስተናገድ። - የውጭ ስራዎች፡ ቢሮውን ወክሎ ወደ ተለያዩ ተቋማት በመሄድ የቢሮ ጉዳዮችን በቅልጥፍና ማስፈጸም እና መከታተል። - ማስተዋወቅ እና ውል፦ የቢሮውን አገልግሎቶች ለደንበኞች ማስተዋወቅ እና የውል ስምምነቶችን ማመቻቸት። ችሎታ፡ መሰረታዊ የኮምፒውተር (Word, Excel) እውቀት ያላት፣ ቀልጣፋ፣ የንግግር እና የተለያዩ ተቋማት ጋር ሄዶ ጉዳይ የማስፈጸም ብቃት ያላት። ደሞዝ፡ በስምምነት የስራ ቦታ: አዲስ አበባ, ሀያት አደባባይ ከስራው ሁኔታ አንፃር የመኖሪያ አድራሻዋ ለስራ ቅርብ ቢሆን ይመረጣል! ለማመልከት በቴሌግራም ሊንክ @SM_ArcPLC ማመልከት ወይም በአካል በመቅረብ የትምህርትና ተያያዥ ማስረጃ ኮፒ በማቅረብ መመዝገብ ይችላሉ፡፡ ለተጨማሪ ማብራሪያ ይደውሉ! ☎️ 0991473978
እንኳን ለጌታችን ፣ ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! መልካም ፋሲካ!
for Electrical Enginers Only!
ተጨማሪ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን ለመቅጠር የወጣር ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን በመመልመል ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ከታች በተዘረዘሩት በአማራ ክልል በሚገኙ ምርጫ ክልሎች ላይ መሥፈርቱን የሚያሟሉ ተጨማሪ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን በመመልመል መቅጠር ስለሚፈልግ፤ የተያያዘውን ማስፈንጠሪያ https://nebe-election.org/recruitment በመጠቀም ከዛሬ ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ እስከ የካቲት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ እንድትመዘገቡ ቦርዱ ያሳውቃል። በምርጫ ክልል ጽ/ቤት ደረጃ ምዝገባ የሚካሄድበትን ቀን ቦርዱ ወደፊት ያሳውቃል። የምልመላ መሥፈርት፡- • ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣ • የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣ • የትምህርት ዝግጅት፦ 12ኛ እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣ • የሥራ ቦታ፦ ቦርዱ በሚያቋቁማቸው የምርጫ ጣቢያዎች፣ • የክልሉን የስራ ቋንቋ መናገር እና መጻፍ የሚችሉ • የሥራ ቆይታ ፦ ለሁለት ወር፣ • ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የመምህራን እና ቴክኒካል አሲስታንስ የስራ ማስታወቂያ
без подписи
ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ የስራ ማስታወቂያ
እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የደስታ ይሁንላችሁ!
ትላንት ማለዳ በአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን አካባቢ የታየው ትዕይንት ልብን የሚሰብርና የሀገራችንን ትልቁን ማህበራዊ ህመም ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ባለስልጣኑ ለ48 ክፍት የስራ መደቦች ብቻ ባወጣው ጥሪ መሰረት፣ ስራ ፍለጋ የወጣው በሺዎች የሚቆጠር ወጣት አካባቢውን አጥለቅልቆት አርፍዷል። ይህ ምስል ዝም ብሎ ሰልፍ አይደለም፤ ይልቁንም በወጣቶቻችን ትከሻ ላይ ያለውን የኑሮ ጫና እና የስራ ጥማት በግልፅ የሚናገር ትልቅ አዋጅ ነው። ጥቂት የማይባሉ ወጣቶች ለዚያች ለአንዲት የስራ እድል ሲሉ ማለዳውን ብርዱን ተቋቁመው በሰልፍ ሲጠበቁ አርፍደዋል። ነገር ግን ለ48 ወንበሮች በሺዎች የሚቆጠሩ መመዝገባቸው፣ በሀገራችን ያለው የስራ አጥነት ችግር ምን ያህል አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደደረሰ ያሳያል። ወጣቱ ዝግጁ ነው፣ ጉልበትና እውቀት አለው፤ የሚጎድለው ግን ያንን አቅሙን የሚጠቀምበት መድረክ ነው። ይህ ትዕይንት ለፖሊሲ አውጭዎች ትልቅ የቤት ስራ የሚሰጥ ነው። ስራ አጥነት የቁጥር ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጅ ክብርና ተስፋ ጉዳይ ነው። እንዲህ ያለውን ሰፊ ክፍተት ለመሙላት መደበኛ ከሆነው አሰራር ወጣ ያለ እና ወጣቱን በተግባር ተጠቃሚ የሚያደርግ መፍትሄ ከመቼውም ጊዜ በላይ ያስፈልጋል። የእነዚህን ወጣቶች አይን ስንመለከት፣ ነገን በተሻለ ተስፋ እንዲጠብቁ የሚያደርግ ተግባራዊ እርምጃ መጠበቃችን ተገቢ ነው። @ኢትዮ ሊድ
የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ለሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን (ለመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር) ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል ። በክፍት ቦታዎች መወዳደር የምትፈልጉ ፤ ዝርዝር መረጃውን ከታች ከተቀመጠው ሰንጠረኝ ይመልከቱ! ለመመዝገብ ደግሞ መስፈንጠሪያውን ( ሊንኩን) ይጠቀሙ። መልካም እድል! የምዝገባ አድራሻ፦ https://forms.gle/nJD7Z51ekJYSH3uZ8