- Последний пост
- 13 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 1
- Всего постов
- 26
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 93
- 1/48двое суток
- 106
- 1/72трое суток
- 114
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
'' ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? '' '' ኢየሱስም፡— ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም።'' - ማርቆስ 10:18 - ይህንን ቃል የተናገረው ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። አንዳንድ ወገኖች ይህንን ቃል በመጥቀስ ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር አይደለም ፤ ቸር እግዚአብሔር ብቻ ነው ፥ ስለዚህ እርሱ እግዚአብሔር አይደለም ( ሎቱ ስብሐት) ይላሉ። ኢየሱስ ክርስቶስ ቸር እግዚአብሔር እንደሆነ ምንም ጥርጥርም የለው። እንኳን ጌታችን፤ ብዙ ሰዎችም ሳይቀር ቸር ተብለዋል...እኛ ቸሮች እንድንሆንም ታዘናል። 🌿 '' ከቸር ሰው ጋር ቸር ሆነህ ትገኛለህ፤ ከቅን ሰው ጋር ቅን ሆነህ ትገኛለህ፤'' (መዝ 17:25) 🌿 '' ቸር ሰው ይራራል ያበድራልም፥ በፍርድም ነገሩን ይፈጽማል።'' ( መዝ 110:5) 🙌 የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት ሰው እንኳ ከሚሰራው ሥራ አንዱ የቸርነት ሥራ ነው። '' የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፣'' (ገላ 5:22) እንዲህ ከሆነ የጌታችን ንግግር እንዴት ይታያል? ጌታችን ልብንና ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ ነውና በሰዎች ልቡና ያለውን ተንኮልና ቀናነት በራሱ ስለሚያውቅ ( ዮሐ 1፡49 ፣ ዮሐ 4፡18 ) የዚህንም ሰው የልቡን ሐሳብ አወቀ። ይህ ሰው በልቡ የኢየሱስን እግዚአብሔርነት ሳያምን እንዲሁ በአፉ #ቸር_መምህር-ሆይ ብሎ የተጠራው። ጌታችንም ከእግዚአብሔር በቀር ሰው በባሕርዩ ቸር ሊባል አይገባውም አለው ( ቅዱሳን ቸር ቢባሉ በጸጋ ነውና) ጌታችንን ቸር ያለው ሰው እርሱ ክርስቶስ እግዚአብሔር አምላክ እንደሆነ ሳያውቅ - ሳያምን ነበርና እንዲሁ ቸር ብሎ የጠራው። ስለዚህ አምላክነቴን እግዚአብሔርነቴን ሳታውቅ ሳትረዳ ስለምን ቸር ትለኛለህ? አምላክነቴን ተረድተህ ቸር በለኝ። ከእግዚአብሔር( ከእኔ) በቀር ቸር ማንም የለምና ማለቱ ነው። 👏 ኢየሱስ ቸር እንደሆነ ማስረጃዎች። '' የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ቸር ስጦታ አውቃችኋልና፤ ሀብታም ሲሆን፥ እናንተ በእርሱ ድህነት ባለ ጠጎች ትሆኑ ዘንድ ስለ እናንተ ድሀ ሆነ።'' (2 ቆሮ 8:9) የኢየሱስን እግዚአብሔርነቱን አምነን ቸሩ አማኑኤል ሆይ እንበለው። ይቆየን።
" ወቅድመ ሥዕላ ስግዱ ወኢሰገደሰ ላቲ ይደምሰስ እምቅዋሙ ወኢይትዐወቅ ዝክረ ስሙ ወይበሉ መላእክተ ሰማይ ኲሎሙ አሜን ፥ በሥዕሏም ፊት ሰገዱ ለሥዕሏ ያልሰገደ ግን ከቆመበት ቦታ ይጥፋ ስም አጠራሩም አይታወቅ፡፡ በሰማይ ያሉ መላእክት ይደረግ ይሁን ይበሉ፡፡" 1. የሰገዱበት ምክንያት (የሥዕላት ክብር) በኦርቶዶክስ እምነት ለቅዱሳን ሥዕላት (በተለይም ለክርስቶስ፣ ለድንግል ማርያምና ለቅዱሳን ሥዕላት) የሚቀርበው ስግደት የአምልኮ ስግደት (Latria) ሳይሆን የጸጋ እና የክብር ስግደት (Dulia) ነው። በሥዕሉ ላይ የሚታየውን አካል (ባለቤቱን) ለማክበርና ለመዘከር የሚደረግ መግለጫ ነው። አማኙ በሥዕሉ ፊት ሲሰግድ ለቀለሙ ወይም ለጨርቁ/ለእንጨቱ ሳይሆን፣ በሥዕሉ ላይ ለተሳለው ቅዱስ አካል ያለውን ክብርና ፍቅር ይገልጻል። 2. "ያልሰገደ ግን ከቆመበት ቦታ ይጥፋ..." የሚለው ጠንካራ አገላለጽ ይህ ዓይነቱ ጠንካራና የርግማን መልክ ያለው አገላለጽ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ከተከሰቱት የአይኮኖክላስት (Iconoclasm - ሥዕላትን የማጥፋት/የመቃወም) ንቅናቄዎች እና ክርክሮች ጋር የተያያዘ ነው። የታሪክ አውድ፡ በታሪክ ሥዕላትን አናከብርም የሚሉና ቅዱሳን ሥዕላትን የሚያረክሱ ወገኖች በተነሱበት ወቅት፣ የሥዕላትን ክብር ለመጠበቅና አማኙን ከክህደት ለመጠበቅ ሲባል እንዲህ ያሉ ጥብቅና የጠንካራ ቀኖና መግለጫዎች በድርሳናት ላይ ይጻፉ ነበር። ፍርዱ፡ ይህ አገላለጽ እምነቱንና የሥዕላቱን መለኮታዊና መንፈሳዊ ክብር በአክራሪነት ለመጠበቅ የመጣ መንፈሳዊ ማስጠንቀቂያ (Anathema) ነው። 3. "በሰማይ ያሉ መላእክት ይደረግ ይሁን ይበሉ" ይህ ደግሞ ምድራዊው ጸሎት፣ ውሳኔና ምስጋና ከሰማያዊው አምልኮ ጋር ያለውን አንድነት የሚያሳይ ነው። ቤተ ክርስቲያን በምድር የምትወስነውና የምታደርገው መንፈሳዊ ሥርዓት በሰማይ ባሉ መላእክት ዘንድ ተቀባይነትና ድጋፍ እንዳለው የሚገልጽ ቀመር ነው።
በሥዕሏም ፊት ሰገዱ ለሥዕሏ ያልሰገደ ግን ከቆመበት ቦታ ይጥፋ ስም አጠራሩም አይታወቅ፡፡ በሰማይ ያሉ መላእክት ይደረግ ይሁን ይበሉ፡፡
видео или голосовое, без подписи
ስለ ምን ማወቅ ይፈልጋሉ? ጥያቄዎትን በኮሜንት ያስቀምጡ። @WwEotc
‹‹አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ፡፡ መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳቸውን ተሳለሙት። ቀጥለውም በያዙት መስቀል አማትበው ሕዝቡን ባረኩ፡፡ የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተው ካዩ በኋላ መልሰው ከኪሳቸው ከተቱት፡፡ ወዲያው ወታደሮቸ በሩምታ ተኩሰው ገደሏቸው፡፡ ይህ እንደሆነ አስገዳዩ ኮሎኔል ተመልካቹን ሕዝብ አጨብጭቡ ብሎ አዘዘና ተጨበጨበ። ማታ ከአስገዳዩ ኮሎኔል ጋር ተገናኝተን ስንጫወት ‹‹በዚህ ቄስ መገደል እኮ ሕዝቡ ተደስቷል›› አለኝ፡፡ ‹‹እንዴት?›› ብለው ‹‹አላየህም ሲያጨበጭብ?›› አለኝ፡፡ ‹‹ባታውቀው ነው እንጂ የሕዝቡ ባሕል ሲናደድም ያጨበጭባል›› አልኩት፡፡ ‹‹እንዴት?›› ቢለኝ እጄን አጨብጭቤ አሳየሁት፡፡" አቡነ ጴጥሮስ ሲገደሉ በቦታው ሆነው የተከታተሉት ሙሴ ፓይላክን የተባሉ ግለሰብ በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ለጳውሎስ ኞኞ ከነገሩት የተወሰደ፡፡ ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ/ም
ቅዱስ ዑራኤል - የከበረው መልአክ የህይወትን ጽዋ ለአበው የሚያጠጣቸው እርሱ ነው። ጌታ አምላክ ኢየሱስ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በምድሪቱ የረጨ እርሱ ነው። ጌታ አምላክ ኢየሱስ ሲወለድ በአብሪ ኮከብ ተመስሎ 3ቱን ነገስታት ወደ ቤተልሄም የመራቸው እርሱ ነው። በሐዲስ ኪዳን እንደተጻፈው በመጠመቂያው ቦታ መልአኩ ሲገባ ውሃው ይነዋወጽ ነበረ ቀድሞ የገባውም የታመመ ሰው ከያዘው በሽታ ሁሉ ይድን ነበረ። ያ ውሀውን የሚቀድሰው መልአክ ዑራኤል እርሱ ነው። ጌታ ኢየሱስ በዚህ በከበረ መልአክ ምልጃ ይማረን። አሜን።
መንፈሳዊት መርከብ ሆይ፡፡ ድንግልናዊት መፆር ሆይ፡፡ ከክፉ ዘመን መከራ አድኝኝ፡፡ አርጋኖን ዘረቡዕ
ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ስለ ነገረ መላእክት ባስተማረበት መጽሐፉ የመላእክት ተፈጥሮአቸው ልዩ ልዩ ነው። ምንም እንኳ መናፍስት ቢሆኑም የራሳቸው አካል አላቸው። ቁመታቸው ከምድር እስከ ጨረቃ የሚደርሱ አሉ ፣ ራሳቸው ብቻ የምድር ትልቁን ተራራ የሚያህል አሉ ፣ ሰውነታቸው በአይን የተሸፈኑ አሉ ፣ ልብሳቸው መብረቅ የሆነላቸው አሉ ወዘተ... እንግዲህ እነዚህን መላእክት ማክበርና መታዘዝ ተገቢ ነው። "በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ።" — ዘጸ 23:20 "በፊቱ ተጠንቀቁ፥ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት።" — ዘጸ 23:21
የቅዱስ ገብርኤል አጋዥነት በግልጽ የሚያሳይ፣ ለተጨነቀች ነፍስ ትልቅ መጽናኛና እምነትን የሚያጽናና ታላቅ የእግዚአብሔር ቃል ነው 👉 «የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል። እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ እዩ ጣሙም፤ በእርሱ የሚታመን ሰው ምስጉን ነው።» — መዝሙረ ዳዊት 34:7-8 የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃና ምልጃ፣ የሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት እያሉጣ በረከት ሁልጊዜም በዙሪያችን ይስፈር፤ ከክፉ ሁሉ ያድነን 🌼
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ። የበረከት የደስታ በዓል ይሁንልን። ሐገራችንን ሰላም ያድርግል።
እምነትና መልካም ኅሊና ይኑርህ። አንዳንድ ሰዎች ኅሊናቸውን በመጣላቸው መርከብ በማዕበል እንደሚጠፋ እምነታቸውን አጥፍተዋል። — 1ኛ ጢሞቴዎስ 1:19
❄️ በእንተ ቅዱሳን መላእክት ❄️ " ልሰግድለትም በእግሩ ፊት ተደፋሁ። እርሱም። እንዳታደርገው ተጠንቀቅ፤ ከአንተ ጋር የኢየሱስም ምስክር ካላቸው ከወንድሞችህ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ፤ የኢየሱስ ምስክር የትንቢት መንፈስ ነውና አለኝ።" (ራእ 19:10) ይህን በመጥቀስም ለመላእክት መስገድ ተገቢ አይደለም የሚሉ ክፍሎችም አሉ። ዳሩ ግን የመልአኩ አባባል ካለመረዳት እንጂ ለመላእክት መስገድ ከሃይማኖት ውጭ ሆኖ ዮሐንስ ባለማወቅ የሰገደለት ሆኖ አይደለም። ይህንንማ እንዳንል የሰጋጁ የዮሐንስ ማንነት ያግደናል። ዮሐንስ ድንግላዊና የጌታ ሐዋርያ ከመሆኑም ሌላ ጌታ የሚወደው በመንፈስ ቅዱስ የተቃኘ፤ ወንግጌልን መልእክታትን የጻፈ ፥ እንዲሁም የዓለምን ፍጻሜ በራእይ ያየ ነው ነው። ይህን ያህል የጌታ ባለሟል የሆነ ቅዱስን ሰው ለትንሿ ለነገር ለመላእክት መስገድ ተገቢ አለመሆን አጥቶት በስሕተት ሰገደ ማለት የጻፋቸው ወንጌሎችም መልእክታትም ስሕተት አላቸው ማለት ነው። ይህ ማለት ግን ሰው እንደ እግዚአብሔር ፍጹም ነው ማለት አይደለም። እሱ በፍጹም እምነት ውስጥ ሳይሆን እሱ ማን መመለክ እንዳለበት ሳያውቅ ለእኛ ማሳወቅ አይችልምና። ስለዚህ በስሕተት ሰገደ ማለት ከፍተኛ ስህተት ነው። ዮሐንስ ለመልአኩ የአክብሮት ስግደት ያቀረበው ለመላእክት መስገድ ተገቢ መሆኑን ስላወቀ ነው። መልአኩም ደግሞ #አትስገድልኝ ማለቱ የዮሐንስን ክብርና ማዕረግ መግለጡ ነው። ዮሐንስም በክብሩ ከመልአኩ እኩል ሆኖ ነበርና፥ እንድም በስልጣን በልጦት ነበር #ካህን ነውና ስልጣነ ክህነትህ ከእኔ ስልጣን ትበልጣለች ሲለው ነው..ስለ ስልጣነ ክህነት ታላቅነት " የትዳር ጉዳይ ይቅርና በመላእክት እንኳ እንድንፈርድ አታውቁምን?" (1ኛ ቆሮ 6:3) ተብሎ ተጽፏልና። ስግደት ደግሞ የበላይና የበታች መግለጫ ስለሆነ አንተ'ኮ በክብር ከእኔ እኩል ነህ። ስለዚህ ለእኔ ልትሰግድ አይገባም ቢለውም ዮሐንስ ግን ከመስጊድ ወደ ኋላ አላለም ትሁት ነውና። ይህን ማረጋገጥ ከፈለግን ራእይ 22:8-9 እንመልከት.. '' ያየሁትና የሰማሁት እኔ ዮሐንስ ነኝ። በሰማሁትና ባየሁትም ጊዜ ይህን ባሳየኝ በመልአኩ እግር ፊት እሰግድ ዘንድ ተደፋሁ። እርሱም። እንዳታደርገው ተጠንቀቅ፤ ከአንተ ጋር ከወንድሞችህም ከነቢያት ጋር የዚህንም መጽሐፍ ቃል ከሚጠብቁ ጋር አብሬ ባሪያ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ አለኝ።'' (ራእ 22:8-9) እንግዲህ ዮሐንስ ተሳስቶ ሰገደ ቢባል እንኳ ሁለት ጊዜ ይሳሳታል? የመጀመሪያው አንሶ? እንግዲህ አባባሉ የትሕትና አባባል መሆኑ ግልጽ ነው። '' መላእክትም ከሰይጣናት የሚለያቸው አንዱ ይህ ነው። ሰይጣናት የማይገባቸውን ክብር ሁሉ በትዕቢት ይቀበላሉ ፤ መላእክት ግን የሚገባቸው እንኳን ቢሆን ስለ ትህትና ይተዋሉ። ክብርን ሁሉ ለጌታቸው ይሰጣሉ። '' ቅዱስ እንድርያስ ዘቂሳርያ ይቆየን 🍋
🍅 " አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤"(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:5) 🍀 በመጀመሪያ መካከለኛ ማለት አማላጅ ማለት አይደለም። ቅዱስ ጳውሎስም የእውነት ኢየሱስ አማላጅ ቢሆን ኖሮ በግልጽ መካከለኛ በሚለው ቃል ፋንታ አማላጅ ቃል የሚለውን ይጠቀም ነበረ.. ጌታ ተማላጅ እንጂ አማላጅ ስላልሆነ... ቅዱስ ጳውሎስ መካከለኛ የሚለውን ቃል ስለምን ተጠቀመ ቢባል? 🍀 ኢየሱስ መካከለኛ ነው ሲባል በእግዚአብሔርነትና በሰውነት መካከል ያለ ፍፁም አምላክ ፍፁም ሰው ነው ማለት ነው፡፡ 🍀 ቅዱስ ጳውሎስ ይህን በዚህ መልክት ይህን ቃል(መካከለኛ) በጻፈበት ዋና ዓላማ 👉 አካባቢው ብዙ የግሪክ፣ የሮምና የአይሁድ ሠዎች ነበሩ፤ እነርሱም በኢየሱስ ላይ ብዙ አመለካለት ስለ ነበራቸው ነው፡፡ #ግሪኮች :- ኢየሱስ የሚናገረው ቃል አስገራሚና ሚሥጢራዊ በመሆኑ ኢየሱስን " ፈላስፋ " ነው ብለው ያስቡ ስለነበረ፣ #ሮማዎች ደግሞ "ነፃ አውጪ" ማለትም እሥራኤላውያንን ከኛ ቀኝ ግዢ የሚያወጣ ሠው ነው ብለው ያሥቡ ሥለነበረ፣ #አይሁዶች ደግሞ "እንዲሁ ተራ ሰው" አድርገው ያሥቡ ሥለነበረ፡፡ 👉 ቅዱስ ጳውሎስ ግን ኢየሱስ እናተ እንደ ምታስቡት ተራ ሰው፣ ፈላስፋ ወዘተ አይደለም፡፡ ኢየሱስ ማለት ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ ነው፡፡ ኢየሱስ በእግዚአብሔርነትንና በሠውነት መካከል ያለ ከሁለቱ አካል አንድ አካል ይዞ የመጣ መካከለኛ ነው፤ ለማለትና ለመናገር በመልክቱ #መካከለኛ አለ፡፡ መካከለኛ የመሆኑ ሚሥጢር ረቂቅ ነው፡፡ 👉 " ከዚችም ዓለም ገዦች አንዱ እንኳ ይህን ጥበብ አላወቀም፤ አውቀውስ ቢሆኑ የክብርን ጌታ ባልሰቀሉትም ነበር፤"(1ኛቆሮ 2:8) ይቆየን! @WwEotc
ፖርኖግራፊ አያረካም... እርካታን ይዘርፋል። ብዙ ሰዎች ፖርኖግራፊ እፎይታን ያመጣል ብለው ያስባሉ። ነገር ግን እውነቱ ግን ጊዜያዊ ማደንዘዣን ብቻ እንደሚሰጥ ነው። በእፎይታ እና በማደንዘዝ መካከል ሰፊ ልዩነት አለ። እፎይታ ሰውን ያድሳል፤ ማደንዘዝ ግን ህመሙን ለጥቂት ጊዜ ዝም አድርጎ ከበፊቱ በባሰ ኃይል ይመልሰዋል። ፖርኖግራፊ ለሰውዬው በሹክሹክታ እንዲህ ይለዋል፦ «ከጭንቀትህ አምልጥ።» «ከብቸኝነትህ አምልጥ።» «ከተገለልህበት ስሜት አምልጥ።» «ከቤትህ ችግሮች አምልጥ።» ነገር ግን ከዚህ ማምለጫ በኋላ ሰውየው የሚመለሰው በበለጠ የተዳከመ፣ ያፈረ፣ ስሜታዊ ዝግጅቱ የተዘጋ እና የትዳር አጋሩን በዓይን ማየት የማይችል ሆኖ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ «ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን አይጠቅምም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን በአንዳችም ስር ከቶ አልገዛም» — 1 ቆሮንቶስ 6፥12 ችግሩ ኃጢአት ሠራሁ ብቻ አይደለም። ጥልቅ ችግሩ ኃጢአቱ በእኔ ላይ መገዛት ሲጀምር ነው። «እቢ» ማለት በማልችልበት ጊዜ፣ እንደሚሰብረኝና እንደሚያጠፋኝ እያወቅሁ ያንኑ በር ደጋግሜ ስከፍት ነው። በውጭ ነፃ ስመስል፣ በውስጤ ግን እስረኛ ስሆን ነው። አንድ ጠቃሚ የስነ-ልቦና መርህ እንዳለው፣ አስገዳጅ ጠባይ (compulsive behavior) የሚቀጥለው በምኞት ብቻ ሳይሆን በቀስቃሾች ጭምር ነው። የተወሰኑ ሁኔታዎች፣ ቦታዎች እና የስሜት ሁኔታዎች ከውድቀት በፊት ሁልጊዜ ይመጣሉ፦ ሌሊት ብቻውን መንቃት ጭንቀት ሐዘን የመገለል ወይም አለመፈለግ ስሜት ከባለቤት ጋር ያለ አለመግባባት ሥራ ፈትነት ስልኩን ወደ መታጠቢያ ቤት ወይም ወደ መኝታ ቤት ይዞ መግባት መሰላቸት (ቦረድ ማለት) የወሲብ ፍላጎትን የሚቀሰቅሱ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶች ለዚህም ነው ማገገም «ደግሜ አላደርገውም» ካለ ቀላል ንግግር በላይ የሆነው። ማገገም የሚጀምረው በታማኝ ጥያቄዎች ነው፦ «መቼ እወድቃለሁ? ለምን እወድቃለሁ? የት እወድቃለሁ? ከመውደቄ በፊት ወዲያውኑ ምን ይፈጠራል?» የቤተክርስቲያን አባቶች እንደሚያስተምሩን፣ አንድ ሐሳብ ትኩረት ሳይሰጠው ከቀረ ማደጉን ይቀጥላል። በመጀመሪያ ልክ እንደ ትንሽ ፍንጣቂ ነው። ገና በጊዜ ከያዝከው ይጠፋል። ችላ ካልከው ግን ወደ አደገኛ የእሳት ነበልባል ይቀየራል። ለዛሬ የሚሆን ተግባራዊ እርምጃ፦ «ቀስቃሾቼ» የሚል ርዕስ ያለው ዝርዝር አዘጋጅ። ለውድቀትህ በር የሚከፍቱ አምስት ነገሮችን ጻፍ። ከዚያም ከእያንዳንዳቸው ቀጥሎ ተግባራዊ ሊሆን የሚችል ሌላ አማራጭ ምላሽ ጻፍ። አብዛኛውን ጊዜ የምትወድቀው ዘግይቶ ከቆየህ በኋላ ከሆነ → ስልኩን ከመኝታ ቤት ውጭ ተወው። ከክርክር በኋላ የምትወድ ከሆነ → ከማምለጥ ይልቅ ሰላምን ፈልግ። ብቸኝነት ቀስቃሹ ከሆነ → የሚታመን ጓደኛን ደውል ወይም ባለህበት ቦታ ውጣ። የተወሰኑ አካውንቶች የሚያፈተኑህ ከሆነ → ሳትደራደር አን-ፎሎ (Unfollow) አድርጋቸው እና ብሎክ (Block) በላቸው። ንስሐ የስሜት ብቻ ጉዳይ አይደለም። ንስሐ አዲስ የአኗኗር ዘይቤ ነው። ጌታ ሆይ፣ ከሕመሜ ወደሚያጠፋኝ በር እንድሸሽ አትፈቅድልኝ። ልቤን በእርግጥ ማርካት የሚችለው አንተ ብቻ ስለሆንክ ወደ አንተ እንድሸሽ አስተምረኝ። #ፖርኖግራፊ_አያረካም #የልብ_ነፃነት #የፈተናውን_ምንጭ_አስወግድ #ንስሐ_ውሳኔ_ነው #አቡነ_ዳዊት_ሐና
видео или голосовое, без подписи
Pornography Doesn't Satisfy... It Steals Satisfaction Many people think pornography brings relief. But the truth is that it only provides temporary numbness. There is a huge difference between relief and numbness. Relief restores a person. Numbness only silences the pain for a little while, then brings it back even stronger. Pornography whispers to a person: “Escape your stress.” “Escape your loneliness.” “Escape your rejection.” “Escape the problems in your home.” But after the escape, the person comes back weaker, ashamed, emotionally closed off, and unable to look their spouse in the eye. The Bible says: "All things are lawful for me, but all things are not helpful. All things are lawful for me, but I will not be brought under the power of any." — 1 Corinthians 6:12 The problem is not only that I sinned. The deeper problem is when the sin begins to rule over me. When I can no longer say no. When I keep opening the same door, even though I know it will break me. When I appear free on the outside, but I am a prisoner on the inside. An important psychological principle is that compulsive behavior is not sustained only by desire—it is sustained by triggers. Certain situations, places, and emotional states often come before a fall: Staying up late alone. Stress. Sadness. Feeling rejected. Conflict with a husband or wife. Idleness. Taking the phone into the bathroom or to bed. Boredom. Sexually suggestive social media accounts. That is why recovery is more than simply saying, “I won't do it again.” Recovery begins with honest questions: "When do I fall? Why do I fall? Where do I fall? What usually happens right before I fall?" The Church Fathers teach us that a thought, if left unattended, continues to grow. At first, it is like a tiny spark. If you deal with it early, it goes out. If you ignore it, it becomes a wildfire. A practical step for today: Create a list titled: "My Triggers." Write down five things that open the door to your fall. Then, next to each one, write a practical alternative response. If you usually fall after staying up late → Leave your phone outside the bedroom. If you usually fall after an argument → Seek peace instead of escaping. If loneliness is the trigger → Call a trusted friend or leave the place where you are. If certain accounts tempt you → Unfollow and block them without negotiation. Repentance is not merely an emotional feeling. Repentance is a new way of living. Lord, do not let me run from my pain to a door that will destroy me. Teach me to run to You, because You alone can truly satisfy my heart. #PornographyDoesNotSatisfy #FreedomOfTheHeart #RemoveTheSourceOfTemptation #RepentanceIsADecision #AbounaDawoudHanna
ሐዋርያትን የመራቸው (በሐዲስ ኪዳን) በሐዲስ ኪዳን ወንጌልን ለአለም ለማድረስ በወጡት ሐዋርያት ላይ ለደረሰው ስደትና መከራ ቅዱስ ሚካኤል የብርታትና የነፃነት መልአክ ሆኖ አገልግሏል። ሐዋርያትን ከወኅኒ ቤት ያወጣቸው፦ ሐዋርያት በምኩራብ ሰብከው በ አይሁድ ቅናት በታሰሩ ጊዜ፣ “የጌታ መልአክ በሌሊት የወኅኒውን ደጅ ከፍቶ አወጣቸው” (የሐዋርያት ሥራ 5፥19)። ቅዱስ ጴጥሮስን ከሄሮድስ እጅ ያዳነው፦ ሄሮድስ ቅዱስ ጴጥሮስን ሊገድለው በሁለት ሰንሰለት አስሮ በጠበቀው ጊዜ፣ መልአኩ መጥቶ ሰንሰለቱን በመበጠስና የብረቱን መዝጊያ በመክፈት በተአምር መርቶ አውጥቶታል (የሐዋርያት ሥራ 12፥7-10)።
ሚ ካ ኤ ል 🌼 ተገፉትን ወገኖች መብት በመጠበቅና ከጨቋኞች እጅ በማውጣት ቅዱስ ሚካኤል ግንባር ቀደም ጠበቃ ነው። የእስራኤል ሕዝብ በግብፅ ሲገፉ፦ የእስራኤል ልጆች በፈርዖን ጭቆና ሥር በነበሩበት ጊዜ፣ በደመናና በእሳት ዓምድ እየተመራጩ ከግብፅ ባርነት እንዲወጡ ያደረገውና ባሕሩን የከፈለው የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው (ዘጸአት 14፥19፣ ዘጸአት 23፥20)። እግዚአብሔርም፦ “በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ፥ ወደ አዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊቱ እሰዳለሁ” ብሏል። ስለ ሙሴ ሥጋ የተከራከረው፦ ዲያብሎስ የሙሴን ሥጋ ለጣዖት አምልኮ ሊጠቀምበትና ሕዝቡን ሊያስት በሞከረ ጊዜ፣ ቅዱስ ሚካኤል ለተገፋውና ለሞተው የእግዚአብሔር ሰው መብት በመቆም ሰይጣንን ገሥጾታል (ይሁዳ 1፥9)።
የኢየሱስ ክርስቶስ የከበረው መልአክ የሆነው ቅዱስ ሚካኤል በምልጃው በረድኤቱ ከእኛ ጋር ይሁን። ነቢያትን የረዳቸው ሐዋርያትን የመራቸው ለአበው ምስጢርን የገለጠ ለተገፉ ጠበቃቸው ሚ ካ ኤ ል 🌼 @WwEotc