Goro Health Center - Dire Dawa
СтатистикаGoro PHCU–Dire Dawa is Public Platform, of Goro PHCU, created to communicate & disseminate only health and health related informations, updates, news, and facts. Youtube link: https://youtube.com/@ghcdire
- Последний пост
- 7 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 20
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- Категория
- Видео
- В каталоге с
- 15 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 373
- 1/48двое суток
- 427
- 1/72трое суток
- 461
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ጎሮ ጤና ጣቢያ EPAQ Cluster አባል ተቋማት በተገኙበት የ2018 በጀት ዓመት 4ኛ ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ተካሄደ። በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ክብርት ዶር ፅጌሬዳ ክፍሌ ጎሮ ጤና ጣቢያ የኢትዮጵያ ጤና ጣቢያዎች ጥምረት ለጥራት ክላስተር ፕሮግራሙን በወጥነት በመተግበር ከተቋሙ አልፎ የአባል ጤና ጣቢያዎች ከፍተኛ ውጤት እንዲያስመዘግቡና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እንዲያሻሽሉ ያስቻለ ጠንካራ አደረጃጀት መሆኑን ገልፀዋል። ዶር ፅጌሬዳ አክለውም ጎሮ ጤና ጣቢያ በብዙ ፕሮግራሞችና ኢንሼቲቮች በሀገር አቀፍ እውቅና ያለው ተቋም መሆኑን ጠቅሰው ሌሎች ተቋማትም ይህንን ልምድና ተሞክሮ ወስደው በመተገበር ማስፋትና እየሰጡ ያሉትን የጤና አገልግሎት ጥራት በስታንዳርዱ መሰረት ማረጋገጥ እንዲችሉ ተጠናክሮ እንደሚሰራ ተናግረዋል። በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት EPAQ Cluster እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና በአዲስ ከተማ ጤና ጣቢያ የተሰራ ምርጥ ተሞክሮ ቀርቦ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በተጨማሪም በመድረኩ ተሳታፊዎች በጎሮ ጤና ጣቢያ የመስክ ምልከታ (Site Visit) ያደረጉ ሲሆን በተቋሙ እየተሰጠ ያለውን የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትና የSBFR ፕሮጄክት ትግበራ ያስገኘውን ለውጥ አድንቀው ወደ ራሳቸው ተቋማትም እንደሚያሰፉ ያላቸውን ፍላጎትና ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የጎሮ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ እንዳላማው እርቅይሁን በቀጣይ EPAQ Cluster EPAQ Cluster አባል ተቋማት መካከል ያለውን ቅንጅትና ትብብር በማጠናከርና አብሮ በመስራት ከዚህ በበለጠ ጥራት ያለው በመረጃ የተደገፈ የጤና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚሰራ ገልፀዋል ። Goro Health Center Center of Excellence Email: ghcdire@gmail.com Telegram: https://t.me/GoroPHCU Facebook: https://www.facebook.com/share/1B4gWe7v2Q/ Website: https://ghcdd.gov.et ለበለጠ መረጃ በ0986200277 ይደውሉ
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ጎሮ ጤና ጣቢያ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ትውውቅ ፕሮግራም ተካሄደ። በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ የፕላንና ፕሮግራም ዳሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አለማየሁ ግርማ ጎሮ ጤና ጣቢያ በአስተዳደሩ ከፍተኛ ተገልጋይ በማስተናገድ ቀዳሚ የሆና በጤና ቢሮ የሚወርዱ ሪፎርሞችንና ኢንሼቲቮችን በተሟላ መልኩ በመተግበር በሀገር አቀፍ እውቅና ያለው ተቋም መሆኑን ገልፀዋል። አቶ አለማየሁ አክለውም ተቋሙ እንደዚህ አፈፃፀሙን በመገምገም ያለበትን ደረጃ ለይቶ የቀጣይ እቅድ ላይ ተወያይቶ ተቋማዊ አደርጎ መተገበር እየሰጠ ያለውን የጤና አገልግሎት ጥራት በማሳደግ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ያለው ጥቅም ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል። በመድረኩ የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ቀርቦ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በተጨማሪም በመድረኩ የተቋሙ SBFR Project ትግበራ የ18 ወራት አፈፃፀም ሪፖርትና የተመዘገበ ውጤት ልምድና ተሞክሮ ቀርቧል። እንዲሁም የጤናው ዘርፍ ሪፎርም እና አክሪዲቴሽን ኦረንቴሽን ለጠቅላላ ሰራተኛው ተሰጧል። በመርሃ-ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የጎሮ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ እንዳላማው እርቅይሁን በቀጣይ የሰራተኞችን የመፈፀም አቅም በማዳበርና የተቋሙን የማስፈፀም አቅም በማሳደግ የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትን ማዘመንና በቴክኖሎጂ ዲጂታላይዝ ማድረግ በመረጃ የተደገፈ ግልፅና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስርዓት ለመገንባት እንደሚሰራ ገልፀዋል ። በመድረኩ በበጀት ዓመቱ የላቀ አፈፃፀም ያስመዘገቡ ሰራተኞችና የስራ ክፍሎች የእውቅናና የምስጋና ሰርተፊኬትና ሜዳልያ ተበርክቶላቸዋል። Goro Health Center Center of Excellence Email: ghcdire@gmail.com Telegram: https://t.me/GoroPHCU Facebook: https://www.facebook.com/share/1B4gWe7v2Q/ Website: https://ghcdd.gov.et ለበለጠ መረጃ በ0986200277 ይደውሉ