Nolawi ኖላዊ
Статистикаይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ነው። እግዚአብሔር አገልግሎቱን ያስፋ! 0911699907 ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
- Последний пост
- 16:31
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 16
- Всего постов
- 29
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Книги (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 810
- 1/48двое суток
- 928
- 1/72трое суток
- 1 001
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
Live stream finished (1 hour)
እግዚአብሔር ትልቅ ነው 3 የመጨረሻው ክፍል ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
2:00 ይጀምራል
Live stream started
ዛሬ ዓርብ ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ላይ ትምህርታችን ይጀምራል :: የትምህርታችን ርእስ " እግዚአብሔር ትልቅ ነው 3 መዝ 144 ፥ 3 ማስታወሻ ብትይዙ ይመከራል። ሌሎች ወገኖቻችንንም ጋብዙ https://t.me/Nolawii
ቅድስት ማርያም/4 ናዝሬት “በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ ፥ ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ ።” ሉቃ. 1 ፡ 26-27 ። መልአኩ ገብርኤል የተላከው ናዝሬት ወደምትባል የገሊላ ከተማ ነው ። ገሊላ ሰሜናዊ የእስራኤል ግዛት ነው ። እስራኤል ሦስት ታላላቅ ግዛቶች ነበሩአት ። ደቡቡ ይሁዳ ፣ ማዕከሉ ሰማርያ ፣ ሰሜኑ ገሊላ ይባላል ። በገሊላ ከሚገኙ አነስተኛ ከተሞች አንድዋ ናዝሬት ናት ። ናዝሬት በብሉይ ኪዳን ስምዋ አልተጠራም ። ታዋቂ የሆኑ ድርጊቶች ያልተከናወኑባት ፣ ስመ ጥር ሰዎች ያልወጡባት ፣ የጦርነትም የዕድገትም መዝገበ ቃላት ያላወቃት አነስተኛ መንደር ነበረች ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመወለዱን ብሥራት የላከው ወደዚህች ወደ ናዝሬት መንደር ነው ። የናዝሬት መንደር የተናቀች ነበረች ። ወደ ተናቀችው መንደር ታላቅ የምሥራች መጣ ። ጌታችን ለልደቱ ቤተ ልሔምን እንደ መረጠ ፣ ለፅንሰቱ ናዝሬትን መረጠ ። እርሱ ከሚጠራበት ስም ገናናው “የናዝሬቱ ኢየሱስ” የሚለው ነው ። የተናቁት ወዳጅ ፣ የምስኪኖች አለኝታ መሆኑን የሚያሳይ ስም ነው ። ናዝሬት በቅርብ ከተሞች እንኳ የተናቀች ለመኖሪያነት የማትመረጥ አነስተኛ መንደር ነበረች ። ማንም የማያውቃት ያቺ ናዝሬት መላው ዓለም ያውቃታል ። የተናቁትን ማክበር እግዚአብሔር ያውቃል ። ትላንት የተናቁ አገራትና ከተሞች ዛሬ እየተወደዱ መጥተዋል ። በተቃራኒው የተከበሩ አገሮችና መንደሮች ተንቀዋል ። በዓለም ላይ በጣም ደምቀው የደበዘዙ ከተሞች ብዙ ናቸው ። ሮም ፣ ባቢሎን ፣ እስክንድሪያ ፣ አንጾኪያ ፣ ቍስጥንጥንያ/ኢስታንቡል ፣ አኵሱም በጣም ስመ ጥር የነበሩ የዓለማችን ከተሞች ናቸው ። ዛሬ ግን ደብዝዘዋል ። ናዝሬት ግን በትንሽ ጀምራ በመላው ዓለም ትታወቃለች ፣ የናዝሬቱ ኢየሱስ በሚለው መጠሪያ ከአምላክ ጋር ስትነሣ ትኖራለች ። እግዚአብሔር የተናቁ አገሮችን ያከብራል ። ዛሬ አገራችን ከዓለም መጨረሻ ሁና ብትታይ እንኳ እግዚአብሔር ቀኝ ኋላ ዙር ያለ ቀን አንደኛ ትሆናለች ። ይህ እንዲሆን የምሥራቹን መቀበል ያስፈልጋል ። ወንጌል በራሱ በእግዚአብሔር ፣ በአበው ፣ በነቢያት ፣ በካህናት ፣ በመልአክ ፣ በድንግል ማርያም ፣ በሐዋርያት የተሰበከ ትውልደ ሐረግ ያለው መልእክት ነው ። ይህን ወንጌል አምኖ መኖር ክብርን ያሰጣል ። እግዚአብሔር ናዝሬትን ብቻ ሳይሆን ታናሽ ብላቴና የምትሆነውንም ድንግል ማርያምንም አከበረ ። እርስዋ ራስዋ አክባሪነቱን ስትገልጥ፡- “እነሆም ፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤” አለች ።(ሉቃ. 1 ፡ 48) ። ከዛሬ ጀምሮ የሚለውን እናስተውል ። ከዚህ ቀን በፊት ማንም የተዘጋጀላትን ክብር አላወቀም ነበር ። እርስዋም አላወቀችም ነበር ። አሁን ግን የአምላክ እናት ሁናለችና ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት እንደሚሏት ተናገረች ። እግዚአብሔር የተናቁ መንደሮችን ፣ የተናቁ ሰዎችን ያከብራል ። እመቤታችን አሁንም በተደነቀው ጸሎትዋ፡- “የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና” ብላለች ። እግዚአብሔር ያያል ። የተናቁትን ለክብር ቀን ያስባል ። ሔዋን ተዋርዳ ነበር ፣ አሁን አያት ። በልጅ ልጅዋ በድንግል ማርያም በኩል የሔዋን ውርደት ተካሰ ። ሔዋን ካመጣችው ውርደት ለድንግል ማርያም የሆነው ክብር በለጠ ። በዚህም የሴት ዓለም ከበረ ። በኮልታፋ ምላሳችን ሰዎች ይንቁን ይሆን ? እስራኤልን እየመራ ያወጣው ሙሴ ኮልታፋ ነበር ። እግዚአብሔር ከአፌ ቅቤው ከአሮን ይልቅ ሙሴን መረጠ ። እንደ ሰው ቢሆን ቃላተኛው አሮን የሕዝብ መሪ ፣ ሙሴ ደግሞ ካህንና ጸሎት አሳራጊ በሆኑ ነበር ። እንደ ሰው ቢሆን ብሉያትን ያጠና ጳውሎስ መምህረ አይሁድ ፣ ጴጥሮስ መምህረ አሕዛብ ተደርገው በተደለደሉ ነበር ። ኃይላችን የማያግዘው ፣ ድካማችን የማይመልሰው እግዚአብሔር በእውነት ድንቅ ነው ። እኔም በልቡናዬ ጉልበት ተንበርክኬ አመሰግነዋለሁ ። ደካማ የሆነ የአካል ክፍል ስላለን ፣ ቁመናችን ስለማይማርክ ሰዎች እንደ ናቁን እናስብ ይሆን ? እነ ኤልያብን ትቶ አጭሩን ዳዊትን ፣ እነ ቀያፋን ጥሎ ቁመተ ትንሽ ዘኬዎስን የመረጠ አምላክ ዛሬም አሠራሩ አልተለወጠም ። ከተናቀች አገር በመምጣታችን እየተጨነቅን ይሆን ? እግዚአብሔር ከፍታን ሲያወርሰን ማንም አያግዘውም። ይቀጥላል ዲያቆን አሸናፊ መኰንን ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም.
видео или голосовое, без подписи
ገለል በል ከፊቴ አገርህ ከድታህ፣ ወገንህ ለግድያው ስም ሰጥቶ መሣሪያ የወደረብህ ፣ ጥፋትህ ጠፍቶህ ፣ ያልበደልከውን ካስ ስትባል ግራ የገባህ ፣ ጥፋትህንም ገዳይህንም ዛሬ ስታያቸው ሕልም ዓለም ውስጥ የገባህ ፣ እመጣለሁ ብለህ ደውለህ ሳትደርስ የቀረኸው አንተ ብላሽ ገለል በል ከፊቴ ። ግንድ ተማፅኖ በሚዳንበት አገር የአምላክህን ስም ጠርተህም የሚራራ ያጣኸው አንተ ጀምር ገለል በል ከፊቴ። ምድር የጌታ ነው ብለህ ተቀምጠህ የሰው ሲሆንብህ ፣ መንገድ የእግዜር ነው ተብለህ አድገህ ሰው አምላክ ካልሆንሁ ሲልህ ጭልም ያለብህ አንተ እሸት ገለል በል ከፊቴ ። ከመቼው አድገህ ለሞት በቃህ፣ ለማታውቀው አያትህ ዕዳ ከፋይ ለመሆን በቃህ። አንተ ሠርክ በጅምር ገለል በል ከፊቴ ። እንዳላለቅስልህ ለማልቀስም ቀን ይፈልጋል ፣ የማልቀሻዋ ቤትም ቤተ ፈያት /የወንበዴ ዋሻ/ ሆናለች። ወንድ በጠላው ዘመን ተወልደህ ፣ ወጣትነትህ እንደ ዕዳ በሚቆጠርበት ምድር ተገኝተህ ፣ በቅጡ መኖር በቅጡ መሞት አቅቶህ የተሰቃየኸው አንተ ጎበዝ ገለል በል ከፊቴ። ስለ ወንድ ልጅ አምላክ ብለህ ስትለምን የተጨከነብህ ፣ እናትህን ልጅህን እያሰብህ በሜዳ የቀረኸው ፣ ገዳይህ በደሉ እንዳይጠፋ ፎቶ አንሥቶ የሚገድልህ ፣ ቪድዮ ቀርፆ ላይበላህ የሚያርድህ አንተ ወጣት ገለል በል ከፊቴ ። የወጣት ሞት ፣ የወንድ ልጅ አበሳ ሃምሳ ዓመት ሞላው ፣ በነጻ ኖረህ በዋጋ ትሞታለህ። ለመብል የረሳህ ለጥይት ያስታውስሃል ። አንተ በሥጋ ሞትህ፣ እኛ ግን በሕሊና እንሞታለን ። አንተ አንድ ጊዜ ሞትህ ቋሚው ደጋግሞ ይሞታል። የሰው አንገት አንድ ነውና ሰው የሆነ ሁሉ ያዝናል። አንተ ስቃይህ ለአንድ ሰዓት ነው፣ ገዳዮችህ ግን ዘመናቸው ሁሉ የስቃይ ነው። ደምህን ደመ ኢየሱስ ይዋቀሰዋል ! አልተሸካከፈም ያገሬ አዝመራው ፣ ዛላው ዛላው ወድቋል በየጎዳናው ። የሚፈሰው ደም ይብቃ!!!
የመጽሐፍ ስጦታ ተማሪዎች የሆናችሁ ና መጽሐፍ መግዛት የማትችሉ ከዲያቆን አሸናፊ መኰንን መጻሕፍት በስጦታ ታገኛላችሁ። 0911699907 በቴሌግራም አሳውቁን! እነዚህ መጻሕፍት በስጦታ እንዲተላለፉ የገንዘብ ስጦታ ያደረጋችሁ ወዳጆች እግዚአብሔር በሰማያዊና በምድራዊ በረከት ይባርካችሁ!
የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! በዚህ ክረምት ከዲያቆን አሸናፊ መኰንን ሥራዎች የመጻሕፍት ስጦታ ለተማሪዎች፣ ለእስረኞች፣ መግዛት ለማይችሉ ፣ ለቤተ መጻሕፍት ለመስጠት አስበናል። ይህን በረከት ለመሳተፍ የምትፈልጉ ቀጥሎ ባለው አካውንት የፈቀዳችሁትን መስጠት ትችላላችሁ ። ያስገባችሁበትን በቴሌግራም 0911699907 ላኩልን ! የእግዚአብሔር በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን! አሸናፊ መኰንን ወርቁ Ashenafi Mekonnen worku የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000165078482
ቅድስት ማርያም/2 የሰው ልጆች በያዙት ነገር የማይረኩት ሁልጊዜም የሚመጣውን የሚናፍቁት መንግሥተ ሰማያት ሲደርሱ እንዲያርፉ ሁነው ስለ ተሠሩ ነው ። ሰይጣን ሰዎችን በሽንገላ ከጣለበት ነገር አንዱ ገንዘብና ሥልጣን ቢኖራችሁ እርካታን ታገኛላችሁ ብሎ በማታለል ነው ። ሰዎች ገንዘብና ሥልጣንን ሲይዙ የሚገጥማቸው ባዶነትና እዚያ ለመድረስ የከፈሉትን ተጋድሎ ማስታረቅ አቅቷቸው ራሳቸውን በተስፋ ማጣት ይጎዱታል ። የሰው ልጆችን በእቅፉ ሊያስጠጋና ዘላለማዊ መልስ ሊሆናቸው አምላክ ወደ ምድር መምጣት ፈለገ ። የአምላክ ጉብኝት ዕለታዊና ያልተቋረጠ ቢሆንም ይህ መምጣት ግን በሥጋ መገለጥ ነው ። በክርስቶስ መምጣት ዓለም መልካም አልተደረገለትም ፣ መልካም ሆነለት ። የማያቋርጥ ደግነት ፈሰሰ ። ሁለት መልእክተኞች ከንጉሡ ፊት ፊት ይሄዳሉ ። አንደኛው ሰማያዊ ፣ አንደኛው ምድራዊ ነው ። ምድራዊ ጥሪት ሁለቱም አልነበራቸውም ። በሰማያዊ ጸጋ አሸብርቀዋል ። እነርሱም መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልና መጥምቁ ዮሐንስ ናቸው ። ለአምላክ መወለድ ፣ ለሰው ዘር መዳን የምሥራች እንዲነግር የተላከ መልአኩ ገብርኤል ነው ። መልአክ በወደቀ ጊዜ አምላክ መልአክ ሁኖ ለምን አላዳነም ሰው በወደቀ ጊዜ እንዴት ሰው ሆነ አላለም ። መልአኩ በሰው መዳን ደስተኛ ነበረ ። የአምላክ ሰው መሆን ሂደት በሰማይ በተሰማ ጊዜ ታላቅ ደስታ ነበረ ። ዓለም በተፈጠረበት ቀን ዓለም እንዲድን ፣ ብሥራት እንዲነገር መልአኩ ተጠራ ። ባለቤቱ ሰማይን ሳይሰናበት በምድር ይገኛል ። ምድርን እንግዳ ሳይሆንባት በሥጋ እንግድነት ይገለጥባታል ። የእግዚአብሔር ልጅነቱን ሳይለቅ የሰው ልጅ ይባላል ። ለአምላክ ልጅ የሰው ልጅ መባል እንግዳ ነው ። ካለንበት የመጣው ካለበት ሊያደርሰን ነው ። ሕዝብና አሕዛብ ሁሉ በዘመናት የናፈቁት ክርስቶስ በሥጋ እየመጣ ነው ። እንግዳን ቤተ ዘመድ ይቀበለዋል ፣ እልልታ ይሰማል ። አንዲት ድንግል ግን በቤትዋ ሳይሆን በማኅፀንዋ ተቀበለችው ። ጉዳዩ እስከ ጊዜው ምሥጢር ነበርና የምሥጢር መዝገብ የሆነችው ማርያም ሰወረችው ። እርስዋ ከሴቶች የተለየች ናት ። ሔዋን ምሥጢር አውጥታ ሞትን ጋበዘች ፣ ምሥጢር ጠባቂዋ የሕይወትን ፍሬ አስገኘች ። የመምጣቱን ዜና የሚናገሩ የተቀደሱ ትንቢቶች በእኔ ይፈጸማል ብላ አንድም ቀን አስባ አታውቅም ። ከሥጋዋ ሥጋ ፣ ከነፍስዋ ነፍስ ነሥቶ ፣ አገሯን አገሩ አድርጎ ሊወለድ መጣ ። አስደናቂው ነገር ከአባቱ የተወለደው መለኮታዊው ልደት የዘመን መቀዳደም የለውም ። እናቱ በሥጋ ልደት እየቀደመችው ቢሆንም የፈጠራት ግን እርሱ ነው ። እናቱን የጦረ ልጅ እናውቃለን ፣ እናቱን የፈጠረ ልጅ ግን ታይቶ ተሰምቶ አያውቅም ። አባቱም በዘመን ያልቀደመው ፣ በክብር ያልበለጠው ይህ ሕፃን እንደምን ያለ ነው !! ዘመን የሌለው ሁኖ ሲኖር ሳለ በዘመን ቋጠሮ ውስጥ የገባው ፣ እርሱ ዘመን የለሽ እርሱ ዘመነኛ ነው ። ዘመናችንን ሊቀድስ ፣ ዓመተ ፍዳን ወደ ዓመተ ምሕረት ፣ ዓመተ ኵነኔን ወደ ዓመተ ጽድቅ ሊለውጥ መጣ ። የፈጠረውን ሥጋ ተዋሐደ ። ለአባቱ የበኵር ልጅ የነበረው ለእናቱም የበኵር ልጅ ሆነ ። ሁለት አባት የለውምና ያለ ወንድ ዘር ተወለደ ። በቀዳማዊ ልደቱ እናት ፣ በደኃራዊ ልደቱ አባት የለውም ። በቀዳማዊ ልደቱ ከአምላክ የተገኘ አምላክ ነው ፣ በደኃራዊ ልደቱ ፍጹም ሰው ነው ። አምላክነቱ ሰውነቱን ሳያጠፋ ፣ ሰውነቱም አምላክነቱን ሳይሰበስብ አንዱ ክርስቶስ በተዋሕዶ ይኖራል ። እግዚአብሔር አንድነት መገለጫው ነው ። ሦስት አካል አንድ አምላክ ነው ፤ አሁንም ክርስቶስ ከሁለት አካል አንድ አካል ፣ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሁኖ በአንድነት ይኖራል ። አንድ ስንሆን እግዚአብሔርን እንመስላለን ። የእግዚአብሔርን የፍቅሩን ውበት ፣ ድሀና ባለጠጋ ፣ ጥቁርና ነጭ ሳይለይ ሁሉም ይናፍቀው ነበር ። ይህን የውበት ፀሐይ ቀና ብሎ ለማየት ሰው በኃጢአት ጎበጠ ፤ ዝቅ ብሎ ያየው ዘንድ በበረት ተወለደ ። ሕፃናትን ለማስተማር በእነርሱ መጠን ዝቅ ብሎ በቁመታቸው ልክ ተንበርክኮ መናገር ውጤታማ ያደርጋል ። እውነተኛው የሕይወት መምህር በእኛ ሥጋ ተገለጠ ። ጣዖትን ከሚሻ ሕፃንነት አዳነን ። ስምዖን የቀሬናው በድንገት መስቀል ተሸከመ ። ድንግል ማርያም ግን በድንገት የአምላክ እናት አልሆነችም ። መሢሑን እጅግ የምትናፍቅ ፣ የብሉይ ኪዳም ትንቢቶችን የምታጠና ፣ በእግዚአብሔር ቤት እግዚአብሔርን የምትጠባበቅ ነበረች ። እግዚአብሔር ንጉሥ ነውና ከለመኑት በላይ ይሰጣል ሲባል ይሰማ ነበር ። ያለመኑትንም እንደሚሰጥ በድንግል ማርያም ታየ ። እርሱም ወላዲተ አምላክ መባል ነው ። ነቢይነትም ፣ ሐዋርያነትም ፣ ሰማዕትነትም ለብዙዎች ይሰጣል ። ለድንግል ማርያም የተሰጠው ግን የማይደገም ጸጋ ነው ። በአምላክ ሰው መሆን ኃይሉ ፣ ዳኝነቱ ፣ ፍርዱ ፣ ችሎታው ሳይሆን ፍቅሩ ተገለጠ ። የሰው ልጅ እግዚአብሔር ነፍጎኛል ብሎ ከሰይጣን ጋር አምላኩን አምቶ ነበር ። ስለዚህ በፍቅሩ ተገለጠ ። እኛ የአባትነት ፍቅር የሚያድርብን ልጅ ስንወልድ ነው ፣ እግዚአብሔር ግን የዘላለም አባት ነው ። ፍቅርንም በእኛ አልተለማመደም ፣ የዘላለም ፍቅር ነው ። መለኮት እኔ ልሙት ብሎ የመጨረሻውን መሐላ ለወዳጆቹ ምሎ ነበር ። በባሕርዩ አይሞትምና መሐላው ተንጠለጠለ ። የሚሞትበትን ሥጋ ለብሶ በመስቀል ላይ ዋለ ። የመጨረሻውን መሐላና ፍቅር በተግባር ገለጠ ። እኔ ልሙት ያሉን ብዙዎች ናቸው ፣ ሞተው ግን አላሳዩንም ። ሩቅ ሁኖ ማዘዝ ቀላል ነው እያሉ ሰዎች አጉረምርመው ነበርና በቅርብ ተገኝቶ ታዘዘ ፣ የሰጠውንም ሕግ ፈጸመ ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞት የሌለበት የዘላለም አባት ፣ የሚመጣው ንጉሥ ፣ የሚያሳርፈው የሰላም አለቃ ፣ የሚራራው ሊቀ ካህን ፣ ልቅደምልህ የሚል መሥዋዕት ፣ እጅግ ልበ ሰፊ ፣ ዝንጉዎችን የሚታገሥ ፣ የኃጢአተኞች ወዳጅ ፣ ሸፍኖ የሚሠራ ፣ አጋልጦ የማያዋርድ ፣ የሕመምተኞች ጤና ፣ የጥያቄዎች ሁሉ መልስ ፣ በለጋስነት ሁሉን የሚሰጥ ፣ የቆሰለ ልብን በደሙ የሚፈውስ ፣ ነፍስን የሚገዛ የሰማይ ልዑል ፣ አገር ለሌላቸው አገራቸው ፣ በግፍ ለሚገደሉት ተበቃያቸው ፣ የወደቁትን በተስፋ ቃል የሚያናግር ፣ አገሩ እዚህ ነው የማይባል ፣ ሁሉም መልኬ የሚለው ፣ የዘር ልዩነትን ያጠፋ ፣ የድሆችን ንቀት ያስወገደ ነው ። የዚህ ታላቅ ጌታ እናት ነሽና ማርያም ሆይ ደስታ ይገባሻል ! ክርስቶስ ሆይ የታመመው አልድን ፣ የወጣው አልገባ ያለበትን ይህን ዘመን ስለ እናት ስለ ማርያም ብለህ ለውጠው ! ይቀጥላል ዲያቆን አሸናፊ መኰንን ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም.
видео или голосовое, без подписи
ቅድስት ማርያም “በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ ፥ ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ ።” ሉቃ. 1 ፡ 26-27 ። ዓለም ሁሉ በታላቅ ኀዘን ፣ ለሞትም በተሸነፈ ልብ ይኖር ነበር ። መዳን በሰዎች ፣ ሰዎችም በሚያደርጉት ጥረት የማይገኝ መሆኑ ታወቀ ። የእንስሳት መሥዋዕትም ሥጋዊና መንፈሳዊ ሞትን ማስቀረት አልቻለም ። መሥዋዕተ እንስሳ ለጊዜው ቍጣን ቢያበርድም የገነትን በር ከፍቶ ጽኑ ይቅርታን ማምጣት አልቻለም ። የአበው ተስፋ ፣ የነቢያት ትንቢት ፣ የአዋቂዎች ሱባዔ ዘገየ እየተባለ ይታሰብ ነበር ። ፈሪሳውያን በታላቅ ቁጭት ሕዝቡን ለመሢሑ መምጣት ያነሣሡ ነበር ። ከእነርሱ የተከፈሉ ኤሤናውያንም በሙት ባሕር ዳርቻ በኩምራን ገዳም ተወስነው ፣ በጾምና በጸሎት ጸንተው ፣ መጻሕፍትን እየጻፉ መሢሑን ቶሎ ና እያሉ ይናፍቁት ነበር ። የእግዚአብሔር ጠባዩ ይህ ነው ። እያለ ና ይባላል ። በልብ ተቀምጦ ይናፍቃል ። የእግዚአብሔር የፍቅር ልብ በሰው ላይ አዝኖ ነበር ። ካሣ ሊከፈል ፣ መዳን ሊፈጸም ፣ ሰውም ወደ ቤቱ ሊመለስ ፣ የዳግም ልደት ምሥጢር ሊጀመር የግድ ያስፈልጋል ። ሰው እንደ ወጣ እንዲቀር የእግዚአብሔር ዘላለማዊ አሳብና ጽኑ ፍቅሩ አላስቻለውም ። እንደ ራሱ የጠፋው ሰው እንደ እግዚአብሔር መዳን አለበት ። ሰው እግዚአብሔርን መምሰል አለበት ተብሎ ስለ ቅድስና ሲነገረው ነበር ። ሰውም በእግዚአብሔር አምሳል ተፈጠረ እየተባለ ዘወትር ይዘመራል ። አሁን ግን እግዚአብሔር ሰውን ሊመስል ፣ የሰውንም ሥጋ ሊለብስ ዘመን ደረሰ ። ይህ ሥጋ በፈላስፎች እንደ ርኵስ ተቆጥሮ ነበር ። ሥጋንም በማጎሳቆል አምላክን ደስ ማሰኘት የሚል የግሪካውያን ፍልስፍና ተስፋፍቶ ነበር ። ሥጋን በመልበሱ ሥጋን ሊያከብረው ፈለገ ። በቀጠሮው ማርፈድ የማያውቅ በሰዓቱ ፣ በቦታው የሚገኝ እግዚአብሔር በስድስተኛው ወር በናዝሬት ገሊላ ተገኘ ። እግዚአብሔር የዘገየ የሚመስለን በእኛ ሰዓት ስለምንጠብቀው ነው ። የእግዚአብሔር ተስፋ በእኛ ጊዜ ቢፈጸም ይጎዳናል ፤ ተስፋው በራሱ ጊዜ ሲፈጸም ይጠቅመናል ። እስራኤልን በምድረ በዳ እየመገበና ዐርባ ዓመት እያስጠበቀ በከነዓን ደግሞ አሞራውያንን ለንስሐ ጊዜ እየሰጠ ነበር ። እኛን እዚህ ሲያቆየን እነዚያን ለንስሐ እየጠበቀ ነው ። እኛ በትዕግሥት ስንጠብቅ እግዚአብሔር ደግሞ የታገሣቸው ሰዎች አሉ ። የእኛ ተስፋ በእኛ ጊዜ ሲፈጸም የእነርሱ ንስሐ ይቀራል ። የእኛ በረከት የዘገየ የመሰለን የሌሎች ሕይወት እየዳነ ስለ ነበር ነው ። ሐኪሙ በቀዶ ጥገና ክፍል ቢዘገይ የእኛ ኪኒን ግን በደቂቃ የሚታዘዝ ፣ ዓመታዊ ምርመራችን ጊዜ የሚሰጥ ነው ። ዓመታዊ ምርመራችን ዘገየ ስንለው እዚያ ጋ ዛሬ ካልሠራላቸው የሚሞቱ ወገኖች ገጥመውት ነው ። እግዚአብሔር የዘገየ ሲመስለን እየፈጠነ ፣ የረሳን ሲመስለን ታላቅ ፍቅርን እየገለጠ ነው ። በራሱ ጊዜ የሚሠራው አምላክ መልአኩ ገብርኤልን ሊልክ ወደ ታላቁ ዙፋን ጠራው ። ከብዙ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል የተመረጠው ለምን ይሆን ? ብለን መጠየቃችን አይቀርም ። ከ600 ዓመታት በፊት መሢሑ የሚወለድበትና የሚሰቀልበት የተሰፈረ የሱባዔ ቍጥር ለነቢዩ ዳንኤል የተገለጠው በቅዱስ ገብርኤል በኩል ነው (ዳን. 9 ፡ 24-27) ። አሁን የሱባዔው ፍጻሜ መሆኑን ለመግለጥ ወደ ድንግል ማርያም ተላከ ። በስድስተኛው ወር ሲል በስድስት መቶኛው ዓመት ማለትም ነው ። ለዳንኤል በተገለጠ በስድስት መቶኛው ዓመት መልአኩ ገብርኤል ለድንግል ማርያም ተገለጠ ። በባቢሎን ግዞት የነበሩት በዚህ የሱባዔ ምሥጢር ደስ አላቸው ። መሢሑ መምጣቱን መስማት የልብ ድጋፍ ሆናቸው ። እግዚአብሔር ታዳጊ ነው ብለው ዘመሩ ። ቀጥሎ የሚታያቸው የፈረሰው መቅደስ መሠራት ፣ ማኅበረ እስራኤል እንደገና ለዝማሬ መቆም ነው ። እስራኤል በባርነት እንደ ተጋዙ ዓለም በሙሉ ወደ ሲኦል ተግዞ ነበር ። እስራኤልን ወክሎ የምሥራቹን ዳንኤል እንደ ሰማ የሰውን ዘር ወክላ ድኅነተ ዓለምን የሰማች ድንግል ማርያም ናት ። ድንግል ማርያም የሰማችው ለመላው የሰው ዘር የሚሆነውን የምሥራች ነው ። ነቢዩ ዳንኤል ግን የሰማው ለእስራኤል ብቻ የሆነውን የምሥራች ነው ። የእግዚአብሔር ቃል የመጣላቸው ነቢያት ይባላሉ ፣ ድንግል ማርያምም የእግዚአብሔር ቃል መጥቶላታልና ነቢይት ትባላለች ። ለእስራኤል ብሔራዊ ጥያቄና ለሰው ዘር ዓለም አቀፋዊ እንቆቅልሽ መልሱ አንድ ነበረ ። እርሱም የመሢሑ መምጣት ነው ። ነቢዩ ዳንኤል በታላቅ ሱባዔ ሳለ የመሢሑ መምጣት በተሰፈረ ዘመን ተገለጠለት ። ድንግል ማርያም በታላቅ ዝግጅት ላይ ሳለች ፣ በጸሎትና ቃሉን በማንበብ ስትተጋ የምሥራች መጣላት ። እንደ ንጉሥ ሳኦል በመንገድ የምሥራች የመጣላት ሳትሆን ለቃሉ ፍቅር ሕይወትዋን ሰጥታ ሳለች የምሥራቹ መጣ ። ቃሉን ስታፈቅር ቃለ አብ ኢየሱስ ከእርስዋ ሰው ሊሆን መጣ ። ቃልን ሰምታ ቃልን ፀነሰች ። የአምላክ አገልጋይ መሆን ስትሻ ወላዲተ አምላክ ለመሆን በቃች ! ይቀጥላል ዲያቆን አሸናፊ መኰንን ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም.
የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! በዚህ ክረምት ከዲያቆን አሸናፊ መኰንን ሥራዎች የመጻሕፍት ስጦታ ለተማሪዎች፣ ለእስረኞች፣ መግዛት ለማይችሉ ፣ ለቤተ መጻሕፍት ለመስጠት አስበናል። ይህን በረከት ለመሳተፍ የምትፈልጉ ቀጥሎ ባለው አካውንት የፈቀዳችሁትን መስጠት ትችላላችሁ ። ያስገባችሁበትን በቴሌግራም 0911699907 ላኩልን ! የእግዚአብሔር በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን! አሸናፊ መኰንን ወርቁ Ashenafi Mekonnen worku የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000165078482
የመጽሐፍ ስጦታ ተማሪዎች የሆናችሁ ና መጽሐፍ መግዛት የማትችሉ ከዲያቆን አሸናፊ መኰንን መጻሕፍት በስጦታ ታገኛላችሁ። 0911699907 በቴሌግራም አሳውቁን! እነዚህ መጻሕፍት በስጦታ እንዲተላለፉ የገንዘብ ስጦታ ያደረጋችሁ ወዳጆች እግዚአብሔር በሰማያዊና በምድራዊ በረከት ይባርካችሁ!
እግዚአብሔር ትልቅ ነው 2 ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
Live stream finished (1 hour)
4:00 ትምህርት ይጀምራል
Live stream started