Rafidim Youth Academy Public Relation Channel
Статистика"ተማሪዎች ላይ መስራት አገር ላይ መስራት ነው!"
- Последний пост
- 16 июл.
- Последнее чтение
- 13 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 20
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- —
- 1/48двое суток
- —
- 1/72трое суток
- —
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ለፈረንሣይ ቅርንጫፍ የአንደኛ ደረጃ እና ለቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን እንዲሁም ለቂርቆስ ቅርንጫፍ ቅድመ መደበኛ ወይም ኬጂ ትምህርት ቤታችን ቤተሰቦች በሙሉ 👇 በሁለቱም ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ እና የፈረንሳይ ቅርንጫፍ ደግሞ የአንደኛ ደረጃ እና የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ በይፋ መጀመሩን ለማብሰር እንወዳለን ። በመሆኑም እንደሁልጊዜው ቀድመን የምንመዘግበው ነባር ተማሪዎቻችንን በመሆኑ ነባር ተማሪዎች ቀድማችሁ መመዝገብ አለባችሁ ። ማሳሰቢያ ፦ ለነባር ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቀነ ገደቡም ከነገ 10 /11/ 2018 ዓ.ም እስከ 15 / 11 / 2018 ዓ.ም ድረስ ሲሆን በእነዚህ ቀናት ብቻ መጥታችሁ መመዝገብ አለባችሁ። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በኋላ ላይ ለሚፈጠረው መጨናነቅም ሆነ የቦታ እጥረት ክፍተት ትምህርት ቤቱ ሃላፊነት የማይወስድ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን ። መልካም ምሽት
ዛሬ የትምህርት ቤታችን የራፊዲም ታላቅ ድግስ ተደርጓል ። 👏👏👏👏👏👏👏 ቤተሰቦቻችን ይህንን ደስ የሚል እና የሚያኮራ ጉዞ ከእናንተ ጋር እያደረግን ስለሆነ እጅግ ደስተኞች ነን ። ሃገርን የሚሰራ ትውልድ የመቅረፅ ትልቅ ሃላፊነትን እየተወጣን እንዳለን እናምናለን ። ለዚህም ደግሞ ዛሬ ያስመረቅናቸው ህፃናቶቻችን እና በዬደረጃው ጀግና ተማሪዎች ሆነው አንደኛ የሚወጡት አዳጊ ልጆቻችን ፤ ከውጤትም በላይ የሆነው ደግሞ የተማሪዎቻችን ግብረ ገብነት ስኬቶቻችንን የምንለካባቸው ግልፅ ማሳያዎች ናቸው ። ዛሬ በአምባሳደር ቲያትር ቤት ከ500 በላይ ቤተሰቦቻችን የታደማችሁበት ፤ ኢትዮጵያን በትንሽ መድረክ ተወክላ ያዬንበት ቀን ነው ። በውዝዋዜ ፣ በድራማ በመዝሙሮች ቀናችን አምሮ ውሏል ። የታሪካዊ አርበኞች ታሪክ በልጆቻችን ጣፋጭ አንደበት ሲወሳ ነበር ። ዛሬ በሁለቱም ቅርንጫፍ 137 የኬጂ ተማሪዎችን መርቀን ወደ አንደኛ ክፍል ያሸጋገርንበት ዕለትም ነው ። ወደፊታችን ብሩህ መሆኑንም የትምህርት ቤታችን ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢንያም ግርማ የደረስንበትን ከፍታ ገልፀውልናል ። በዚህ መርሃግብር በዓመቱ በነበረው የክፍል ለክፍል ወድድር ከዬክፍላቸው አሸናፊ በመሆን ያጠናቀቁትን የምስክር ወረቀት የሰጠን ሲሆን ከሁለቱም ቅርንጫፍ ደግሞ የአሸናፊዎች አሸናፊ በመሆን ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ የወጡትን ተማሪዎች ሽልማት ሸልመናል ። በቀጣዩ ዓመት የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ለመሆን ዛሬ ያስመረቅናቸው የኬጂ ተማሪዎቻችንም በቀጣይ ዓመት እንግዳ ነገር እንዳይሆንባቸው እና በደንብ እንዲላመዱት ብለን በማሰብ በዚህ ዓመት የክፍል ለክፍል ውድድር ማድረጋችን ይታወሳል ። በዚህም በዬቅርንጫፉ አንደኛ የወጡት ተማሪዎች ተሸልመዋል ። በዓመቱ ትምህርት ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ በመሆን በዬክፍሉ ያጠናቀቁ ተማሪዎችን የወርቅ የብር እና የነሃስ ሜዳሊያ ሸልመናል ። ከአጠቃላይ ክፍሎችም አንደኛ በመሆን በሁለቱም ቅርንጫፍ ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎቻችንን ደግሞ የዋንጫ ሽልማት ሸልመናል ። በዚህ አጋጣሚ እነዚህ በሁለቱም ቅርንጫፍ አንደኛ የሆኑት ተማሪዎቻችን ሴቶች ናቸው ። ወደፊት ለሃገራቸው ብዙ እንደሚያበረክቱ እናምንባቸዋለን ። እንኳን ለዚች ቀን አደረሰን ! ራፊዲም ትምህርት ቤት የእውቀት ቤት !
ነገ በዕለተ ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን የዓመቱ ስኬታማ የመማር እና የማስተማር ሥራችንን እና የድካማችንን ፍሬ የምናይበት ዕለት ነው ። በእርግጥ የራፊዲም ጥረት ፤ ትጋት እና ሂደት የዓመት ሳይሆን የዓመታት መሆኑ እርግጥ ነው ። ነገእንደ አምና እንደ ታች አምናው የቅድመ መደበኛ ተማሪዎቻችንን ልናስመርቅ ፣ የደረጃ ተማሪዎቻችንን ልንሸልም ፣ መምህራኖቻችንን ልናመሰግን ብሎም ዳግም ለሌላ አዲስ ዓመት እና አዲስ ቀን ልንዘጋጅ የዓመቱን ሥራችንን ልንዘጋ ነው ። ነገ ታላቁ ድግሳችን እንደ አምናው ሁሉ በተመሳሳይ በአምባሳደር ቲያትር ቤት ይደረጋል ። ታዲያ ወላጆች እንዲሁም ተማሪዎች ጠዋት 1 : 30 በስፍራው በመገኘት ያለንን ሰዓት በአግባቡ እንድንጠቀም እናሳስባለን ። እንኳን ለዚች ቀን አደረሰን 👏
በፈረንሳይ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን የክልል አቀፍ ፈተና ካስፈተንናቸው የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች 97 % ማሳፋችንን እንገልፃለን ። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የስድስተኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ደግሞ እንደተለቀቀ የምናሳውቃችሁ ይሆናል ።
👉 እንደሚታወቀው የስድስተኛ እና የስምንተኛ ክፍል የክልል አቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት በዛሬው ዕለት ተለቋል ። ታዲያ እኛም በቂርቆስ ቅርንጫፍ ትምህርት ቤታችን 100 % ተማሪዎቻችንን አሳልፈናል ። ከስድስተኛ ክፍል 51 ተማሪዎችን ከስምንተኛ ክፍል ደግሞ 42 ተማሪዎችን አሳልፈን እጅግ ደስ ብሎናል ። እንደ ትምህርት ቤትም ታላቅ ኩራት ይሰማናል ። 👉 ታዲያ በዚሁ አያይዘን የምናስታውሳችሁ የፊታችን ቅዳሜ በ27 / 10 / 2018 ዓ.ም የትምህርት ቤታችን የዓመቱ ትምህርት የመዝጊያ መርሃግብር በደማቅ ሁኔታ በአምባሳደር ቲያትር ቤት ይደረጋል ። የደረጃ ተማሪዎች እና የጥያቄ እና መልስ ውድድርን ከ 1ኛ እስከ 3ኛ ሁናችሁ ያጠናቀቃችሁ ተማሪዎች በዕለቱ ከጠዋቱ አንድ ተኩል ላይ እንድትገኙ እያሳስባለን ። መልካም ምሸት 👏
በዓመቱ በተደረገው የጥያቄ እና መልስ ውድድር ከ1 እስከ 9 የወጡ ተማሪዎቻችን ናቸው ።
без подписи
የተማሪዎች ሙዝ የመብላት ውድድር እጅግ አዝናኝ ነበር ።
без подписи
без подписи
👉 እንደሚታወቀው በሁለቱም ቅርንጫፍ ትምህርት ቤቶቻችን የሁለተኛውን መንፈቅ ዓመት የአጋማሽ ፈተና ሰጥተን ጨርሰናል ። በመሆኑም በዛሬው ዕለት በሁለቱም ቅርንጫፍ ለተማሪዎቻችን የፈተና ወረቀቶቻቸውን መልሰናል ። 👉 ዛሬ ደግሞ በፈረንሳይ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን ወደ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚሸጋገሩትን የኬጂ 3 ተመራቂ ተማሪዎችን ምክንያት በማድረግ የመዝጊያ እና የሽኝት ፕሮግራም አድርገናል ። እጅግ ደስ የሚል ቀን አብረናቸው አሳልፈናል ። ተመልከቷቸው 👇
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
👉 ዛሬ በቂርቆስ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን የ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ እና የደረጃ 2 ተመራቂ ተማሪዎች የቅድመ አንደኛ ትምህርታቸውን ማጠናቀቃቸውን በማስመልከት እጅግ ደማቅ ዝግጅት አድርገን ከልጆቻችን ጋር ቆንጆ ቀን አሳልፈናል ። በተለይም ተመራቂ ተማሪዎች መምህራኖቻቸውን አመስግነዋል ። ይህን ማዬት ደግሞ ለእኛ እጅግ የሚያኮራን ነገር ነው ። 👉 በመጨረሻም የሁለተኛው መንፈቅ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና የፊታችን ሰኞ በ15 / 10 / 18 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እያሳወቅን ወላጆች በተሰጣችሁ ፕሮግራም መሰረት ልጆቻችሁን በማገዝ ለፈተና ብቁ ሆነው እንዲቀርቡ እንድታደርጉ መልክታችንን እናስተላልፋለን ። ፎቶዎች አሉን መልካም ምሽት
በነገው ዕለት በሁለቱም ቅርንጫፍ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤታችን የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የክልል አቀፍ የሚኒስትሪ ፈተና እንደሚወስዱ ይታወቃል ። በመሆኑም ተማሪዎች ነገ ጠዋት አንድ ሰዓት ላይ ዩኒፎርማችሁን ለብሳችሁ እንዲሁም ምሳ እቃችሁን ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን ። ከዚሁ ጋር ተያዬዞ ለፈተና የሚያስፈልጓችሁን እርሳስ ላጲስ ፣ መቅረጫ እንዲሁም የትምህርት ቤት መታወቂያ እና የመፈተኛ አይዲያችሁን እንዳትረሱ እናሳስባለን ። መልካም ምሽት
без подписи
ዛሬ በቂርቆስ ቅርንጫፍ የቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤታችን የዓመቱ የመጨረሻ የጥያቄና መልስ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ተከናውኗል ። ታዲያ ይህን / ይችን አሸናፊያችንን ለይተን ያወቅን ሲሆን ማን እንደሆነ ግን በዓመቱ የመማር ማስተማር ሥራችንን መዝጊያ በምናደርግበት ደማቅ መርሃግብር ላይ የምንገልፅላችሁ ይሆናል ። የተወዳዳሪዎችን ፎቶ ግን ከታች እንደሚከተለው እናጋራችኋለን 👇 መልካም ምሽት