- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 2
- Всего постов
- 21
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 2 339
- 1/48двое суток
- 2 680
- 1/72трое суток
- 2 891
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ሙሉ ሸዋ! @Shewapress
የ አማራ ወቅታዊ እጣ ፋንታ ይህ ሆኗል ይሄን ስርዓት የምንታገልበት ብዙ ምክንያት ነው ያለን። @showapress
በሰሜን ሸዋ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም በመሬት መንሸራተት አደጋ የ14 ሰዎች ሕይወት አለፈ በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው ታሪካዊው የጻድቃኔ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም በደረሰ ድንገተኛ የመሬት መንሸራተትና ርዕደ መሬት የ14 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፣ በ5 ሰዎች ላይ ደግሞ የከባድና ቀላል አካል ጉዳት መድረሱ ተገለጸ። አደጋው የተከሰተው ከክረምቱ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት ሲሆን፣ በወቅቱ * ለጸበል፣ * ለሱባኤና * ለንግስ ከአራቱም አቅጣጫዎች በገዳሙ ተገኝተው በነበሩ ምዕመናን ላይ ጉዳቱ መድረሱ ታውቋል። የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በአደጋው ስፍራ በአካል በመገኘት ለሕይወታቸው ያለፉት ጸሎተ ፍትሐት ያደረሱ ሲሆን፣ ለተጎዱትና ለተጨነቁት ምዕመናንም አባታዊ ቃለ በረከትና የማጽናኛ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል። ሀገረ ስብከቱ በደረሰው ድንገተኛ የመርዶ አደጋ ጥልቅና መሪር ኀዘን የተሰማው መሆኑን ገልጾ፣ ለሞቱት ዕረፍተ ነፍስን፣ ለተጎዱት ፈጣን ፈውስን እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው መጽናናትን ተመኝቷል። ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን በገዳሙ የተሰበሰቡትን ቅዱሳን አባቶችንና እናቶችን ጸሎት ተቀብሎ፣ ለሞቱት ወገኖቻችን በገነተ መንግሥቱ ዕረፍተ ነፍስን እንዲያድልልን፣ በሕክምና ላይ ለሚገኙት ተጎጂዎች አልጋቸውን አንስቶ ፈጣን የሕሊናና የሥጋ ፈውስን እንዲልክልን፣ እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸውና ለጠቅላላው የቤተክርስቲያን ልጆች የመንፈስ ቅዱስን መጽናናት እንዲያሳድርልን ከዕንባ ጋር በጸሎት እንለምናለን። ©ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት @Showapress
በዛሬው እለት በደብረብርሃን አጂፕ ሰፈር ነዋሪ የሆኑ ከአንድ ቤተሰብ አባላት አራት (4) ግለሰቦች በመኪና አደጋ በአሳዛኝ ሁኔታ ህይወታቸው እንዳለፈ ተሰምቷል። ከቁልቢ ገብርኤል ንግስ ወደ ቤታቸው እየተመለሱ በነበረበት ወቅት አሌልቱ ሲደርሱ የተሳፈሩበት ሚሊባስ ከሲኖ ጋር በመጋጨቱ ነው ይህ አሳዛኝ ልብ ሰባሪ ዜና የተሰማው። በዚህ አደጋ የሹፌሩ ባለቤት፣ አባቱ፣ እናቱ ህይወታቸው አልፏል። ለመላው ቤተሰቦቻቸው፣ለዘመዶቻቸው፣ ጎረቤቶቻቸው እንዲሁም ለሚያውቋቸው ወዳጆቻቸው በሙሉ ፈጣሪ መፅናናትን እንዲሰጣቸው እንመኛለን። ፈጣሪ ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ያኑርን። ከ እንደዚህ አይነት አደጋ ፈጣሪ ይሰውረን🙏 @Showapress
без подписи
без подписи
ሰሚ ያጣው መንዝ መንገድ ጣርማ በር ፣ሰፌድ ሜዳ ፣ሞላሌ ፣ወገሬ መንገድ እንድህ ተቆፍሮ ሀገር አልሚው የመንዝ ህዝብ እየተሰቃየ ነው ጩኸቱንም የሚሰማው አካል አጥቷል ። @shwapress
без подписи
♦እጅግ አሳዛኝ ! በከተማችን አዲስ አበባ የተፈጸመው ይህ ዘግናኝ እና ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እጅግ አሳዛኝ ነው ። የ2026 የ«ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ» አሸናፊ እና ሞደል ሩት ይርጋለም ታላቅ እህት ወጣት ቅድስት ይርጋለም፣ በቤተል አካባቢ ከቤቷ አቅራቢያ በአጋቾች ከተወሰደች በኋላ በጭካኔ ህይወቷ ማለፉን ተነግሯል ። አጋቾቹ የ2 ሚሊዮን ብር ቢጠይቁም፣ ምንም ዓይነት ርህራሄ በሌለው ሁኔታ የዚችን ንጹህ ወጣት ህይወት ቀጥፈዋታል። የሰው ልጅ ህይወት እንደ ቅጠል የሚረግፍበት እና ሰው በገዛ ሀገሩና በገዛ ሰፈራው ሰላም የሚያጡበት ይህ አይነት በደል በእጅጉ ያሳዝናል ። @Showapress
አሁን ላይ የገጠመን ትግል እንድህ ያለ ነው። @showapress
без подписи
без подписи
без подписи
የብልፅግና አገዛዝ በዛሬው እለት በደቡብ ወሎ ዞን ፣ መካነሰላም (ቦረና ወረዳ )፣ አባይ በረሀ ውስጥ በምትገኘው ቅድስት አርሴማ ገዳም ላይ በፈፀመው አሰቃቂ የድሮን ጥቃት 8 መነኮሳት ወዲያውኑ ሲሞቱ 10 በሚሆኑት ላይ ደግሞ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሷል:: ከንፁሃን ሞት በተጨማሪ በገዳሙ የሚገኙ ታሪካዊ ቅርሶች መወደማቸውን መረጃዎች ተሰምተዋል። @showapresa
без подписи
«መንግሥት የሕዝቡን የኑሮ እውነታ በቁጥር ጨዋታ ከመሸፈን ይውጣ» ዶክተር ደሣለኝ ጫኔ ባለፉት አምስት ዓመታት የሕዝቡን የኑሮ ስቃይና የመንግሥትን መዋቅራዊ ድክመቶች በቅርበት ሲታዘቡ መቆየታቸውን የገለጹት የፓርላማ አባል ዶክተር ደሣለኝ ጫኔ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ መንግሥት ላይ ጠንከር ያሉ የትችትና የጥያቄ ጠይቀዋል። ስድስተኛው የፓርላማ ዘመን አምስተኛ ዓመት ማጠቃለያ የመንግሥት ሪፖርት በቀረበበት ወቅት ንግግር ያደረጉት የሕዝብ ተወካዩ፣ መንግሥት በተለያዩ አካባቢዎች የቀጠሉትን የሰላም እጦቶችና የፖለቲካ ምኅዳሩን መጥበብ ችላ በማለት፣ በኢኮኖሚ ስኬት ስም የቁጥር ጨዋታዎችን እያቀረበ ሕዝብን እያደናገረ ነው ሲሉ ወቅሰዋል። በተለይም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ የመጣው ሰማይ የነካ የዋጋ ግሽበት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን የመግዛት አቅም ያሳጣና መካከለኛውን የኅብረተሰብ መደብ ያጠፋ ስውር ረሃብ መውለዱን ገልጸዋል። በትምህርት ዘርፍ በኩል የታየውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የ92 በመቶ መውደቅ ሲሉ የገለጹት ዶክተር ደሣለኝ፣ ይህ አሳሳቢ ውጤት የመንግሥትን የትምህርት ሥርዓት መዋቅራዊ ኪሳራ የሚያሳይ በመሆኑ ትምህርት ሚኒስትሩ ሊጠየቁበት ይገባል ብለዋል። አያይዘውም በሀገሪቱ ሰብአዊ ቀውስ እያለ የመረጃ ማጥራት በሚል ሰበብ የእርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ወደ 2.3 ሚሊዮን ዝቅ ተደርጎ መቅረቡ እውነታውን የማይወክል የፖለቲካ ቁጥር ማሳመሪያ ነው ሲሉ ነቅፈዋል። ተወካዩ እንደ መፍትሔ ያቀረቡት መንግሥት ትኩረቱን ከኮሪደር ልማትና ከሪዞርቶች ግንባታ በመቀነስ፣ ወደ መሠረታዊ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ ወደ ማኅበራዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራሞችና ሁሉንም የታጠቁ ኃይሎች ያካተተ እውነተኛ ብሔራዊ የፖለቲካ ድርድር ላይ እንዲያደርግ ነው። በመጨረሻም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ችግሮችን በኃይል ከመፍታት ወጥተው፣ ሕዝቡ በአዲሱ የ2019 ዓመተ ምህረት በተግባር ሊያየው የሚችለውን ግልጽ የሰላም የጊዜ ሰሌዳና ቁርጠኝነት እንዲያብራሩ በይፋ ጠይቀዋል። @showapress
በአዘቦቱ፥ መንበር ከካህኑ በቀር ምዕመን ቀርቶ ዲያቆንም መንካት አይፈቀድለትም። ክፉ ቀን ሲመጣ ግን የማይሆነውም ይሆናል። ይህ ግፉዕ ማኅበረ ምዕመን ቤቱን፣ ከብቱን፣ ግማሽ ሕይወቱን የኋሊት ጥሏል፣ ተነጥቋል። መንበሩን፣ ደመ ክርስቶስ የሚሠዋበትን ግን በክፉ ቀን እንኳ አልዘነጋም። ልቤን የደቃኝ ምስል። ወገኖቻችሁ ድኩማን ብንሆንም፥ ይህን መታመናችሁን መገፋታችሁን ከሰማይ የሚያይ አምላክ አላችሁ።…
በአዘቦቱ፥ መንበር ከካህኑ በቀር ምዕመን ቀርቶ ዲያቆንም መንካት አይፈቀድለትም። ክፉ ቀን ሲመጣ ግን የማይሆነውም ይሆናል። ይህ ግፉዕ ማኅበረ ምዕመን ቤቱን፣ ከብቱን፣ ግማሽ ሕይወቱን የኋሊት ጥሏል፣ ተነጥቋል። መንበሩን፣ ደመ ክርስቶስ የሚሠዋበትን ግን በክፉ ቀን እንኳ አልዘነጋም። ልቤን የደቃኝ ምስል። ወገኖቻችሁ ድኩማን ብንሆንም፥ ይህን መታመናችሁን መገፋታችሁን ከሰማይ የሚያይ አምላክ አላችሁ። @Showapress
በኢትዮጵያ በአማራ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት ወንጀልና በመጪው ግንቦት ወር የታቀደውን የይስሙላ ምርጫ ለመቃወም፣ በተለያዩ የአውሮፓ ዋና ከተሞች ታላላቅ የሕዝብ ተቃውሞ ሰልፎች ይካሄዳሉ። ከስቶክሆልም እስከ ብራሰልስ፣ ከለንደን እስከ ሮም የተጠራው ታላቅ ተቃውሞ፣ በአማራ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የህልውና አደጋና የይስሙላ ምርጫውን ድራማ በመቃወም በዲፕሎማሲው መስክ አዲስ ምዕራፍ ለመክፈትና ለፍትሕ አብሮ ለመቆም የተሰነቀ የሕዝብ ንቅናቄ መሆኑ ታውቋል። ዝግጁ የዲያስፖራ ሠራዊት ...!
''ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እባክህ ከኢትዮጵያ አናት ላይ ውረድ"አርቲስት ተመስገን ገብረእግዚአብሔር'' ታዋቂው የሙዚቃ አርቲስት ተመስገን ገብረእግዚአብሔር (ተሙ) በሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ያለውን ጥልቅ ስጋት እና አስተያየት በማህበራዊ ሚዲያ በለቀቀው ተንቀሳቃሽ ምስል ይፋ አድርጓል። ድምፃዊው በንግግሩ አሁን ያለው የመንግስት አመራር መንገድ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን በመጥቀስ አስተዳደሩ ኃላፊነቱን እንዲያስረክብ ጠንከር ያለ ጥሪ አቅርቧል። አርቲስቱ በሀገሪቱ እየታየ ያለው ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ቀውስ ከግል ጥቅምና ከፖለቲካ ፍላጎት በላይ የሆነ የሰብአዊነት ጉዳይ መሆኑን ገልጿል። አሁን ያለው ገዥው መንግስት የአንድን ወገን ፍላጎት ብቻ የሚያስቀድም መሆኑን የጠቀሰው ድምፃዊው፣ እራሱም የዚህ ሂደት ተጠቂ እንደነበር አስታውሷል። በተለይም በህዝቦች መካከል እየተፈጠረ ያለው ክፍፍል ቀደምት አባቶች ካቆዩልን የአንድነት እና የመከባበር እሴት ጋር የሚቃረን መሆኑን በዝርዝር አስረድቷል። በተጨማሪም በህዝብ ስም የሚደረጉ የፖለቲካ ንግግሮች ትክክለኛውን የህዝብ ፍላጎት የማይወክሉ መሆናቸውን በመግለጽ፣ አመራሩ በሰላማዊ መንገድ ከስልጣን እንዲወርድ አሳስቧል። @showapress