ቤተ መጻሕፍት
Статистика"መጻሕፍት፡ ለሰው ልጅ መድኀኒት የታዘዘባቸው የማዘዣ ወረቀት መኾናቸዉን ተገንዝባችኊ አንቡቧቸው።" ('ርጢን' ገጽ ፲፫)፧፧፧፧ የ'ቤተ መጻሕፍቱ' ሊንክ https://t.me/betemetsihaf ለማንኛውም አስተያየት https://t.me/getnetfekadu
- Последний пост
- 5 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 27
- Тип
- открытый
- Язык
- am
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 583
- 1/48двое суток
- 668
- 1/72трое суток
- 720
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
без подписи
ከሰው ወገን ማንም እንደ እኔ ኀጢአት የሠራ በደለኛ የለም፤ እንደ አንተም ያለ መሐሪ ይቅር ባይ አምላክ አይኖርም፤ ፈጣሪዬ ክርስቶስ ሆይ፣ ዓለማትን ኹሉ የፈጠርህ ፈጣሪ እንደ መኾንህ መጠን፥ በኋለኛው ዘመን በዓለም ላይ ለመፍረድ በምትመጣበት ጊዜ፥ ከጎንህ በፈሰሰው ደም ኀጢአቴን እጠብልኝ! [{ መልክአ መድኀኔዓለም }]
#ወርኃዊ_ጸሎት እና #የገድለ_ቅዱሳን #ማሰሚያ_ቀን ዐርብ ሐምሌ ፳፬(24)/፳፻፲፰ ዓ.ም. በዚኹ ዕለት ተገኝተው በጸሎቱ ተሳታፊ ይኾኑ ዘንድ በአክብሮት ጠርተነዎታል መርሐ_ግብሩም፥ ከጠዋቱ 1:00 እስከ 10፡00 ሲኾን፥ ከ1፡00 - 6:00 #ጸሎት ይደረሳል፣ #ተኣምረ_ማርያም እና #ድርሳናት ይነበባሉ፤ ከ6:00 - 8:30 #ሥርዐተ_ቅዳሴ ከተካኼደ በኋላ ተመልሰን ወደ አዳራሽ በመመለስ ከ8:30 - 10:00 #ገድላት፣ #ሃይማኖተ_አበው፣ #ስንክሳር ይነበባል። በመጨረሻም ንፍሮ፣ የንፍሮ ውሃ እና ዳቦ ተስተናግደው የመርሐ ግብር ፍጻሜ ይኾናል። ከተቻልዎት #ሙሉውንቀን ካልተቻልዎትም በሚያመችዎት ሰዓት መካፈል ይችላሉ። 👉ሌሎችንም ይጋብዙ። ፨በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም፥ #የተምሮ_ማስተማር_ሰንበት ት/ቤት ፨
አኹን ስንት ሰዓት ነው?
ሰው ሆይ፦ እያንዳንዷን ድርጊትህን የሚመለከት፣ የሰማይ እና የምድር ንጉሥ እንዳለ ፈጽመህ አትርሳ፡፡ [ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ]
If you give all your love to God, you'll receive all of His in return, to pass on to other people. St. Paisios
የምትሰጠው ነገር ሲኖርህ ስጥ፤ ምንም ከሌለህ ግን ፍቅርን ስጥ። አባ ፓይስዮስ
``አልጠቅምም አትበል`` ስለ ሌሎች መዳን ከማይጨነቅ ክርስቲያን በላይ ` ሰነፍ ሰው ` የለም፡፡ ወዳጄ 。 “እኔ ድኻ ነኝና ይህን ማድረግ አልችልም” የምትል አትኹን፤ ባለ ኹለት ዲናሯ ሴት ትወቅስሃለችና፡፡ 。 ዳግመኛም “ወርቅም ብርም የለኝም” ብሎ የተናገረ ጴጥሮስ ይወቅሰሃልና፡፡ 。"ምናምንቴ ነኝ" አትበል፤ እንዲህ ስትል ምናምንቴዎቹ ሐዋርያት እንዳይሰሙህ! 。"እኔ በሽተኛ ነኝ" አትበል፤ በሽተኛው ጢሞቴዎስ ይታዘብሃልና፡፡ ፈጽመህ 。 “እኔ ሌሎች ሰዎችን ወደ ክርስቶስ ማምጣት አይሆንልኝም” አትበል፡፡ 。በእውነት ክርስቲያን ከኾንክ፣ ይህን ከማድረግ ይልቅ፣ አለማድረጉ ይከብዳልና፡፡ 。እግዚአብሔር እንዲህ እንድትኾን አድርጎ ፈጥሮሃልና፣ ተፈጥሮህን መካድ አይቻልህም፡፡ 。ክርስቲያን በጨለማ ውስጥ ለሚኖሩ ወንድሞቹም ብርሃኑን ከሚከለክል ይልቅ፣ ፀሐይ ብርሃኗን ብትከለክል ይቀላልና። ስለዚህ አልጠቅምም አትበል፡፡ [ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ]
የሰው ልጅ ሆይ፣ ኀጢኣትህ ከሚያስከትልብህ መከራ ይልቅ፣ ኀጢኣት ስትሠራ የምታሳዝነውን ፈጣሪኽን አስብ፡፡ [ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ]
ሁሉንም ጸሎታችሁን ስላልመለሰ፣ እግዚአብሔርን የምታመሰግኑበት ቀን ይመጣል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ
✝️ ከክርስቶስ ፍቅር ✝️ ማን ይለየናል፤ . መከራ ነውን፥ . ሐዘን ነውን፥ . ስደት ነውን፥ . ረኀብ ነውን፥ . መራቆት ነውን፥ . ጭንቀት ነውን፥ . ሾተል ነውን፤ . [መታሰር ነውን]፤ … * መጽሐፍ እንዳለ {[(ስለ አንተ ዘወትር ይገድሉናል፤ እንደሚታረዱ በጎችም ኾነናል)]}፧ . ነገር ግን ሞትም ቢኾን፥ . ሕይወትም ቢኾን፥ . መላእክትም ቢኾኑ፥ . አለቆችም ቢኾኑ፥ . ያለውም ቢኾን፥ . የሚመጣውም ቢኾን፥ … * ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንደማይችል አምናለኊ፤ . ኀይልም ቢኾን፥ . ከፍታም ቢኾን፥ . ዝቅታም ቢኾን፥ . ሌላ ፍጥረትም ቢኾን፥ … * ከክርስቶስ ፍቅር ሊለየን የሚችል የለም።" ('የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት፤ ወደ ሮሜ ሰዎች፤ ም. ፰፥ ቊ. ፴፭ - ፴፱)
ጠዋት ከእንቅልፋችሁ ስትነሱ፣ በዚህ ቀን ለምታደርጉት ለእያንዳንዱ ነገር፣ ለእግዚአብሔር መልስ እንደምትሰጡ አስቡ:: አባ ሙሴ ጸሊም
"Give me Christian mothers and I will give you Saints to change the world," St. John Chrysostom
“Having children is a matter of nature; but raising them and educating them in the virtues is a matter of mind and will.” ~ St. John Chrysostom "ልጅ መውለድ የተፈጥሮ ጉዳይ ነው፤ ነገር ግን ልጆችን ማሳደግና በጎነትን ማስተማር የአእምሮ እና የፍላጎት ጉዳይ ነው።" ~ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ሌቦች ባዶ ቤትን ለመበርበር አይመጡም፤ ወርቅ እና ብር ወዳለበት ቤት እንጂ፡፡ ዲያብሎስም ልክ እንደዚህ ነው፤ ሊፈትናቸው የሚመጣው፣ መንፈሳዊ ሀብታትን ወዳከማቹት ነው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
без подписи
#ለመጸለይ_ሲደክምህ፣ ስንት ጊዜ ሳይደክምህ ኀጢአት እንደ ሠራህ አስብ🤔። [{#ተወዳጁ_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ}] https://t.me/betemetsihaf
... የቤተ ክርስቲያን ልጆች ኹላችኊ፣ . ብቻውን ኀጢአት የሌለበት #በቅዱስ_ደሙ የገዛችኊ ሆይ! ኑ፤ ተሰብሰቡ፤ . ሕማማቱን በዕንባ እናስብ፤ . በፍርሐት እና በጭንቀትም ኾነን "#መድኀኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ስለ_እኛ_መዳን_ብሎ_ሞተ" እያለን ለልቡናችን እንንገረው። . ልቡናችኹም ይደንግጥ፤ . ነፍሳችኹም ትንቀጥቀጥ፤ . ኹል ጊዜ የጌታችንን ሕማማት በማሰብ ማልቀስ፦ #ዕንባችኊ_የጣፈጠ፣ #ልቡናችኊ_የበራ_ይኾናልና፤ . ኹል ጊዜ ይኽነን እያሰባችኊ፣ ዕንባችኁን እያፈሰሳችኊ፣ ጌታ ስለ እናንተ ስለ ተቀበለው መከራ ምስጋና አቅርቡለት፤ . ምክንያቱም ይኽ ዕንባችኊ በምጽአቱ ቀን፣ #በመንበሩ_ፊት_መመኪያ እና #ሐሴት_ማድረጊያ_ይኾንላችኋልና። [ ድርሳነ ቅዱስ ኤፍሬም ቅጽ ፩፤ ትርጒም በዲ/ን መዝገቡ ከፍያለው፤ ገጽ ፪፻፷፫/263፤ ፳፻፲፪/2012 ዓ.ም.]
без подписи
без подписи