ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
СтатистикаThis channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz- ይህ ገጽ የሚንቀሳቀሰው በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አይደለም https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ “ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።” — 2ኛ ቆሮ 11፥28
- Последний пост
- 13:11
- Последнее чтение
- 12:59
- Постов за неделю
- 9
- Всего постов
- 34
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- Категория
- Видео
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 4 238
- 1/48двое суток
- 4 856
- 1/72трое суток
- 5 238
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
ቅዳሴ ማርያም ድንቅ ምሥጢር፣ ማራኪ ንባብ ያለው አኰቴት ነው። በ #ኤማሁስሥርዓተአምልኮ በአጠቃላይ ስለ ምሥጢረ ቅዳሴ በተለየ መልኩ ስለ ቅዳሴ ማርያም ሰፋ ያለ ውይይት ቀርቧል። አዳምጡት https://youtu.be/QB497IDgpDY?si=1MU3BzFPm9vkYu2i
видео или голосовое, без подписи
ተአምራት ክፍል 1 / መምህር ያረጋል አበጋዝ https://youtu.be/oFaG6yJaDhs
https://youtu.be/slGFzgBd-zE?si=Jfvin7vSv2pvXwrC
https://youtu.be/AHvh4kKRa1c?si=BnuhnK7iOuRzug9F
ራስህን በሐሰት አትውቀስ ራስን መውቀስ ትህትና አይደለምና ታላቁ ትህትና ሰዎች ሲወቅሱህ መታገስ ነው። #ቅዱስ_ሰራፕዮን
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሰባት በዚች ቀን እግዚአብሔር የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ከበረና ከፍ ከፍ ወዳለ ጻድቅ አ.ያቄም ላከው አምላክን የወለደች የእመቤታችን የድንግል ማርያምን ፅንስቷንና ልደቷን በእርሷም ለዓለሙ ሁሉ ድኅነትና ተድላ ደስታ እንደሚሆን ነገረው ። ይህ ጻድቅም ሰው ኢያቄምና የከበረች ሚስቱ ሐና ልጅ ሳይወልዱ ሸመገሉ የከበረች ሐና መካን ሁናለችና ስለዚህም እጅግ ያዝኑ ነበር የእስራኤል ልጆች ልጅ ያልወለደውን ከእግዚአብሔር በረከትን ያጣ ነው እያሉ ያቃልሉት ነበርና ። እነርሱም ልጅን ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ዘወትር ፈጽሞ ይለምኑ ነበር ። ከዚህም በኋላ ወንድ ልጅን ወይም ሴት ልጅን ቢወልዱ ለእግዚአብሔር ቤት አገልጋይ ሊያደርጉ ስለትን ተሳሉ ። የከበረ ኢያቄምም በተራራ ላይ ሳለ ሲጸልይና ሲማልድ እነሆ በላዩ እንቅልፍ እንቅልፍ ብሎት አሸለበ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የተላከ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ተገለጸለት እንዲህም አለው ሚስትህ ሐና ትፀንሳለች ዓለሙ ሁሉ ደስ የሚሰኝባትን የብዙዎችም ዐይነ ልቡ ናቸው በእርሷ የሚበራላችውን በእርሷም ድኅነት የሚሆንባትን ሴት ልጅን ትወልድልሃለች በነቃ ጊዜም ወደ ቤቱ ሒዶ ለሚስቱ ለቅድስት ሐና ነገራት ራእይዋን እውነት እንደሆነች አመኑዋት ከዚህም በኋላ ነሐሴ ሰባት በዚች ቀን የከበረች ሐና ፀነሰች ለዓለም ሁሉ መመኪያ የሆነች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የአምላክ እናት እመቤታችንን ማርያምን ወለደቻት ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ኢያቄምና ሐና ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ።
On Fasting and Feasts By:Saint Basil the Great In this new collection of sermon translations-Basil addresses such issues as drunkenness, hesitations over baptism, community benefits of fasting, how to be thankful when facing loss and disaster, and the mystery of the incarnation. Also included are three sermons on local martyrs Julitta, Mamas, and Barlaam. This small volume of elegant translations will be a vital and valued resource for anyone interested in religion and the body, early Christian spiritual disciplines, and their application to the Church today.
видео или голосовое, без подписи
የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዋና የትምህርት ምንጭ የሆነው የአብነት ትምህርት ቤት በየአመቱ በሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎችን በመምህርነት አስመርቆ ያወጣል። እነዚህ ተማሪዎች የሚማሩት ትምህርትና ከሦስት እና ከአራት መቶ አመት በፊት የነበሩት ሊቃውንት የተማሩበት መንገድም ሆነ የተማሩት ትምህርት ይዘት ተመሳሳይ ነው። ብዙዎች ይህን ትውፊትን እንደማስጠበቅ አድርገው ይረዱታል። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ቤተክርስቲያን አድርጎ ያቆያት ዋና ቁምነገርም ይህ እንደሆነ ያስባሉ። ወደፊትም ቤተክርስቲያኒቱን ለመጠበቅ የትምህርት መንገዳችንም ሆነ ትምህርታችን መነካት የለበትም ይላሉ። ነገር ግን እዚህ ጋር መሠረታዊ የሆነ ጥያቄ ይነሳል። ከአብነት ትምህርት ቤት የሚወጡ መምህራን ከዘመኑ ጋር መራመድና ዘመኑ የሚሠራበትን ፍልስፍና ያለማወቃቸው ነገር ነው። የማያውቁትን ሕመም ደግሞ ማዳን እንደማይቻል ግልጽ ነው። የመምህራን ዋና ተልእኮ ደግሞ የዘመኑን መንፈስ ማንበብና መፈወስ መቻል እስከሆነ ድረስ ትምህርታችንም ሆነ የትምህርት መንገዳችን ላይ ጥያቄ ማንሳታችን የግድ ይሆናል። ከየኔታ ኃይለማርያም ጋር ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ደፈር ብለን ለመወያየት ሞክረናል። መልካም ቆይታ። https://youtu.be/84qnUpLiPeg?si=sA22oVkx2kT9njo_
https://youtu.be/Fptcm13WAkQ?si=NJypRn_ctRB_hQaj
видео или голосовое, без подписи
ፍልሰታ ምን ማለት ነው? ፍልሰታ ማለት ‹ፈለሰ – ተሰደደ› ከሚለው ግሥ የወጣ ነው፡፡ ‹ፍልሰት› ማለት ደግሞ የተለያየ ትርጕም ቢሰጠውም ‹ፍልሰታ ለማርያም› ተብሎ ሲገለጽ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ወደ ማያልፈው ዓለም ከመቃብር የወጣችበት (የተነሣችበት) ቀን ማለት ነው፡፡ ወይም ደግሞ ከሥጋዊው ዓለም ወደ መንፈሳዊው ዓለም የተሸጋገረችበት ማለት ነው፡፡›› 'ፍልሰታ ለማርያም' የሚለው የግእዝ ቃል ሲኾን ‹ፍልሰታ› ማለት ደግሞ ‹ፈለሰ› ከሚል ግሥ የተገኘ ነው፡፡ ‹ፍልሰት› ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መሔድን (መፍለስን) ያመለክታል፡፡ እመቤታችን ካረፈች በኋላ የሥጋዋን መፍለስ አስመልክቶ ሐዋርያት የእመቤታችን ሥጋ የት እንደ ተቀበረ አላወቁም ነበርና እግዚአብሔር የእመቤታችንን ሥጋ እንዲገልጥላቸው የጾሙት ጾም ነው፡፡ ሐዋርያት ኹለት ሱባዔ ጾመው የእመቤታችንን ሥጋዋን ሰጥቷቸው ትንሣኤዋንና ዕርገቷን በማየት በረከት ያገኙበት ጾም ነው፡፡ ስለኾነም ምእመናን ፍልሰታ ለማርያምን ከልጅ እስከ አዋቂው በጾም በጸሎትና በመቍረብ በጋራ በፍቅር፣ በሰላም ያሳልፉታል፡፡›› ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን እንዲጠብቃት ከተደረገ በኋላ ሐዋርያት ‹‹የእመቤታችን ነገር እንዴት ነው?›› ብለው በጠየቁት ጊዜ ‹‹እመቤታችንማ በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር ናት›› ብሎ ነገራቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ሐዋርያት እመቤታችን ከመቃብር መነሣቷንና ማረጓን ማየት አለብን፤ እንዴት ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ እንቀራለን ብለው በመንፈሳዊ ቅናት በመነሣሣት ነሐሴ አንድ ቀን በዕለተ ሰኞ ሁለት ሰባት ሱባዔ ያዙ፡፡ በዐሥራ አራተኛው ቀን ጌታችን የእመቤታችንን ሥጋ አንሥቶ ሰጣቸውና በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡ እመቤታችን በ፷፬ ዓመቷ ጥር ፳፩ ቀን ዐርፋ ነሐሴ ፲፬ ቀን ተቀብራለች፡፡ ይኹንና ሐዋርያት ቢቀብሯትም ትንሣኤዋንና ዕርገቷን አላዩም ነበር፡፡ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያየው ሲቀብሯት ያላየው ሐዋርያው ቶማስ ነው፡፡ ቶማስ እንዲያስተምር ሕንድ አገር ዕጣ ደርሶት አስተምሮ በደመና ሲመለስ ነሐሴ ፲፮ ቀን እመቤታችን ስታርግ ሕዋ ላይ ተገናኙ። ምእመናን ጾመ ፍልሰታ የእመቤታችን ዕረፍት፣ ትንሣኤና ዕርገቷ የሚዘከርበት ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ የኾነ ጾም ነው፡፡ በየዓመቱ ሕፃን አዋቂው ሳይቀር የእመቤታችን ፍቅር አድሮባቸው ጾሙን ይጾማሉ፣ ያስቀድሳሉ፤ ይቈርባሉ፡፡ የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? የፍልሰታን ጾም ከሌሎቹ አጽዋማት ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው? ኢትዮጵያ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዐሥራት አገር በመኾኗ እና ሕዝበ ክርስቲያኑ ለእመቤታችን ልዩ ፍቅር ስላላቸው መሬት ላይ እየተኙ፣ ጥሬ እየበሉ በሰላም በፍቅር ይጾሙታል፡፡ ምእመናን ፍልሰታን ከሌሎች አጽዋማት በተለየ መልኩ መሬት ላይ እየተኙ ይጾሙታል፡፡ ይህ ደግሞ የእመቤታችን ፍቅር ስለሳባቸው ነው፤፡፡ ይቆየን ምንጭ፦ ማኅበረ ቅዱሳን
https://youtu.be/52Fy7qNZAuU?si=mf0_Vi6TyYQIiE4S
ብሒለ አበው ዲያብሎስ ዝናሩን አራገፈ ቀስቱን ጨረሰ ቤተ ክርስቲያንን ግን አልጎዳትም:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሁሉም ከአንተ ነው ሁሉም በአንተ ነው አንተም በሁሉ አለህ በገናናነትህ ከልዑላን ይልቅ ልዑል ነህ፡: ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ለበሽተኛው የሚጠቅመውን የሚያውቅ ሐኪሙ እንጂ በሽተኛው አይደለም፡፡ ሊቁ አውግስጢኖስ በእግዚአብሔር ቸርነት የምትሠራ ሥራ ስትጀመር ጥቂት ናት፤ ኃላ ግን በሥራ ትሰፋለች፡፡ አረጋዊ መንፈሳዊ የእኔን ባርነት አንተ አትፈልገውም እኔ ግን የአንተን ጌትነት እሻዋለሁ፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ አንተ ሰማይን ለእኔ እንደ ጣሪያ አዘጋጅተህልኛል እራመድባትም ዘንድ ምድርን አደላድለህልኛል፡፡ አንተ ባሕሩን አርግተህልኛል አውሬውንም ለማዳ አድርገህ ልኛል፡፡ ክቡርና ድንቅ ከሆኑት ሥራዎችህ አንዳችም ያስቀረህብኝ ነገር የለም፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ለቤተ ክርስቲያን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ አቤቱ ይህን ማድረግህ እርስዋን በከበረ ደምህ ትቀድሳት ዘንድ ነው፡፡ ለእርስዋ ሲል ታሥሮ መጎተት የቻለ፣ የበደለ ውም በደል ሳይኖር ርኩስ ምራቅን ሲተፋበት ታግሶ አምላክ በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ ቅዱስ ቄርሎስ
https://youtu.be/ECF3db9TYEE?si=-380uMmsOwT3cRPG