Injibara University
Статистика- Последний пост
- 10 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 25
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- Категория
- Образование
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 5 457
- 1/48двое суток
- 6 253
- 1/72трое суток
- 6 744
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት መዘራት ተጀመረ። ========================== ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የ2018/19 የመኸር እርሻ የስንዴ ምርጥ ዘር ብዜት መዘራት ተጀምሯል። በዘር ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊና የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲዉ ከሚሰጣቸው የማህበረሰብ አገልግሎት ሥራዎች አንዱ ለምግብነትና ለዘር ብዜት አገልግሎት የሚውል የዳቦ ስንዴ ምርት አምርቶ ለአርሶ አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ማቅረብ እንደሆነ ገልፀው በዘንድሮ የ2018/19 የመኸር እርሻ ሰብልም ደንደኣ እና ሰከላ የተባሉ ሁለት አይነት የስንዴ ምርጥ ዘር ዝርያዎችን በግቢ ውስጥ በሚገኘው 20 ሄክታር የእርሻ መሬት ላይ ዘር የመዝራት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ኮሌጅ ዲን የሆኑት ሀብታሙ አድማስ (ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የስንዴ ምርጥ ዘር መዘራት ከጀመረ ሁለት ሶስት አመታትን ያስቆጠረ መሆኑን አስታውሰው በዘንድሮው የመኸር የስንዴ ዘር የማስጀመር መርሃ ግብር ዩኒቨርሲቲው በግቢው ወስጥ ከግንባታ ሳይት ነፃ የሆኑ የእርሻ መሬቶችን በሳይንሳዊ የአጠቃቀም ዘዴ የአፈር አሲዲማነትን መቋቋም የሚችሉ የስንዴ ዝርያዎችን በ20 ሄክታር መሬት ላይ በመዘራትና ምርምሮችን በማካሄድ በሚቀጥለው ዓመት የተሻለ ምርት አምርቶ ለአርሶ-አደሩ ለማሰራጨት ሰፊ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል። የዩኒቨርሲቲው የስንዴና ገብስ ምርጥ ዘር ብዜት ተመራማሪና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ የሆኑት አቸነፍ ጥጋቡ (ዶ/ር ) እንደገለፁት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ባለፈ በርካታ ሀላፊነቶችን እየተወጣ የሚገኝ ተቋም መሆኑን ጠቅሰው በ2018/19 የምርት ዘመን የተሻሉ ግብዓቶችን ተጠቅሞ ልዩ ልዩ ምርምሮችን በማካሄድ ጥራቱን የጠበቀ በቂ የዳቦ ስንዴ ምርጥ ዘር አምርቶ ለአርሶ-አደሩ በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ ለማድረግ ፕሮጀክቱ ትኩረት አድርጎ አየሰራ ነው ብለዋል። ፕሮግራሙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የግብርና ኮሌጅ ተመራማሪዎችና የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች በተገኙበት ተጀምሯል። ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተጠቀም!
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
ለሀገር በቀል ዕውቀት(Indigenous Knowledge) ተመራማሪዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ፡፡ ========================== ነሃሴ 2/2018 ዓ.ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ሀገር በቀል ዕውቀት ዙሪያ ምርምር እየሰሩ ለሚገኙ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በአይነታዊ መረጃ ትንተና (Qualitative Data Analysis) ዙሪያ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ እና የምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር) እንደተናገሩት ዩኒቨርቲው ከትምህርት ሚኒስተር በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ በሀገር በቀል ዕውቀት ያተኮሩ ምርምሮችን በመስራት እና ሰነድ በማዘጋጀት ላይ መሆኑን ጠቅሰው የዛሬው ስልጠናም በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ምርምር እየሰሩ የሚገኙ ተመራማሪዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ስልጠናው ተመራማሪዎች ከአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር የተለያዩ አካባቢዎች የሰበሰቡትን የሀገር በቀል ዕውቀት መረጃ የተለያዩ ሶፍትዌሮችን በመጠቀም ለመተንተን እና ሳይንሳዊ የሆነ የምርምር ሰነድ እንዲያዘጋጁ የሚያስችል መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ክንዴ ሰልጣኞች በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት እና ልምድ በአግባቡ ተጠቅመው ምርምሮቻቸውን እንዲያከናውኑ አሳስበዋል ፡፡ የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምር፣ ህትመት እና ሥነ-ምግባር ስርጸት ዳይሬክተር ተሰራ ቢተው (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርቲው በሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ሰፊ ፕሮጀክት ቀርጾ እየሠራ እንደሚገኝ ገልፀው ለተመራማሪዎችም የተለያዩ ምሁራንን በመጋበዝ በአይነታዊ ጥናት (Qualitative research) MAXQDA software እና ሌሎች የመረጃ ትንንተና ዘዴዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ ስልጠናው በዋናነት መረጃ ትንተና (Qualitative Data Analysis) ማለትም Foundation, መረጃ ማዘጋጀት (Data Preparation) Coding, Codebook, Themes ,Interpretation reporting ላይ በማተኮር የሀገር በቀል ዕውቀት ላይ ለሚሰሩ 16 ተመራማሪዎች ለሁለት ቀናት የተሰጠ ሲሆን ስልጠናውን የሰጡት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢ ጤና (Public Health) መምህር የሆኑት ህይወት ተስፋ ናቸው፡፡ ያለህን እምቅ አቅም ለይተህ ተቀም!
без подписи
без подписи