አንድ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
Статистикаበዚህ ቻናል አማራ ስለተጋረጠበት የህልውና አደጋ እና ስለመፍትሔወቹ እናወራለን
- Последний пост
- 11 авг.
- Последнее чтение
- 14 авг.
- Постов за неделю
- 7
- Всего постов
- 22
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 95
- 1/48двое суток
- 108
- 1/72трое суток
- 117
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
''አስ-ከ-ሬን ማንሳት ተከልክለን አውሬ እየበላው ነው!''😥 ለአመታት የዘለቀው የአበሽጌ ወረዳ ሰቆቃ አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል። የኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ በሆነችውና በጉራጌ ዞን ስር በምትተዳደረው አበሽጌ ወረዳ የአማራ ወጣቶች በማንነታቸው ብቻ ''የፋ-ኖ ደጋፊ ናችሁ'' ተብለው እየተፈረጁ በመንግሥት የፀጥታ ሀይሎች እየ-ተገ-ደሉ እንደሚገኙ ከስፍራው በምስል የተደገፈ መረጃ ደርሶናል። በቀን 24/11/18 ዓ.ም ብቻ 3 ወጣቶች አገና ከተማ ላይ ''ፋ-ኖ ናችሁ'' በሚል ፍረጃ በፀጥታ ሀይሎች ከተያዙ በኃላ በ25/11/2018 ዓ.ም አበሽጌ ወረዳ ''ናቻቁሊት'' ከሚባል ቀበሌ ወስደው ረሽ-ነዋ-ቸ-ዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች '' አንስተን ለመቅበር ስንሔድ አስ-ከ-ሬን እንዳናነሳ በፀጥታ ሀይሎች ተከልክለናል'' ሲሉ ገልፀዋል። ለቀናት በድናቸው የፊጥኝ እንደታሰረና የራስ ቅላቸ-ው በጥይት ፈ-ራ-ርሶ የወደቁትን ወጣቶችን አሳዛኝ ምስልም እንደምትመለከቱት አጋርተውናል። በአበሸጌ ወረዳ በአካባቢው ለዘመናት የኖሩና በሰፋፊ የሜካናይዝድ ግብርና ስራ ላይ የተሰማሩ አማራዎች በብዛት የሚኖሩ ሲሆን ላለፉት አመታት ያለእረፍት እያስተናገዱት ባለው አገዛዛዊ ጥቃት እጅግ በርካቶች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል ፣ በመቶዎች የሚቆጠሩና በስም የሚታወቁ አደፍርስ አሰፋን መሰል ባለሀብቶች ጭምር ለአመታት ያለፍትህ ታስረው ይገኛሉ ፣ ሀብት ንብረታቸው የተወረሰባቸው በርካቶች ናቸው ፣ የተገደሉና አካላቸውን ያጡትም ከፍተኛ ቁጥር አላቸው። አማራጭ አጥተው በስጋት ውስጥ እዚያው የተቀመጡትን ደግሞ ''የፋኖ ደጋፊዎች ናችሁ'' እያሉ በአደባባይ እየ-ረሸ-ኗቸ-ው ይገኛሉ። ''እኛ ኢትዮጵያዊ አይደለንም ወይ ? ወደማን እንጩህ ? ወዴትስ እንሂድ ?'' የሚሉት ነዋሪዎቹ ድምፃችንን እንድናሰማላቸው ጠይቀዋል!
• እንደመስሳቸዋለን እያለ ነው። "…ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በደቡብ ጎንደር ድልኳዜ በተባለ ሥፍራ ራሳቸውን በራሳቸው መርጠው የዐበማለት መግለጫ ያወጡትና በወቅቱም በነበረው የአመራር ምደባ የዕዙ ምክትል ወታራዊ አዛዥ ለአስተዳደር ጉዳዮች ተብሎ የተሾመው በምስሉ ላይ የምታዩት አ ርበኛ ሸጋ ጌታቸውየተባለው ባለሥልጣን እነ አርበኛ ባዬ ቀናው፣ እነ አርበኛ ሳሚ ባለድል ወዘተረፈ በሦስት ቀን እጃቸውን ሰጥተው ወደ ድርጅታችን ካልገቡ እንደመስሳቸዋለን በማለት እሱ መጻፍ ባይችልም በስሙ በተከፈተው የፌስቡክ ገፁ ላይ የእንግጠም ክተት ይለይልን ዐዋጅ ማወጁ ተመልክቷል። "…ሰሞኑን በነበረው የአመራሮች የሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ የጄነራል አሳምነው ጽጌን ፎቶ በመሸላለማቸው ከእነ አያሌው መንበር "እንዴት የገዳይን ፎቶ ትሸላለማላችሁ?" በማለት ክፉኛ ተቃውሞ ከስኳዱ የተነሣበት ይሄው የድልኳዜ የጠቅላይ ግዛቱ ቡድን ከዚህ ቀደም በኢትዮ 251 ሚዲያ በአቶ ሙላት አድኖ በኩል የሞት ዐዋጅ አውጆበት ጄነራል ውባንተን የገደለው ቡድን አሁን ደግሞ ከሞት የተረፈውን የውባንተን ምክትል እና የውባንተ ወታደራዊ አዛዥ የነበረውን እነ አርበኛ ሳሙኤል ባለድልን በሦስት ቀን ገብሩ፣ አለበለዚያ የውባንተ አባተ ዕጣ ፈንታ ነው የሚደርስባችሁ ብሏል። "…በዚህ ዓይነት እነ አርበኛ ሳሚ ፣ እነ ባዬ ቀናው ጉዳቸው ፈላ ማለት ነው። ከወያኔ ጋር ጦርነት ሳይጀመር ወያኔ የመደበችው የበረከት ስምዖን የቅርብ ሰው የሆነውን ዮሐንስ ንጉሡ ሙጨን መሪ አድርጎ የመረጠው የስኳድ ቡድን በጎንደር ዐማሮች ላይ እዘምታለሁ እያለ ነው። • እናንተስ ምን ትላላችሁ ? እስቲ ሐሳብ ስጡበት።
ሸዋ የአገር ካስማ
ሰላም ቤተሰቦች ይህንን የfb አካውንት ተከተሉ ከአማራ ፋኖ ጋር በተያያዘ ብቻ ወቅታዊ መረጃወችን እንለቃለን https://www.facebook.com/AFNFinshwa
በተጨማሪ ደግሞ ሸዋ በወርዱና በቁመቱ ልክ እስካልተወከለ ድረስ። ወንጀለኛ የፋኖ አመራሮች ለምሳሌ መከታው፣እስክንድር ፣አስረስ፣ጌታ..... በሕግ እስካልተጠየቁ ድረስ በሸዋ በእስክንድር አቀጥተኛ ትእዛዝ እና በመከታው አሰፈጻሚነቴ የታሰሩ እንቁ የሸዋ ፋኖዎች እንደ እነ ልመንል ሻውል ዳዊት ቀጸላ እና ሌሎች በርካታ የግፍ እስረኞች እስካልተፈቱ ድረስ ። አዲሱን ድርጅት ለመተቸት እና ምላሽ እስከሚገኝ በአመክንዮ ለመጠየቅ እንገደዳለን
без подписи
በአማራ ክልል ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ስብሰባ ላይ የነበሩ 36 የመንግስት ሚሊሻዎች በድሮን ተገደሉ። በአካባቢው የሚገኙ የመከላከያ አዛዦች ጥቃቱ የተፈጸመው በስህተት መሆኑን ተናግረዋል ። ቢቢሲ ነው የዘገበው
በአፋህድ የብልጽግና ኤጀንት የነበረው ማስረሻ ሰጤ ወደመጣበት ተመልሷል ለብልጽግና እጅ መስጠቱ ተረጋግጧል መልካም መቀላቀል
ዛሬ ህዳር 15/2018 ዓ.ም ማህበራዊ ሚዲያው ላይ በሰፊው አጀንዳ ሆኖ የዋለውን እጅግ ኢ ሰብዓዊ የሆነ ድርጊት አስመልክቶ ህዝብ ማወቅ ያለበት እውነታ! ፋሽስቱ አገዛዝ ብልፅግና በሆድ እደር አክቲቪስቶቹ እና በሚዲያ ሚሊሻዎቹ በኩል አንድ እጅግ አሰቃቂ ኢ ሰብዓዊ ድርጊት የተፈፀመበት ድርጊቱንም ፋኖ አደረገው በሚል ተንቀሳቃሽ ምስል አሰራጭተዋል:: ነገሩ እንዲህ ነው ድርጊቱን የፈፀመው ግለሰብ በፋኖነት ወረኢሉ ዙሪያ ሲንቀሳቀስ የነበረና ከአገዛዙ ተልዕኮ ተሰጥቶት በዘረፍና ሌሎች ተግባሮች ፋኖን ከህዝብ ለመነጠል ሲሰራ የነበረ በኋላም ምኒልክ ዕዝ አደረጃጀቱን በማጠናከር መሰል ፋኖ መሳዮችን ሲያሳድድ እርምጃ ይወሰድብኛል በሚል ህዳር 3/2018 ዓ.ም (November 12) ወረኢሉ ላይ ወደ ብልፅግና እጅ ሰጥቶ ገብቷል:: ለዚህም ተጨባጭ ማስረጃዎችን ከስር አጋርቻለሁ! ድርጊቱን የፈፀመው ግለሰብ በተጠቀሰው ቀን ወደ ብልፅግና የገባ ሲሆን ባገዛዙ በኩል ግለሰቡ ይህንን ድርጊት እንዲፈፅም በማድረግና በኋላም ፋኖ ፈፀመው በማለት ተንቀሳቃሽ ምስሉን ባወጡት በሰዓታት ውስጥ ወንጀለኛው በመንግስታችን በቁጥጥር ስር ውሏል በሚል በሚዲያ ሚሊሻዎቻቸው በኩል ዘገባ ሰርተዋል:: ከዚህ ጋር ተያይዞም ይሄ ፍፁም ኢ ሰብዓዊ የሆነ ድርጊት በአገዛዙ የተቀነባበረ ሴራ ዛሬ ላይ እንዴት ሊሰራ ቻለ? ለምንስ ተፈለገ? የሚለው ጥያቄ ህዝባችን ምላሽ ሊያገኝለት የሚገባ ጥያቄ ነው! ፋሽስቱ የብልፅግና አገዛዝ 2010 እና 2011 ዓ.ም በአማራ ህዝብ ላይ የፈፀማቸው ግፎችና ዘር ማጥፋቶች እስካለንበት ጊዜም የቀጠለ ቢሆንም ሰሞኑን ደግሞ በተለየ ሁኔታ በተለያዩ የሃገሪቱ ክልሎች እና በክልሉ እንደ አዲስ በሰፊው እየተፈፀመ ይገኛል:: አስገድዶ መድፈር እድሜ ሳይለኝ ባለትዳሮችና ነፍሰ ጡሮችን ጨምሮ እየተፈፀመ ሲሆን የንፁሃን ጅምላ ጭፍጨፋውም በሰፊው ተጠናክሮ ቀጥሏል:: ታዲያ ይሄ ብልፅግና መር የአማራ ህዝብ ግፍና በደል እንዲሁም ዘር ማጥፋት የአለም አቀፉን ማህበረሰብ ዝምታ የሰበረና በአለም አቀፉ ሚዲያ ቢቢሲ (BBC) ጭምር ዶክመንታሪ የተሰራበትና ሽፋን ያገኘበት ሁኔታ ተፈጥሯል:: በዚህ የተደናገጠውና በአማራ ህዝብ ላይ እየፈፀመው ያለው ዘር ማጥፋት የተጋለጠበት ብሎም አጀንዳ የሆነበት አገዛዙ አጀንዳውን መቀልበስና አድበስብሶ ማስቀረት ብሎም አጀንዳ መስጠት በማሰቡ የተሴረ ሴራና እጅግ ዘግናኝ ኢ ሰብዓዊ ድርጊት መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ ብሎም አለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲያውቅልን እንፈልጋለን! አበበ ፈንታው
без подписи
ናትናኤል እና አያሌው መንበረ
без подписи
без подписи
без подписи