S H E K A Y I N A H
Статистикаይህ #የሸካይና ፔጅ ነው የዚህ አገልግሎት አላማ #ትውልዱን ወደ ተገለጠው የእግዚአብሔር ክብር እለት ተዕለት እንድትጠጋ ማገዝ ነው:: ይህ ቻናል የተከፈተው የእግዚአብሔርን_ክብር ለተጠሙ ተሀድሶ ለሚሹ አማኞች ነው። @Shekayinaah @Shekayina_bot
- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 2
- Всего постов
- 30
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 141
- 1/48двое суток
- 161
- 1/72трое суток
- 174
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
የሐዋርያት ሥራ 3:6 "....በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ” አለው።" 📌በዚህ ክፍል በሐዋሪያቱ ላይ የእግዚአብሔር የፀጋ ስጦታ ሲገለጥ እንመለከታለን። ይህም ለምስክርነት ነው። 📍"የፀጋ ስጦታ:- እግዚአብሔር አብ፣ ክርስቶስ ኢየሱስ በሰራው ስራ ምክንያት፣ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ለሰው ልጆች ለምስክርነት የሰጣቸው ነው።" የሐዋርያት ሥራ 3:13 ".....ብላቴናውን ኢየሱስን አከበረው።" 📌 የፀጋ ስጦታዎች ዋነኛ ዓላማ ኢየሱስን ማክበር ነው! የሐዋርያት ሥራ 3:15 "...ለዚህም ነገር እኛ ምስክሮች ነን።" 📌የኢየሱስ ክርስቶስን ሞት እና ትንሳኤ፣ በስሙም በማመን ስላለው መዳን ህያው መስካሪዎች ነን። 📍"የዳንን ቀን ያልሞትንበት ምክንያት ምስክሮች እንሆን ዘንድ ነው።" https://t.me/shekayinah
C A M P U S B R I D G E 2026 Jesus for every campus Great Commission Ministry Ethiopia, 12 graduates yearly training is here. Register 0929518782 / @Shekayinaah GC EMPOWERED FELLOWSHIP SLM “WIN THE STUDENT TODAY WIN THE WORLD TOMORROW” Stay tuned Follow us Instagram | Telegram | TikTok | All students
ኦሪት ዘፍጥረት 3:11 (AMH) •••••••••• ¹¹ እግዚአብሔርም አለው። ዕራቁትህን እንደ ሆንህ ማን ነገረህ? ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዝሁህ ዛፍ በውኑ በላህን?
እግዚአብሄርን መራብ ያቃተን አለምን መጥገብ ስለከበደን ነው Telegram
ለወንጌል ሰራተኛ ይህች አለም ደሞዝ የመክፈል አቅም የላትም በእግዚአብሄር አክሊል የሚከፈለው ስራ Telegram
እግዚአብሔራዊ ረሀብ ያለበት ሰው ለእራሱ ብቻ አይደለም ለእግዚአብሔር ይተርፈል:: Telegram
እርዳታ ከሰማይ ካልመጣ ውለታ ነው ከሰማይ ሲመጣ የፍቅር መገለጫ ነው። ከሰው እጅ ቀድሞ የእግዚአብሄር ይዘርጋላቹ Telegram
ብርታትን አቅም ያሳጣ ድካም አቅም የሚያጣው ብርቱ በሆነው በእግዚአብሔር ፀጋ ነው። Telegram
ወንጌል ውጪ ከሚሰብከው በላይ ውስጥ ሊኖር ይገባል Telegram
S H E K A Y I N A H pinned «ወንጌል የማእረግ ሂወት እንጂ የማእረግ ሞት የለውም ከሞት በሁዋላ ያለው ይበልጣል ሞትን አታሳምሩት ከሞት በሁዋላ ላለ ህይወት ተዘጋጁበት ጌታ ሊመጣ ነው። Telegram»
ኢየሱስ ነኝ ያለው ሁሉ ወንጌል ነው 1. "የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ" ዮሐንስ 6:35 — ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ “ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም።” 2. "የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ" ዮሐንስ 8:12 — ደግሞም ኢየሱስ፦ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም” ብሎ ተናገራቸው። 3. "በሩ እኔ ነኝ" ዮሐንስ 10:9 — “በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፤ ይገባልም ይወጣልም ማሰማርያም ያገኛል።” 4. "መልካም እረኛ እኔ ነኝ" ዮሐንስ 10:11 — “መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ይሰጣል።” 5. "ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ" ዮሐንስ 11:25 — ኢየሱስም አላት፦ “ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳ ሕያው ይሆናል።” 6. "መንገዱና እውነት ሕይወትም እኔ ነኝ" ዮሐንስ 14:6 — ኢየሱስም እንዲህ አለው፦ “መንገዱና እውነት ሕይወትም እኔ ነኝ፤ በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።” 7. "እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ" ዮሐንስ 15:1 — “እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፤ ገበሬውም አባቴ ነው።” S H E K A Y I N A H
ወንጌል የማእረግ ሂወት እንጂ የማእረግ ሞት የለውም ከሞት በሁዋላ ያለው ይበልጣል ሞትን አታሳምሩት ከሞት በሁዋላ ላለ ህይወት ተዘጋጁበት ጌታ ሊመጣ ነው። Telegram
መዝሙረ ዳዊት 127:1-2 (AMH) •••••••••• ¹ እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ፥ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤ እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ፥ ጠባቂ በከንቱ ይተጋል። ² በማለዳ መገሥገሣችሁም ከንቱ ነው። ለወዳጆቹ እንቅልፍን በሰጠ ጊዜ፥ እናንተ የመከራን እንጀራ የምትበሉ፥ ከተቀመጣችሁበት ተነሡ። Telegram
ሰላምህን አገኘሁ ፍቃድህን ለየው Telegram
በጥሪ ውስጥ ካላቹ ትግላችሁ ውስጥ ሰላም አለ ያለቦታችሁ ስትሆኑ ግን ሰላማችሁ ውስጥ ብዙ ህመም ያገኛቹሀል Telegram
የማይካድ ድንጋጤ ክብርህ ጋር ይገኛል የማይካድ ፍቅር እግርህ ስር ጥሎኛል በምን ቋንቋ ነው ይህ ውበት ሚወራው ይኸው የእኔ አቅም እንባዬን አንብበው Telegram
እየሰራቹ ስትታዩ እና ለመታየት ስትሰሩ ልዩነት አለው የፈሪሳዊ እና የኢየሱስ ህይወት ውስጥ ሰፊው ልዩነት ይህ ነበረ መቃብር ምንም ያህል ጥሩ ሀውልት ቢኖረው ውስጡ እሬሳ ነዉ Telegram
ሳናስፈልግህ ፈለከን Telegram
አትፍሩ ለሁሉም ጊዜ አለው ለጊዜው ደግሞ እግዚአብሄር በተረገዘ ማግስት አይወለድም ሁሉም በጊዜው ያለቅሳል በጊዜው ደግሞ ይስቃል ክረምት ብቻ አይሆንም በጋውም ይመጣል Telegram
1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2:13-21 (NASV) •••••••••• ¹³ ስለ ጌታ ብላችሁ ለምድራዊ ባለሥልጣን ሁሉ ተገዙ፤ የበላይ ባለሥልጣን ስለሆነ ለንጉሥ ቢሆን፣ ¹⁴ ወይም ክፉ አድራጊዎችን ለመቅጣትና በጎ አድራጊዎችን ለማመስገን እርሱ ለሾማቸው ገዦች ታዘዙ፤ ¹⁵ ምክንያቱም፣ መልካም በማድረግ የአላዋቂዎችን ከንቱ ንግግር ዝም እንድታሰኙ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው። ¹⁶ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ሆናችሁ በነጻነት ኑሩ እንጂ ነጻነታችሁን የክፋት መሸፈኛ አታድርጉት። ¹⁷ ለሰው ሁሉ ተገቢውን አክብሮት ስጡ፤ ወንድሞችን ውደዱ፤ እግዚአብሔርን ፍሩ፤ ንጉሥን አክብሩ። ¹⁸ እናንተ አገልጋዮች ሆይ፤ ለደጎችና ለገሮች ጌቶቻችሁ ብቻ ሳይሆን፣ ለክፉዎችም በፍጹም አክብሮት ታዘዙ። ¹⁹ ስለ እግዚአብሔር ሲል የግፍ መከራን የሚቀበል ሰው ምስጋናን ያገኛል። ²⁰ ክፉ ሥራ ሠርታችሁ ብትቀጡና ብትታገሡ ምን ምስጋና ይኖራችኋል? ነገር ግን መልካም ሥራ ሠርታችሁ መከራ ብትቀበሉና ብትታገሡ ይህ በእግዚአብሔር ዘንድ ምስጋና ያስገኝላችኋል። ²¹ የተጠራችሁትም ለዚሁ ነው፤ ምክንያቱም ክርስቶስ ስለ እናንተ መከራን የተቀበለው የእርሱን ፈለግ እንድትከተሉ ምሳሌን ሊተውላችሁ ነው። Telegram