ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ ▪️መጋቤ ምስጢር
Статистикаኦ አሐውየ እለ አፈቅረክሙ ጸልዩ ዲበ ድካምየ ከመ ይዕቀበኒ እግዚእ በዐቢይ ሣህሉ በሃይማኖት ርትዕት እስከ ፍጽሜ ደሓሪት እስትንፋስ። ወዝንቱ ውእቱ ባሕቲቱ ተስፋየ። ወስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ለዓለመ ዓለም አሜን። ሃይ. አበ. ዘቴዎዶስ. ፹፫፡፵፬ https://t.me/joinchat/SWWiqKcuci79Brh9
- Последний пост
- 6 авг.
- Последнее чтение
- 14 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 20
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 363
- 1/48двое суток
- 415
- 1/72трое суток
- 448
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
፩. ግእዝ ጉባኤ ቃና • ቅድሜከ እቁም እመ ፈቀደ ልብከ፥ • ላዕሌየ አንብር በርተሎሜዎስ ጸጋከ። ፪.፩. ዕዝል ጉባኤ ቃና • እሑድ ተዐቢ ወትትሌዐል እምነ ዕለታት ኵሎን፥ • አምጣነ ባቲ ተፀንሰ በሥጋ ብርሃነ ሕይወት መድሕን። ፪.፪. ዕዝል ጉባኤ ቃና • ምስለ ንጽሀ ሥጋ ድንግል ኀበ ምድረ ግብጽ መቅበርት፥ • ተሰደ ዮሴፍ ወልደ ገብርኤል ሠማዕት። ፫. ዘአምላኪየ • መቃብር ዐብድ እመ ልቡና አጥረይከ፥ • መጽሐፈ ወቅኔ ተመሀር ቤተከ፥ • መምህረ መጽሐፍ ወቅኔ አምጣነ መጽአ ኀቤከ። ፬. ሚ በዝሑ • ብርሃነ ሕይወት ይረክብ ዘይተልወኒ ሊተ እመ ኢየሱስ ይቤለነ፥ • ዘአልቦ ሐሰት ኢየሱስ ሐሰወነ፥ • እስመ ጊዜ ጽልመት ኮነ እመ ተሎነ ኪያሁ ብርሃነ ሕይወት ኀጣእነ። (ዮሐ. ፰፥፲፪) ፭. ዋይዜማ • ብርሃነ ሕይወት እግዚእነ ዘኵሎ የአምር በዕለተ እሑድ ገብረ፥ • መቃብረ ወሕልፈተ ሥጋ ሰማየ ወምድረ፥ • ምድረሰ ዕፁበ ዲበ ወኢምንት ሣረረ፥ • ወበአፈ ሙሴ ነቢይ ዘከመ ተነግረ፥ • መላእክተ በእሑድ ፈጠረ። ፮. መስኮት ዋይዜማ • በኢየሩሳሌም ድሬዳዋ ነጊሠ ነግሠ መጠነ አርብዓ ዓመት፥ • በዓለ ቅኔ ዳዊት ብርሃነ ሕይወት፥ • ወአስኬማ መንግሥቱ ርትዕት። ፯. ሐፂር ዋይዜማ • ዳዊት ብርሃነ ሕይወት ዘአልቦ ጽልሑት፥ • እምአኀዊሁ ተሐርየ ለሕልፈተ ሥጋ መንግሥት። • (ዳዊት ብርሃነ ሕይወት ዘአልቦ ጽልሑት፥- ፰. ሥላሴ • ሰብእ ውስተ ምድር ለእመ ያደሉ ለዘመዱ መልአከ ሰማይ ገብርኤል ለወልዱ እስመ ኀበ ሞት ፈነዎ፥ • በሰማይ ከመ ግብረ ሰብእ ኢሀሎ አድልዎ፥ • ወእምድሕረ ነቢይ ኤልያስ ለሥጋ ባሕረ ዮርዳኖስ ዐደዎ፥ • ሐሜለተ ኤልያስ ተመጢዎ፥ • ብርሃነ ሕይወት ኤልሳዕ ዘበአሕይዎ፥ • ሐሜለቶ ኤልያስ ጸገዎ። ፱. ዘይእዜ • በረቂቅ ብርሃን ዘይትአመን በብርሃን ያንሶሱ ወያደነግፅ ጋኔነ፥ • ወኀበ ጽልመት ኢየሐውር ይነሥእ ዳእሙ ዘሕይወት ብርሃነ፥ • ወአመ ክርስቶስ ይኴንን ሓጥኣነ ወጻድቃነ፥ • በብርሃነ ሕይወት ረቂቅ አምጣነ አመነ፥ • ብርሃነ ሕይወት ክርስቶስ ያስተቀጽለነ ለነ። • (በብርሃነ ሕይወት ረቂቅ አምጣነ አመነ፥) ፲. ሣህልከ • አመ ግብተ በጽሐ ወአመ ቦአ፥ • ሕልፈተ ሥጋ ክረምት ወሐጋየ ነቢር ወፅአ፥ • ኢትዮጵያ ዘትሴሰዮ ሥርናይ ብርሃነ ሕይወት ውስተ ምድር ተዘርአ። ፲፩. ሐፂር ሣህልከ • ነያ ትበኪ በአንጐርጕሮ፥ • ኢትዮጵያ ዘስእነት ብርሃነ ሕይወት ነጽሮ። (ነያ ትበኪ በአንጐርጕሮ፥) ፲፪. መወድስ • ብርሃነ ሕይወት ረቂቅ ዘኢይጸልም ብሂለከ ያሬድ ለምንት ትሔስወነ፥ • ዘነበብከ ቃለ ሰሚዐነ፥ • በግብት ብርሃነ ሕይወት እስመ ጸልመ ብነ፥ • ወእንዘ ናንሶሱ በብርሃን ግብተ ጠፍአ ወማሰነ ብርሃንነ። • ንሕነሂ አ-እ-መርነ ወጠየቅነ፥ • ምጽአተ ፀራዊ ሕልፈተ ሥጋ ዘከመ ሀለወ በአፍኣነ፥ • ወክሡት ውእቱ ከመ ታሕተ ሞት ኵልነ፥ • ሞት ለለ አሓዱ አኮኑ ይጸንሐነ። ፲፫. ኵልክሙ መወድስ • ብርሃነ ሕይወት ስፉሕ አውልዐ ገዳም ዘበታሕቴሁ አጽለለ አኀወ ወአበወ፥ • እንዘ በላዕሌሁ ዝናም በርተሎሜዎስ ሀለወ፥ • ሐዲጎ አሕመልምሎቶ አመ ወርሐ ሐምሌ እፎኑ መጽለወ፥ • ሥነ ልምላሜሁ ዘበበ አሜ ለዘይትዓቀብዎ ህዝብ እስመ እመ ይትዐቀብ ኢመጠወ። • ዘይቱሰ ዝክረ ቅኔ አመ ላዕለ መሬት ተክዕወ፥ • ፈወሰ መፃጕዐ ወድውየ አ-ሕ-የወ፥ • ወመዓዛሁ ጸሎት አልባበ ብዙሓን ፄወወ፥ • እስመ በርተሎሜዎስ ሰሊኆት/ቀፂመት ምስሌሁ ተሰናአወ፥ • ለነሂ ኮነነ ዘውስተ ገነት አፈወ። • (እስመ በርተሎሜዎስ ሰሊኆት/ቀፂመት ምስሌሁ ተሰናአወ፥) ፲፮. ሐፂር ኵልክሙ መወድስ • መቃብር ጸሊም እመ ኢትቀይሕ እንከ፥ • ብሩህ ብርሃነ ሕይወት ተውህበከ ለከ። ➖▪➖ 👁 እምኀበ መጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ 👁 ሐምሌ ፳፮/፳፻፲፰ ዓ/ም
Channel photo updated
✅ በሥላሴ መካከል የሥልጣን መበላለጥ የለም። ቅዱስ ሳዊሮስም “ወአልቦ በውስተ ቅድስት ሥላሴ ግብርናት ወኢ ተጋንዮ ወኢይትሌዐል አሓዱ እምካልኡ በመዓርገ መለኮት ወኢይኤዝዞ አሓዱ ለካልኡ ዘከመ ተለኣኪ በሥልጣኑ አላ እሙንቱ ዕሩያን በአሓዱ ክብር ዘመለኮት ወምልክና ወሉዓሌ ብርሃን ዘአኃዜ ኵሉ - በሦስቱ አካላት ውስጥ መገዛት፣ መታጠቅና መፍታት የለም፤ በመዓርገ መለኮትም አንዱ ካንዱ አይበልጥም፤ አንዱ አንዱን እንደ መልእክተኛ አድርጎ በሥልጣኑ አያዝዘውም፤ በአንድ መለኮት ክብርና በአገዛዝ የሁሉ ፈጣሪ ገንዘብ በሚሆን በባሕርይ ዕውቀት አንድ ናቸው እንጂ።” ብሏል። ሃይ. አበ. ፹፬፡፮። ✅ ሥላሴ አምላክ ወይስ አማልክት? ሥላሴ አንድ አምላክ ይባላሉ እንጂ ሦስት አማልክት አይባሉም። ቅዱስ አትናቴዎስም “አምላክ ውእቱ አብ፥ ወአምላክ ውእቱ ወልድ፥ ወአምላክ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ፤ ወኢይትበሀሉ ሠለስተ አማልክተ አላ አሓዱ አምላክ - አብ አምላክ ነው፤ ወልድም አምላክ ነው፤ መንፈስ ቅዱስም አምላክ ነው፤ ነገር ግን አንድ አምላክ እንጂ ሦስት አማልክት አይባሉም።” ብሏል። ሃይ. አበ. ፳፭፡፬። ቅዱስ ጎርጎርዮስም “ወኢንሰግድ ለሠለስቱ አማልክት አላ ለአሓዱ አምላክ - ለአንድ አምላክ እንሰግዳለን እንጂ ለሦስት አማልክት አንሰግድም።” ብሏል። ሃይ. አበ. ፷፡፮። ✅ ቅድመ ዓለም የወልድ ከአብ መወለድ አይመረመርም። ወልድ ቅድመ ዓለም ከአብ ሳያንስና ሳይበልጥ አብን አህሎ፥ አብን መስሎ ከአብ አካል ዘእምአካል ባህርይ ዘእምባህርይ ተወልዷል። አብ ወልድን ከባህርዩ የወለደበት ዘመንም አይታወቅም። ጥንትም የለውም። የወለደበት ምስጢርም በመላእክትም ሆነ በሰዎችም አእምሮ አይታወቅም። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘቂሳርያም “ወልደቱሰ ለወልድ እምአብ ዘኢይትረከብ ወኢይትከሀል ተናግሮቱ እስመ መንፈሳዊ ውእቱ እንበለ ተኃሥሦ እስመ ለመንፈሳዊ ኢይክል ሥጋዊ ረኪቦቶ ወኢይደልዎ ይትኃሠሥ በእንቲኣሁ እስመ ኢይትማሰል በህላዌ እጓለእመሕያው ወኢኮነ ልደቱ ከመ ልደተ እጓለእመሕያው ዐቢይ ምስጢር ውእቱ ወኢይትረከብ - የወልድ ከአብ መወለዱ የማይመረመር ሊናገሩትም የማይቻል ነው፤ የማይመረመር ረቂቅ ስለሆነ ግዙፉ ረቂቁን መርምሮ ማወቅ የማይቻለው ነውና፥ የርሱን ነገር ይመረምር ዘንድ አይቻለውምና፥ ከሰው ባሕርይ ጋርም አይመሳሰልምና፥ ልደቱም እንደ ሰው ልደት አይደለምና ረቂቅ ምስጢር ነው። አይመረመርም።” ብሏል። ሃይ. አበ. ፲፫፡፲፩-፲፪። ✅ ከአብ ወልድ ሳይወለድና መንፈስ ቅዱስ ሳይሠርጽ የተቈጠረ ጊዜ የለም። “ወልድ ከአብ በተወለደበት ቅጽበት መንፈስቅዱስ ከአብ ሳያንስና ሳይበልጥ አብን አህሎ፥ መስሎ አካል ዘእምአካል ባህርይ ዘእምባህርይ ከአብ ሠርጿል። ወይም መንፈስ ቅዱስ ከአብ በሠረጸበት ቅጽበት ወልድ ከአብ ተወልዷል። በወልድ ከአብ መወለድና በመንፈስ ቅዱስ ከአብ መሥረጽ መካከል መቅደም መቀዳደም የለም። አብም ወልድን ቢወልድና መንፈስቅዱስን ቢያሠርጽም ከወልድና ከመንፈስቅዱስ በዘመን አይቀድምም፤ በሥልጣንም አይበልጥም። አብ መንፈስቅዱስን ያሠረጸበት ዘመንም ከቶ አይታወቅም። ጥንትም የለውም። ከባህርዩ ያሠረጸበት/ያስገኘበት ምስጢርም በመላእክትም ሆነ በሰዎች አእምሮ አይታወቅም። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም “ኢነአምር ዘከመ እፎ ወለዶ አብ ለወልድ ወዘከመ አሥረጾ ለመንፈስ ቅዱስ - አብ ወልድን እንዴት እንደ ወለደውና መንፈስቅዱስን እንዴት እንዳሠረጸው አናውቅም።” ብሏል።” መጽ. ምስ. ፫፡፲፰። ቅዱስ ዲዮናስዮስም “ልደተ ወልድ ወፀአተ መንፈስ ቅዱስ እምአብ ይትነከር ወኢይትነገር ወይትሌዐል ላዕለ ኵሉ ሕሊናት ወኢይትረከብ - ከአብ የወልድ መወለድና የመንፈስ ቅዱስ መሥረጽ በዕፁብ ይወሰናል እንጂ እንዲህ ነው ተብሎ አይነገርም፤ ከሕሊናት ሁሉ በላይ ነው፤ አይመረመርም።” ብሏል። ሃይ. አበ. ፲፡፲፩። #ማስታወሻ፦ የሥላሴ የአካል፣ የግብርና የባሕርይ ከዊን ስሞች፦ • በአካል የሚጠሩባቸው ስሞች፦ አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ፤ • በግብር የሚጠሩባቸውን ስሞች፦ ወላዲ/አሥራጺ፣ ተወላዲ፣ ሠራጺ፤ • በባሕርይ ከዊን የሚጠሩባቸው ስሞች፦ ልብ፣ ቃል፣ እስትንፋስ፤ ጦማሪ፦ መጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ
“በእግዚአብሔር አብ፤ በእግዚአብሔር ወልድ፤ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እናምናለን።" ሃይ. አበ. ፲፱፡፳፱። እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፍጥረታትንም ሁሉ ከመፍጠሩ በፊት በአምላክነቱ ጸንቶ የነበረ፥ ፍጥረታቱንም ሁሉ ፈጥሮ አሁንም ያለ ሕያው አምላክ ሲሆን ሰማይንና ምድርንም አሳልፎ ፍጻሜ ሳይኖረው ለዘለዓለሙ የሚኖር ዘለዓለማዊ አምላክ ነው። እግዚአብሔርም በባሕርይ፣ በህልውናና በአገዛዝ አንድ አምላክ ሲሆን በስም፣ በግብርና በአካል ሦስት ነው። ✅ ፩. የሥላሴ የስም ሦስትነት፦ ሥላሴ የስም ሦስትነት አላቸው። ይህም ማለት “አብ፣ ወልድ፥ መንፈስ ቅዱስ” ተብለው መጠራታቸው ነው። በሦስቱ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ'ም የስም ተፋልሶ የለም። ቅዱስ ዮሐንስ ዘእስክንድርያም “አስማትሰ ኢየሐብሩ በበይናቲሆሙ፥ ስመ አብ ለከዊነ ስመ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፥ ወስመ ወልድ ለከዊነ ስመ አብ ወመንፈስ ቅዱስ፥ ወስመ መንፈስ ቅዱስ ለከዊነ ስመ አብ ወወልድ - የአብ ስም የወልድና የመንፈስ ቅዱስ ስም ሊሆን፤ የወልድም ስም የአብና የመንፈስ ቅዱስ ስም ሊሆን፤ የመንፈስ ቅዱስ ስምም የአብና የወልድ ስም ሊሆን ስሞች እርስ በርሳቸው አይቀላቀሉም።” ብሏል። ሃይ. አበ. ፺፡፱። ✅ አብ ወልድና መንፈስ ቅዱስ በወልም ሆነ በተናጠል የሚጠሩበት ስም፦ እግዚአብሔር፥ አዶናይ፣ ጸባኦት፣ ኤልሻዳይ፣ አምላክ፣ ፈጣሪ’ና የመሳሰሉት የአንድነት ስም ይባላል። ቅዱስ ጎርጎርዮስም “አንሰ ሶበ እቤ እግዚአብሔር እብል በእንተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እስመ አሓዱ ውእቱ መለኮተ ሥላሴ ወሠለስቲሆሙ አሓዱ እሙንቱ በመለኮት - እኔ እግዚአብሔር ባልሁ ጊዜ ስለ አብ፣ ስለ ወልድና ስለ መንፈስ ቅዱስ እናገራለሁ፤ የሦስቱ ባሕርይ አንድ ነውና፤ ሦስቱም በመለኮት አንድ ናቸውና።” ብሏል። ሃይ አበ. ፺፮፡፮። ✅ ፪. የሥላሴ የአካል ሦስትነት፦ ሥላሴ ለእያንዳንዳቸውና ለየራሳቸው ፍጹም አካል አላቸው። አብ ፍጹም አካል አለው። ወልድም ፍጹም አካል አለው። መንፈስ ቅዱስም ፍጹም አካል አለው። የሥላሴ አካላትም ውሱንነት የሌለባቸው፣ በሰው እጅ የማይዳሰሱ፣ በሰው ዐይንም የማይታዩ፣ በሁሉ ምሉኣን የሆኑ ናቸው እንጂ እንደ ሰው ልጅ አካል ግዘፍና ውሱንነት ያለባቸው አካላት አይደሉም። እንደ ሰው አካል የተወሰነ፣ የተከፋፈለና ቅርጽ ያለው አካልም የላቸውም። ቅዱስ አትናቴዎስም፦ “የሥሉስ ቅዱስ የሚሆኑ ሦስት አካላት፣ ሦስት ገጻት፣ ሦስት መልክዓት እንዳሉት፥ ስለ መለኮት የተነገረውንም ሁሉ እናምናለን። በከበሩ በሠለስቱ ምእት መጻሕፍት እንደ ተነገረ ስለነርሱ የተነገረውም እውነት ነው። መርምሮ ማወቅ ግን አይቻልም፥ እናምንበታለን እንጂ። ለእግዚአብሔር ዐይን፣ ጆሮ፣ እጅና እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈው ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው። የተናገርነውም ሁሉ ለእግዚአብሔር አለው፤ ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም።” ብሏል። ሃይ. አበ. ፳፰፡፳፱-፴። መዝ. ፴፫፡፲፭፤ ፻፲፰፡፸፫። ፩ ጴጥ. ፫፡፲፪። ራእ. ፩፡፲፫-፲፯። ሥላሴ በአካል ሦስት እንደ ሆኑና በየአካላቸው ጸንተው እንደሚኖሩም ቅዱስ ሚናስ “አካለ አብ ካልእ እምአካለ ወልድ ወእምአካለ መንፈስ ቅዱስ፤ ወአካለ ወልድኒ ካልእ እምአካለ አብ ወእምአካለ መንፈስ ቅዱስ፤ ወአካለ መንፈስ ቅዱስኒ ካልእ እምአካለ አብ ወእምአካለ ወልድ - የአብ አካል ከወልድ አካልና ከመንፈስ ቅዱስ አካል ልዩ ነው፤ የወልድ አካልም ከአብ አካልና ከመንፈስ ቅዱስ አካል ልዩ ነው፤ የመንፈስ ቅዱስም አካል ከአብ አካልና ከወልድ አካል ልዩ ነው።” ብሏል። ሃይ. አበ. ፻፡፰። የአብ፣ የወልድና የመንፈስ ቅዱስ ሦስት አካላትም ቀድመው ተገኝተው “አብ፣ ወልድ፥ መንፈስ ቅዱስ” የሚል ስም በኋላ የወጣላቸው አይደለም። ወይም ስሞቻቸው ቀድመው ተገኝተው አካላት የተከተሉ አይደለም። የሥላሴ አካላት ከሥላሴ ስሞች አይቀድሙም፥ አይከተሉምም። ስሞቻቸውም ከአካሎቻቸው አይቀድሙም፥ አይከተሉምም። ሰው በማሕፀን ሲፈጠር ሰው የሚለው የባህርይ ስሙና አካሉ እንደማይቀዳደሙና በዕሪና እንደሚገኙ በሥላሴ አካላትና አስማትም መቅደም መቀዳደም፣ መከተል መከታተል የለባቸውም። ሃይ. አበ. ፲፫፡፬-፮። ✅ ፫. የሥላሴ የግብር ሦስትነት፦ የአብ ግብሩ ወላዲነት አሥራጺነት፣ የወልድ ግብሩ ተወላዲነት፥ የመንፈስ ቅዱስ ግብሩ ሠራጺነት ነው። ስለዚህ ሥላሴ በግብር ስማቸው “አብ ወላዲ፥ አሥራጺ፥ ወልድ ተወላዲ፥ መንፈስ ቅዱስ ሠራጺ” ይባላሉ። ያንዱን ግብር ላንዱ መስጠትም አይቻልም። አብ ቢወልድና ቢያሠርጽ እንጂ አይወለድም፤ አይሠርጽምም። ወልድም ቢወለድ እንጂ አይወልድም፤ አያሠርጽም፤ አይሠርጽምም። መንፈስ ቅዱስም ቢሠርጽ እንጂ አይወልድም፤ አያሠርጽምም፣ አይወለድምም። ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአንጾኪያም “ነአምሮ ለአብ በኢልደት፤ ወለወልድኒ በልደት፤ ወለመንፈስ ቅዱስኒ በፀአት - ባለመወለድ አብን፣ በመወለድ ወልድን፣ በመሥረጽ መንፈስ ቅዱስን እናውቀዋለን።” ብሏል። ሃይ. አበ. ፺፱፡፱። ዮሐ ፲፬፡፰-፲። ✅ ሥላሴ በባህርይ፣ በሥልጣን፣ በፈቃድ… አንድ ናቸው። ቅዱስ አግናጥዮስም፦ “አብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ህልው እንደ ሆነ፤ ወልድም በአብና በመንፈስ ቅዱስ ህልው እንደ ሆነ፤ መንፈስ ቅዱስም በአብና በወልድ ህልው እንደ ሆነ እናምናለን። ይህች ሦስትነት ያለ መለየትና ያለ መለወጥ በሦስት አካላት በአንድ መለኮት የተካከለች ናት። አንዲት አገዛዝ፣ አንዲት ፈቃድ፣ አንዲት ኀይል፣ አንዲት መንግሥት፣ አንዲት ስግደት፣ አንዲት ምስጋና፣ አንዲት ክብር፣ አንድም ጽንዕ ለሥላሴ ንገባል። አንዲት ምክር፣ አንዲት ሥልጣን፣ አንዲት ክብር፤ አንዲት ጽንዕ፣ አንዲት አኗኗር፥ አንዲት ፈቃድ ለሥሉስ ቅዱስ አለቻቸው። አብም አብ ነው እንጂ ወልድም መንፈስ ቅዱስም አይደለም። ወልድም ወልድ ነው እንጂ አብም መንፈስ ቅዱስም አይደለም። መንፈስቅዱስም መንፈስቅዱስ ነው እንጂ አብም ወልድም አይደለም። አብ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን ወደ መሆን አይለወጥም። ወልድም አብንና መንፈስቅዱስን ወደ መሆን አይለወጥም። መንፈስ ቅዱስም አብንና ወልድን ወደ መሆን አይለወጥም። እነዚህ ሦስቱ አካላት በጌትነትና በክብር ፍጹማን ናቸው። በአንድ መለኮት አንድነትም አንድ ናቸው።” ብሏል። አግና. ሃይ. አበ. ፲፩፡፭-፰። ✅ በሥላሴ ዘንድ የዘመንና የጊዜ መቀዳደም የለም። ሠለስቱ ምእትም “ኢሀሎ አብ ዘመነ ዘእንበለ ወልድ፥ ወኢሀሎ ወልድ ዘመነ ዘእንበለ መንፈስ ቅዱስ፥ ወመንፈስ ቅዱስሂ ኢሀሎ ዘመነ ዘእንበለ አብ ወወልድ፥ አላ ሥሉስ ቅዱስ ህልው በኵሉ ዘመን ወመዋዕል እንዘ ኢይትዌለጥ ወእንዘ ኢትይፋለስ - አብ ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም። ወልድም ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም። መንፈስ ቅዱስም ከአብና ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም። ሥሉስ ቅዱስ በዘመኑም ሆነ በቀኑ ሁሉ በግብርም በስምም ላይለወጥ ሳይፋለስ ጸንቶ ያለ ነው እንጂ።” ብለዋል። ሃይ. አበ. ፲፱፡፭።
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
ጊዮርጊስ ወልደ ዓሚድ በሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረ ከዓረብ ምድር የተገኘ ዓረባዊ ኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያን ነው። የታሪክ አጥኚና ደራሲም ነበር። በግብጽና በሶርያ በቤተ መንግሥትም ትልቅ ዝናና የላቀ ክብር ነበረው፡፡ ይህም በስሙ "ጊዮርጊስ ወልደ ዓሚድ" ተብሎ የተሰየመውን ዜና መዋዕል ከአዳም ዘመን አንሥቶ እስከ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ያለውን የ6114 ረጅም የዘመን ታሪክን አጕልቶ በመተረክ የሚናገር ግዙፍ መጽሐፍ ነው። ከአዳም አንሥቶ ዓለም ዐቀፋዊ የሆነውን ታሪክ የያዘው "ጊዮርጊስ ወልደ ዓሚድ" የተሰኘው ይህ መጽሐፍ ተጽፎ የተጠናቀቀው በ614 ዓ/ም ነው። ነገር ግን አንዳንድ ሰዎች ጊዮርጊስ ወልደ ዓሚድ የተጻፈበት ዘመን ከ1255 -1261 ዓ/ም ያለው ዘመን መሆኑን ይጠቍማሉ። ጊዮርጊስ ወልደ ዓሚድ የነበረበትንም ዘመን ከ1199 - 1267 ዓ/ም ድረስ መሆኑን ይናገራሉ። ይህም የታሪክ መጽሐፍ ጠቅላላ ፻፷፭ ምዕራፍ ያለውና ባለ ፯፻ ገጽ የሆነ እጅግ ግዙፍ መጽሐፍ ሲሆን እስካሁን ድረስ ሙሉ ለሙሉ በግእዝና በዐማርኛ ቋንቋዎች ጎን ለጎን ሆኖ በአንድ ጥራዝ ሳይታተም ቆይቷል። አሁን ግን በግእዝና በዐማርኛ ቋንቋዎች ጎን ለጎን ሆኖ በአንድ ጥራዝ ሊታተም ፍጻሜውን ወደ ማግኘት ደረጃ እየደረሰ ይገኛል። ➖▪➖ የጊዮርጊስ ወልደ ዓሚድ ይዘት በከፊል ➖▪➖ • ከአዳም አንሥቶ እስከ 6114 ዓ/ዓ ያለውን ታሪክ ቅደም ተከተሉን ጠብቆ ይተርካል። • ከመጀመሪያ አንሥቶ እስከ 614 ዓ/ም ድረስ ያሉትን የሮም ነገሥታትን ታሪክ ይተርካል። • በዐለም ላይ የነገሡት የተለያዩ ሀገራት ሐያላን ነገሥታት ሙሉ ታሪካቸውን ይተርካል። • የልዩ ልዩ ሀገራትና ከተሞች ምሥረታን ይተርካል። • የልዩ ልዩ መናፍ*ቃ*ን ምንፍ*ቅ*ናንና ታሪካቸውን ተርኮ ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ ይሰጣል። • በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ታሪካቸው ያልተሟሉትን አሟልቶ ይዟል። • ከአንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን አንሥቶ እስከ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ የተነሡትን ቅዱሳን ሊቃውንትን በመዘርዘር ሙሉ ታሪካቸውን ያስቀምጣል። • የእግዚአብሔር ሀልዎትና መግቦት፣ አንድነትና ሦስትነት፥ በጥቅሉ ምሥጢረ ሥላሴን በጕልህ ያስገነዝባል። • ነገረ ማርያም፣ ነገረ ቅዱሳንንና ነገረ መስቀልን በአግባቡ እንዲገነዘቡ ያደርጋል። • ሐዲሳትንና ብሉያትን በትርጓሜ የሚማሩ ደቀ መዛሙርት በአንድምታ ለሚያገኟቸው ታሪኮች ምንጭ ሆኖ ያገለግላል። • ስለ ሥነ ፈለክ፣ ስለ ዑደተ ፀሓይ ወወርሕ፣ ስለ ምሕዋረ ከዋክብትና ስለ ዐበይት አፍላጋት... ሰፊ ዕውቀትን ያስጨብጣል። • የተለያዩ ነገድ አሰፋፈርና አቀማመጥን ለይተው እንዲያውቁ ያግዛል። • የኢትዮጵያ ጥንታዊ ዐለም ዓቀፋዊ መሪነትንና ሐያልነትን እንዲያውቁ ያደርጋል። • የዘመናት ቀመርን ጠንቅቀው እንዲረዱ ያግዛል። • የግእዝ ቋንቋ ችሎታን (ክሂሎትን) ያዳብራል። ✍️ መጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ
видео или голосовое, без подписи
የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤ ዛሬ ሠኔ ፲፫/፳፻፲፰ ዓ/ም በሳባ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሁለገብ አዳራሽ ለጸዋትወ ዜማ መምህራንና መሪጌቶች (መዘምራን) ሰፊ ሥልጠና ሰጠ። "እዜምር በመንፈስየ ወእዜምር በልብየ ለርእስየኒ ወለቢጽየኒ = በነፍሴ እዘምራለሁ፥ በልቤም ለራሴና ለባልንጀራዬ እዘምራለሁ።" ፩ ቆሮ. ፲፬፡፲፭። በብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ ሐምሌ ፩/፳፻፲፯ ዓ/ም የተዋቀረው የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤ በድጓ፣ በአቋቋም በዝማሬ መዋሥእትና በቅዳሴ በመምህርነት እያገለገሉ ላሉ የጸዋትወ ዜማ መምህራንና መሪጌቶች (መዘምራን) "ያሬዳዊ ዜማና መጽሐፍ ቅዱስ" በሚል ርእስ ሰፊ ሥልጠና አከናውኗል። ጉባኤውም በጸሎት የተጀመረ ሲሆን የሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራአስኪያጅ መጋቤ ሠናያት ቀሲስ #ኀይለማርያም ገብረ ሚካኤል በጉባኤው ለተገኙ የጸዋትወ ዜማ መምህራንና መሪጌቶች የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክትን ከሰጡ በኋላ ሥልጠናውን በተመለከተ የብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ ጥብቅ መመሪያን አስተላልፈዋል። ሥልጠናውንም በአጽንዖት እንዲከታተሉና የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰቶችን ለምእመናን በሚመጥን አቀራረብ ማድረስ ይቻል ዘንድ ዐደራ ብለዋል። በመቀጠልም የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤ ዋና ሰብሳቢ የሆኑት መጋቤ ምስጢር #ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ "ያሬዳዊ ዜማና መጽሐፍ ቅዱስ" በሚል ርእስ ተነሥተው ሰፊ ሥልጠና ሰጥተዋል። በትምህርታቸውም ቅዱስ ያሬድ ከብሉይ፣ ከሐዲስ፣ ከሊቃውንት፣ ከመነኰሳትና ከታሪክ መጻሕፍት ጠቅሶ ጸዋትወ ዜማን መድረስ መቻሉን በመግለጽ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰቶች ሁሉ ከመጽሐፍ ቅዱስ ቃል የተቀዱ መሆናቸውን በመግለጽ ለምእመናን ማድረስ የሚቻልበትን መንገድ በጥልቀት አብራርተዋል። በጸዋትወ ዜማ በመምህርነት የተመረቁ በሥልጠናው የተገኙ መምህራንና መሪጌቶችም (መዘምራን) የተሰጣቸው ሥልጠና እጅግ አመርቂ መሆኑን ገልጸው ተገቢ የሆኑ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። ለጥያቄዎቻቸውም ተገቢ የሆነ ምላሽ ሥልጠናውን በሰጡት መጋቤ ምስጢር #ያሬድ ዘርአ - ቡሩክ ተሰጥቷቸዋል። መምህራኑም ወንጌልን ይበልጥ ለማስፋፋትና ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን በደስታ ገልጸዋል። በማያያዝም የሀገረ ስብከቱ የካህናት አስተዳደር ክፍል ኀላፊ መልአከ ገነት ቀሲስ #ደሳለኝ ሀብቱና የሀገረ ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ክፍል ኀላፊና የሊቃውንት ጉባኤ አባል የሆኑት መጋቤ ብሉይ #ሠምረ_አብ ገብሬ ልዩ ልዩ መልእክቶችን አስተላልፈዋል። በመጨረሻም የሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራአስኪያጅና የሊቃውንት ጉባኤ ዋና ጸሓፊ መጋቤ ሐዲስ ቆሞስ አባ #ዕንባቆም ገብረ ኪዳን ልዩ የሀገረ ስብከቱ መመሪያና ቃለ ምዕዳን ከሰጡ በኋላ ጉባኤውን በጸሎት አጠናቀዋል። ➖▪➖ የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቃውንት ጉባኤ ቀደም ሲል በ፳፻፱ ዓ/ም የሀገረ ስብከታችን ዋና ሥራአስኪያጅ በሆኑት መጋቤ ሠናያት ቀሲስ #ኀይለማርያም ገብረ ሚካኤል አሳሳቢነት፥ በብፁዕ አቡነ #ዳንኤል መልካም ፈቃድና መመሪያ ሰጪነት የተዋቀረ ሲሆን እንደ ዐዲስ ሐምሌ ፩/፳፻፲፯ ዓ/ም በብፁዕ አቡነ #በርተሎሜዎስ ልዩ መመሪያ ሰጪነት በሰፊው ተደራጅቶ አመርቂ መንፈሳውያን ተግባራትን በማከናወን ላይ ያለ መሆኑ የሚታወቅ ነው። #የድሬዳዋ_ሀገረ_ስብከት_ጽሕፈት_ቤት 📢 ለፈጣንና ተአማኒ መረጃዎች ➩የፌስቡክ ገጻችን 👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=61563382452089 ➩የቲክቶክ ገጻችን👇 https://www.tiktok.com/@ddhagersebektmedia ➩የቴሌግራም ገጻችን👇 https://t.me/ddhageresebket #Follow #Share #Like #ያድርጉ_ቤተሰብ_ይሁኑ
• ቅኔ ዘሠኔ ፲፪/፳፻፲፰ ዓ/ም ፩. ግእዝ ጉባኤ ቃና • በሌሊት ብርሃነ እንዘ ያበርህ ጥዩቀ፥ • ብሩህ ኮከብ ሊቀ ብርሃናት ሠረቀ። ፪.፩. ዕዝል ጉባኤ ቃና • ኵሉ ለያጽልል ተትሒቶ መትሕተ ሊቃውንት አእዋም፥ • እስመ ከመ ይዝንም ግብተ ሀለዎ ለቅኔ ያሬድ ዝናም። ፪.፪. ዕዝል ጉባኤ ቃና • ሚካኤል ቀሲስ በጽንሓሕከ ለቤተ ክርስቲያን ምርጕዛ፥ • መዓዛ ዕጣንከ ፍቅረ ዐዋዴ ለኢትዮጵያ አምዕዛ። ፫. ዘአምላኪየ • ለአርዌ ዐመፃ ወሞት ዘኢሐደገ እከዮ፥ • ሚካኤል እምኢትዮጵያ ፍጡነ ደርብዮ፥ • ወለዘበሕምዙ ደወየ ቀዲሙ በምሕረትከ አጥዕዮ። ፬. ሚ በዝሑ • ነዳየ ሐጕለ ፀር ባሕራን በሠይጠ መጽሐፍ አእተተ ንዴተ ሐጕለ ፀር ወሱታፉ፥ • አምጣነ አኮ ነዳይ ዘይትረሳዕ ለዝሉፉ፥ • ወበሀብተ መጽሐፍ ከብረ በዐይነ ሚካኤል አንባቢ እስመ ይትነበብ መጽሐፉ። ፭.፩. ዋይዜማ • ቤተ ክርስቲያን አፎምያ ዘባቲ ሐለፈ አስተራኒቆስ ሰላም፥ • አውሥአቶ ነገረ መስቀል ለመልአክ ሕሡም፥ • ወአይቴ ሀለወ ትእምርተ መስቀልከ ዮም፥ • ትቤሎ፦ ቅድመሰ ዘሖርከ ኀበ ማርያም፥ • ብሥራታዊ ብሥራተከ ሢም። ፭.፪. ዋይዜማ • ሚካኤል ግብረ ዚኣከ ግብረ መደልው ውእቱ እስመ ከመ ታዘልፍ ዘልፈ፥ • ቀዊመከ ማእከለ ፍኖት ታነብብ መጽሐፈ፥ • ወታነውሕ ቃለ ኀበ ኀበ ትከሥት አፈ፥ • መሠረተከሂ አሐዘ ወአስተናደፈ፥ • ውስተ ባሕር ዘገደፈ እልፈ። ፮. መስኮት ዋይዜማ • መልአከ ጽልመት ለአፎምያ ያመክራ ምዕረ እመ ውስተ ቤታ የአቱ፥ • ዘምስሌነሰ ይነብር በበ ዕለቱ፥ • እስመ ንሕነ ለሰይጣን አዕርክቱ። ፯. ሐፂር ዋይዜማ • ምዝጋናየ እምይትባኅነኒ መዊተ እፈቱ፥ • አምጣነ ቅኔ ሀብትየ ወሕይወትየ ውእቱ። • (ምዝጋናየ እምይትባኅነኒ መዊተ እፈቱ፥) ፰. ሥላሴ • መላእክት እኩያን መላእክተ ብርሃን ተመሲሎሙ በኢትዮጵያ ተርእዩ አኮኑ እንዘ ይትመያየጡ ስብዐ፥ • ሚካኤል ሰይፈ መዓትከ ነሢአከ ነዐ፥ • ወበላዕሌሆሙ ኩን እንከሰ ዘእምልብከ ቍጡዐ፥ • ወኢትትመሰሎሙ መዘንግዐ፥ • ምሕረተከሂ ይነጽር ኵሉ ዘበፅዐ፥ • እምኀቤከ ለይትመጦ ጽንዐ። ፱.፩. ዘይእዜ • ሚካኤል ለምንት አርምሞትከ እስመ ውስተ ቤትከ ጽድቅ እንበለ ይኩን ማእምረ፥ • መልአከ ብርሃን ተመሲሎ እኩይ መልአከ ጽልመት አሐዘ መንበረ፥ • ይትሐደግሰ ወንጌል መልክዐ መልክዕ ኢተምህረ፥ • ትምህርተ ጽድቅሂ ይትመሀር ለእመ ተነግረ፥ • ሐዲጎ ትምህርተ አፎምያሀ አፍቀረ። • (ትምህርተ ጽድቅሂ ይትመሀር ለእመ ተነግረ፥) ፱.፪. ዘይእዜ • ሶበ ኮነ ቀትር ጽልሑተ ጸር ለሐላፌ ፍኖት ባሕራን ኢረከባሁ ድካም፥ • ምጽላለ ሕይወት እስመ ኮኖ ዘበቈለ ማእከለ ፍኖት ሚካኤል ኦም፥ • ወውእቱ ኦም ሚካኤል ዘይጌርም፥ • መድሓኒት ውእቱ ለዘየሐምም፥ • ወእምአፎምያ ተግሕሠ ደዌ ምክረ ፀር ሕሡም። (መድሓኒት ውእቱ ለዘየሐምም፥) ፲. ሣህልከ • እመኒ በሐይል እምእለ ነግሡ፥ • በኢትዮጵያ ድንግል አድሕኖተነ ተኀሡ፥ • ሚካኤል አርምሞተከ ወተደሞተከ ገብርኤል አግሕሡ። ፲፩. ሐፂር ሣህልከ • ሚ ትትሜዐዝ ደብረ ምሕረት፥ • እስመ በላዕሌሃ ይውሕዝ #በርቶሎሜዎስ ዕፍረት። • (ሚ ትትሜዐዝ ደብረ ምሕረት) ፲፪. መወድስ • መልእክተ ሕይወት ይኩን ከመ ተወለጠ ጦማረ ሞቱ ለባሕራን ዘይትአመን ረድኤተ፥ • ከመ ምስሌሁ ለባሕራን ለእመ ምስሌነ አንተ፥ • መልአከ ሕይወት ሚካኤል ወልጥ ጦማረ ሞትነ ወአሰስል ሞተ፥ • ወመልእክተ ሞትነ ደምሲሰከ በሰሌዳ ሰብእነ ጸሐፍ ፊደለ መጻሕፍት ሕይወተ፥ • እግዚእነሂ ኢይደሉ አርምሞትከ እስፍንተ፥ • ሰብእ ላዕለ ሰብእ እስመ ኮኑ አራዊተ፥ • ወበአፈ ዳዊት እብለከ ለእመ ሰማዕከኒ ሊተ፥ • ከዐው ላዕሌሆሙ መዓተ ወመቅሠፍተ። ፲፫. ኵልክሙ መወድስ • ዕንጦንስ ብኪ በይነ ደቂቅከ እስመ ደቂቅከ ኀልቁ ውስተ ማዕበለ ግዮን ትዕይንት፥ • አመ ውስተ ገዳም ኮነ አፍቅሮ ንዋይ ክረምት፥ • ወመፍትው መቃርስ ከመ ትበል ትኩዝየ በመዋዕልየ አንሶሱ ለምንት፥ • ሚካኤል ዘወሀበከ አስኬማከ ለከ መዝገበ ንዋይ (ምክንያተ ሞት) እስመ ኮነት። • አመሂ የሐልፉ ማእከለ አድባር ማያት፥ • ይትዌከፉ ለጽምኦሙ ሐለስዮታት መነ**ሳት፥ (መዝ. ፻፫፡፲፩) • ወእምጋኔነ ቀትር ረቂቅ ወእሞተ ግብት፥ • መሐረነ አምላክነ አምላከ ጻድቃን ወሠማዕት። • ወኢይኩን ብነ ዘቤተ ክርስቲያን ድቀት። • መሐረነ አምላክነ አምላከ ጻድቃን ወሠማዕት። ፲፬. ሐፂር ኵልክሙ መወድስ • ቅኔ መዓር ዘምስለ ማኅሌት ሐሊብ፥ • እስመ ቀርበ እንዘ ይጻውዑ ተጋብኡ ህዝብ። ፲፯. ዕዝል ክብር ይእቲ • መኰንነ ጽድቅ ክርስቶስ እመ ፈቀድከ ከመ ንትጋዐዝከ ለከ፥ • አኮ ርቱዕ ዘዕለተ ዐርብ ፍትሕከ፥ • እስመ እንዘ ፍቅር አንተ ነፍስተ ይሁዳ ጸላእከ፥ • ወእምክልኤቱ ፈያት ለአሓዱ ግብረ አድልዎ ፈጸምከ። ፲፰. ዕዝል ዕጣነ ሞገር • ምሕረተ ሚካኤል ፅንስት ዘበዘያንጸበርቅ ሥና፥ • ኵሉ ይትሜነይ ይጸወና፥ • ጊዜ ወሊዶታ ድሕረ አልጸቀ ለእመ ኢረከበት ዳሕና፥ • ወለእመ ኢቆመት በጥዒና፥ • ውስተ ቤተ ሐኪም ትሑር እንዘ ሀለወት በፍና፥ • ወለደቶ ማእከለ ፍኖት ለባሕራን ህፃና። ዐሠረ ነጋሢ • ኦ #መልአክ ዘልማድከ #ዘሐይለ_ማርያም ትሕትና፥ • አስምዐነ ለነ #ዘበርተሎሜዎስ ዜና፥ • በዘማርያም ቅድስና፥ • ወትንቢተ #ዕንባቆም ንስማዕ #እምገብረ_ሐና፥ • ጸግወነ ንጹሀ ልቡና። ➖▪➖ • ሠኔ ፲፪/፳፻፲፰ ዓ/ም • ርእሰ አድባራት ወገዳማት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል • ጊዜ ፮ ሰዓተ ሌሊት • መጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ በውጪ ሀገር ያሉ ቅኔ ለመማር፦ የሚከተለውን ሊንክ ጠቅ አድርገው በመግባት መመዝገብ ይችላሉ፦ https://t.me/kineyared ቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/yaredzer
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
እኅታችን ከነልጇ በጀርመናዊ ማርቲን ሉተር ከተመሠረተው ቤተ እምነት ወጥታ ንጹሕ የወንጌልን ቃል ተምራ ዛሬ ሠኔ ፯/፳፻፲፰ ዓ/ም በድሬዳዋ መካነ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዐተ ጥምቀት መሠረት ተጠምቃ የሥላሴን ልጅነት አግኝታለች። ፍቅርተ ሥላሴ ወለተ ሥላሴ በሚል ዐዲስ ስመ ክርስትናም እናትና ልጅ ተጠርተዋል። "ወብየ ካልኣትኒ አባግዕ እለ ኢኮና እምዝንቱ ዐጸድ ወኪያሆንሂ ሀለወኒ አምጽኦን = ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፥ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል።" ዮሐ. ፲፡፲፮
ሃይማኖተ አበው ፹፫፡፳፭-፵፬
"እለ ውስተ ሞቅሕ አድሕን ወለኵልነ ኩን ጸወነ።"
видео или голосовое, без подписи
ቅዱስ ጳውሎስም “አገልግሎታችን እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም” ሲል ምክንያት እየፈጠርን ከመንፈሳዊ ሕይወትና ከአገልግሎት ወደ ኋላ ማለት እንደሌለብን አስተምሮናል። ፪ ቆሮ. ፮፥፫። በጾም ወቅት መጸለይ፣ መመጽወትና መስገድ በጾም የምናገኘውን ዋጋ ከፍ ያደርገዋል። ሁላችንም ጾሙን በደስታና በፍቅር ጾመን በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስን እናገኝ ዘንድ የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የቅዱሳን አባቶቻችንና የቅዱሳት እናቶቻችን ምልጃና ጸሎት አይለየን! አሜን! “ንጹም ጾመ ወናፍቅር ቢጸነ ወንትፋቀር በበይናቲነ - ጾምን እንጹም! ፤ እርስ በርሳችንም እንዋደድ!” ቅዱስ ያሬድ