Addis Ababa Health Bureau / አዲስ አበባ ጤና ቢሮ / AACAHB /
Статистикаጤና ለሁሉም !! ይህ ቻናል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ጤና ጣቢያ ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የጤና መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡
- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 87
- Всего постов
- 135
- Тип
- открытый
- Язык
- am
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 12 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 1 312
- 1/48двое суток
- 1 503
- 1/72трое суток
- 1 621
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ 6 መቶ ለሚሆኑ የህግ ታራሚዎች የክረምት በጎ ፍቃድ የነፃ ህክምና አገልግሎት ሰጠ። አ/አ ጤና ቢሮ ነሀሴ 8 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ በሚገኙ ጤና ተቋማት እየሰጠ ያለውን በክረምት በጎ ፈቃድ ነጻ ህክምና አገልግሎት በተጠናከረ መልኩ እየሰጠ ይገኛል ። በዛሬው እለት የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በሸገር ሲቲ ማረሚያ ቤት ለሚገኙ 6 መቶ ለሚሆኑ የህግ ታራሚዎች ነፃ የህክምና አገልግሎት መስጠቱን ገልጿል ። የነፃ ህክምና አገልግሎቱን የህክምና የህክምና ቡድኑ ወደ ማረሚያ ቤቱ በመሄድ ለታራሚዎቹ የተለያዩ የምርመራ እና ህክምና አድርጓል። ሆስፒታሉ ሁለት ሚልዮን ብር የሚገመቱ መድሃኒቶች እና የንጽህና መጠበቂያዎችን ለታራሚዎቹ ድጋፍ ሰጥቷል ። የሸገር ሲቲ ማረሚያ ቤት ዋና ኮሚሽን ኮሚሽነር ዋንጋሪ ጫላ በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ የተሳተፉትን የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ባለሙያዎችና ሰራተኞች ላደረጉት የሰብዓዊነት ተግባር ምስጋና በማቅረብ፣ድጋፉ ለተቋማቸው ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልፀዋል። የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የህንፃ አስተዳደር ኃላፊ አቶ ፊራፊስ በተቋሙ የሚከናወኑ የማህበረሰብ ተኮር አገልግሎቶች የሆስፒታሉ ማህበራዊ ሀላፊነት አካል መሆናቸውን ገልፀው በተለያዩ የበጎ ፍቃድ መርሃ ግብሮች በመሳተፍ ለማህበረሰቡ የሚችለውን አስተዋፅኦ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። የነፃ የህክምና አገልግሎቱን ያገኙ ታራሚዎችም በተደረገላቸው አገልግሎትና ድጋፍ አመስግነዋል። የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ከተቋሙ ውጭ በማረሚያ ቤቱ በመሄድ የነፃ ህክምና አገልግሎት መስጠት መቻሉ ፈትሀዊ የጤና ተደራሽ በማድረግ የዜጎችን እኩል ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ሰብአዊ ተግባር መሆኑም ተመላክቷል። “ጤና ለሁሉም፣ አገልግሎት በበጎ ፍቃድ፣ ሰብዓዊነት በተግባር!”
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
የአፍ እና ጥርስ ጤና አጠባበቅ ነሐሴ 8/2018 ዓ.ም የአፍ ውስጥ ጤና ከጠቅላላ ጤንነታችን ጋር በቀጥታ የተያያዘ መሆኑን ያውቃሉ? የጥርስ ሀኪም የሆኑት ዶክተር ኢዩኤል ገብሬ ከአዲስ ሚዲያ ኔትወርክ ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ የአፍ ውስጥ ጤናን መጠበቅ ከጠቅላላ ጤንነታችን ጋር በቀጥታ የተያያዘ መሆኑን አብራርተዋል። የጥርስ እና ምላስ ንጽህናን መጠበቅ፤ የጥርስ ንጽህና ሳይጠበቅ ሲቀር ጥርሶች ሊቦረቡሩ እና ለተለያዩ የድድ በሽታዎች ተጋላጭ ሊሆኑ ይችላሉ። ከጥርስ ባለፈ ምላስን በጽዳት አለመያዝ ፈንገሶች እንዲከማቹና ለከፍተኛ የአፍ ጠረን መነሻ ምክንያት ይሆናል። ትክክለኛው የጥርስ ማጽጃ ዘዴዎች፤ ጥርስን በቀን ሁለቴ ማፅዳት እንደሚገባ የገለጹት ዶክተር ኢዮኤል፣ በተለይም ማታ ሳያጸዱ መተኛት በባክቴሪያ መራባት ምክንያት ለአፍ ጠረን እና ለጥርስ መቦርቦር እንደሚያጋልጥ ያብራራሉ። የጥርስ ብሩሽን አጠቃቀም በተመለከተ ሲያስረዱም፣ የጀርባውን ክፍል በ45 ዲግሪ በማዘንበል፣ የፊት ለፊቱን በክብ፣ እንዲሁም የውስጥ ክፍሎችን ከታች ወደ ላይ በማድረግ በተገቢው ማጽዳት እንደሚገባ ይናገራሉ። የአፍ ጤና እጥረት የሚያስከትላቸው የጤና ችግሮች፡ በአፍ ውስጥ የሚፈጠሩ ኢንፌክሽኖችና የጥርስ ችግሮች በደም ዝውውር አማካኝነት ወደ ልብ፣ የስኳር በሽታ እና እስከ ስትሮክ ሊያደርሱ እንደሚችሉ ዶክተር ኢዩኤል አስገንዝበዋል። ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምልክቶች፤ ውሃ በሚጠጡበት ጊዜ ጥርስን መጥዘጥዘት፣ እንዲሁም በጥርሶች ጥግ ጥግ ላይ ሻህላ መፈጠር የችግሩ መጀመሪያ መገለጫዎች በመሆናቸው ወዲያውኑ ወደ ክሊኒክ በመሄድ መታየት እንደሚያስፈልግም ዶክተሩ ያስረዳሉ። የጥርስ ህክምና አማራጮች፤ እንደ ችግሩ ከባድነት የጥርስ እጥበት፣ ሙሌት፣ የሰርቪካል ህክምና፣ የሰው ሰራሽ ጥርስ መተካት እንዲሁም በብሬስ ወይም በኢንቪዝብል አለይነር አማካኝነት የጥርስ አቀማመጥን ማስተካከል ይቻላል። መከላከያ መንገዶች፤ ጣፋጭ ምግቦችን ሲመገቡ የአፍ ውስጥ ንጽህናን በአግባቡ መጠበቅ፣ በቤት ውስጥ ተገቢውን የንጽህና ልምድ ማዳበር እና በዓመት እስከ ሁለት ጊዜ ወደ ክሊኒክ በመሄድ የጥርስ እጥበት ማከናወን ለአፍ ጤና መረጋገጥ ትልቅ ሚና እንዳለውም አስገንዝበዋል። AMN-
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи