ተግባራዊ ክርስትና
Статистика{ ከቅዱሳን ሕይወት ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን } "" ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ፤ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ ! "" /ያዕ 1÷22/
- Последний пост
- 9 авг.
- Последнее чтение
- 13 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 20
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 1 125
- 1/48двое суток
- 1 289
- 1/72трое суток
- 1 390
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
https://youtu.be/vOgbA_qLqfo?si=kCejsc-PEYn86w0g
አቤል ይባላል የግቢ ጉባኤያችን አባልና የ12ኛ ክፍል ተማሪ ነው። አሁን ግን እንደምትመለከቱት አደጋ አጋጥሞት የእኛን እርዳታ ይፈልጋልና የምንችለውን ያህል ከላይ በተጠቀሱት አካውንቶች በመላክ እናግዘው። ማጋራትም እርዳታ ነውና ይህን ፖስት ለምናውቃቸው ሰዎች በማድረስ እነርሱም እንዲያግዙ እናድርግ። CBE: 1000348860538 Telebirr: 0911398024 / 0931534451
✝ በእንተ ሱባኤ ! ሱባኤ በሰዋስው ትርጉሙ ሰባት ማለት ነው ፡፡ ሰባት ቁጥር በእስራኤላውያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው ፡፡ እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረት ፈጥሮ አጠናቋል ፡፡ ‹‹እግዚአብሔርም የሠራውን ሥራ በሰባተኛው ቀን ፈጸመ›› እንዲል /ዘፍ.2፥2/ ፡፡ ቅዱስ ዳዊትም ‹‹ስለ ጽድቅህ ፍርድ ሰባት ጊዜ በቀን አመሰግንሃለሁ›› በማለት ለጸሎት የሚተጉ ምእመናን በቀን ለሰባት ጊዜ እግዚአብሔርን ማመስገናቸው እንዳለባቸው ይመክራል /መዝ.118፥164/ ፡፡ ሱባኤ በመንፈሳዊ ትርጉሙም አንድ ሰው ከዚህ ቀን እስከዚህ ቀን በጸሎት ከፈጣሪዬ እገናኛለሁ ብሎ የሚያቅደው መንፈሳዊ እቅድ ነው ፡፡ ከዚህ አንጻር አንድ ሰው ለሰባት ቀናት ቢጾም «አንድ ሱባኤ ጾመ» ለዐሥራ አራት ቀን ቢጾም «ሁለት ሱባኤ ጾመ» ይባላል ፡፡ ሱባኤ የተጀመረው ከውድቀት በኋላ በመጀመሪያው ሰው በአዳም ነው ፡፡ አዳም በገነት ሰባት ዓመት ከአንድ ወር ከዐሥራ ሰባት ቀን በደስታ ከኖረ በኋላ ሕግ አፍርሶ የፈጣሪውን ቃል ጥሶ ከገነት ወጥቷል ፡፡ መልሶ ፈጣሪው እንዲታረቀው ሠላሣ አምስት ቀን ሱባኤ ገብቷል ፡፡ በመጨረሻም ‹‹በሐሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ ወእደኅከ ውሰተ መርሀብከ›› ብሎ ተስፋውን ሰጠው ፡፡ ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ አዳም ጥፋቱን አምኖ ከባሕር ውስጥ ሱባኤ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔር በማይታበል ቃሉ «ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንኀለሁ» ሲል ቃል ኪዳን ገብቶለታል ፡፡ እንሆ የ2018 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታ ነገ (ዕለተ አርብ ነሐሴ 1 ቀን) ይጀምራል ። የቻልን ጠዋት በኪዳን ከሰዓት በውዳሴ ማርያም ትርጓሜ እና በቅዳሴ ተገኝተን እናስቀድስ ። በሥራና በትምህርት ያልቻልን ደግሞ ሌሊት ኪዳን በማድረስ እናሳልፍ እላለሁኝ ። መልካም ሱባኤ 🕊 JOIN @Applied_CHRISTIANITY
✝ የቱ ይሻላል ? "እወዳችኋለሁ" ማለት ቀላል ሲሆን ፣ ከባዱ ደግሞ ያንን በሕይወት ማሳየቱ ነው ፡፡ ሌሎችን መተቸት ቀላል ሲሆን ፣ ራስን ማሻሻል ደግሞ ከባድ ነው ፡፡ ስህተት መሥራት ቀላል ሲሆን ፣ ከዚያ መማሩ ደግሞ ብርታትን ይጠይቃል ፡፡ ስላጣነው ፍቅር ማንባቱ ቀላል ሲሆን ፣ ላለማጣት መንከባከቡ ግን ይከብደናል ፡፡ መቀበል እጅግ ቀላል ሲሆን ፣ መስጠት ደግሞ ልባዊ ርኅራኄን ይጠይቃል ፡፡ ስለ መሻሻል ማሰብ ቀላል ሲሆን፣ ከባዱ ግን ወደ ተግባር መቀየሩ ላይ ነው ፡፡ ቀላሉ ሳያገናዝቡ ማውራት ሲሆን ፣ ከባዱ ደግሞ ምላስን መግታት ነው ፡፡ የሚወደንን ሰው መጉዳት ቀላል ሲሆን ፣ የሚከብደው ደግሞ ያንን ቁስል ማዳኑ ነው ፡፡ ሌሎችን ይቅር ማለት ቀላል ሲሆን ፣ ይቅርታን መጠየቅ ግን ከባድ ነገር ነው ፡፡ ሕግጋትን ማውጣት ቀላል ሲሆን ፣ እነርሱን መከተሉ ደግሞ ከባድ ነገር ነው ፡፡ ቀላሉ በእያንዳንዱ ምሽት ማለሙ ሲሆን ፣ ከባዱ ደግሞ ለስኬታማነቱ መዋጋት ነው ፡፡ ወዳጅነትን በቃላት መጠበቁ ቀላል ሲሆን ፣ ትርጉማቸውን መጠበቁ ግን ከባድ ነገር ነው ፡፡ ልጅ እያለን ከሰማናቸው ነገሮች መካከል አንዱ በአካባቢያችን ውሻ ሲያላዝን (የተለየ ድምጽ ሲያሰማ) "'ሰው ሊሞት ነው'" የሚለው አባባል ነው ፤ እጅግ በሚገርም ሁኔታ ግን "እኔ ልሞት ነው" የሚል ያለመኖሩ ጉዳይ ነው ፤ በተለይ አልጋ የያዙ ካሉ የሰዉ ሁሉ ትኩረት መጠቋቆሚያ የመኾናቸው ጉዳይ አጠያያቂ አይሆንም ፡፡ ግን የቱ ይሻላል? ሰውን ማስተካከል ወይስ ራስን ማስተካከል ፤ እነርሱ ልክ አይደሉም ማለት ወይስ እኔ ልክ አይደለሁም ማለት ፤ የሌሎችን ስህተት መዳኘት ወይስ የራስን ድካም መታገል ፤ የቱ ይሻላል? JOIN @Applied_CHRISTIANITY
✝ ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ! #አዘጋጅ ፦ « ቤተ ዝማሬ መንፈሳዊ የዜማ መሳሪያዎች ማሰልጠኛ ተቋም » ለበለጠ መረጃ 📞 +251942177012 📞 +251995975237
✉️ "" ተሸክሞህ ይሄዳል ! "" JOIN @Applied_CHRISTIANITY
✝ ወደ ክርስቶስ መገስገስ የማወቅ ጥማትህ እግዚአብሔርን ለማወቅ የማይፈልግ ከሆነ ከንቱ ነው ፡፡ ስለ ምድር አውቀህ ስለ ሰማይ ዝንጉ ከሆንህ ፣ ስለሚጠፋው እንቅልፍ አጥተህ ስለማይጠፋው ከደነዘዝህ በእውነት ከንቱ ነህ ፡፡ የሚያውቀህን አምላክ ትተህ የማያውቁህን ዝነኞች ስታስስ መዋል ፣ ገና ፈሳሽ ሳለህ ሳትረጋ ያወቀህን ጌታ ገሸሽ ብለህ የካዱህን ስታስብ መኖር ፣ ወላጆችህ ሳያዩህ በዓይነ ምሕረት ያየህን እግዚአብሔር አለማየት ፣ ዓለም ሳይፈጠር የመረጠህን ምርጫህ አለማድረግ በእውነት ከንቱ ነው ፡፡ "ደስታ የሌለው እውቀት ፣ ዕረፍት የሌለው ጥበብ እግዚአብሔርን ማወቅ የሌለበት ነው ፡፡" JOIN @Applied_CHRISTIANITY
[ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ]
Live stream finished (1 hour)
እግዚአብሔርን እያገለገሉ ከእግዚአብሔር መራቅ ፣ እጅግ ይከብዳል ። እንደ መርፌ የሌሎችን ቀዳዳ ሸፍኖ የራስን ችላ ማለት ይከብዳል ። JOIN @Applied_CHRISTIANITY
❖ ከዚህ ምስል ምን ተረዳችሁ ? JOIN @Applied_CHRISTIANITY
"" ብዙ ማገልግላችን ፣ መጸለያችን ፣ መጾማችንና መማራችን ሌሎችን ለመውቀስ ምክንያት ከሆነን ቆም ብለን እራሳችንን መፈተሽ አለብን ። "" JOIN @Applied_CHRISTIANITY
"" አገልግሎታችን ተቀባይነት የሚኖረው ለሰው ሳይሆን ለእግዚአብሔር ብለን ስናደርገው ነው ። "" JOIN @Applied_CHRISTIANITY
እንዴት አመሻችሁ ? ጉባኤ ተጀምሯል እንግባ !
Live stream started
✝ ፍጻሜዬን አሳምረው ! የምትኖርበት ገንዘብ ባይኖርህ እንኳ የምትሞትለት ዓላማ (ሃይማኖት) ይኑርህ ፣ የነገሠም የበለፀገም መጨረሻው "ሞተ" ነው ፣ በክርስቶስ ያመነ ግን ሕያው ነው ። የመጽሐፍ ፍሬ አሳቡ የሚገኘው ማጠቃለያው ላይ ነው ፣ አንተም ጀማሬህ ብቻ ሳይሆን ፍጻሜህ ከመድኃኔዓለም ጋር እንዲሆን አጥብቀህ ጸልይ ። ወዳጄ ! ዛሬን ባርኮ የሰጠህ እርሱ ነው ። አመስግነው! JOIN @Applied_CHRISTIANITY
✝ "" እስቲ ልሞክረው ፣ ምን ያደርጋል ብለን የገባንበት ኃጢአት ብዙ ነው ። JOIN @Applied_CHRISTIANITY
✝ አመሰግንሃለሁ ! ጌታ ሆይ ! ያልገቡኝ ነገሮች ቢኖሩም አንተ ግን መልሴ ነህ ፣ ዝም ያሰኙኝ ነገሮች አያሌ ቢሆኑም እንደ ፈቃድህ ብዬ ትቻቸዋለሁ ። ንጹሕ ያልኩት ምንጭ ሲደፈርስ ምንድነው ምክንያቱ ብልም አንተ ግን ነፍሴን መልሰህ ታሳርፋታለህ ። እውነተኞች ሲደናቀፉ ፣ የጻድቃን መከራ ሲበዛ ምን ዓይነት ዓለም ነው? ብልም አንተ ግን ራስህን እይ ትለኛለህ ። ጌታ ሆይ ! ስለገቡኝና ስላልገቡኝ ነገሮች ሁሉ አመሰግንሃለሁ ። JOIN @Applied_CHRISTIANITY
видео или голосовое, без подписи
✝ "" የማያልፈው ምንድነው? መልሱ ፦ የእግዚአብሔር መንግሥት ነው ።