Ethiopian Shipping and Logistics
Статистика- Последний пост
- 12 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 1
- Всего постов
- 51
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 797
- 1/48двое суток
- 913
- 1/72трое суток
- 985
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
#ESL Leading the Green Legacy: Planting Hope, Growing the Future.
#አዲሱን ሳምንት ለመልካም ተነሳሽነት፣ ለላቀ ውጤታማነትና ለዘላቂ ስኬት! ለኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አመራሮችና ሰራተኞች ሳምንቱ የመልካም ተነሳሽነት፣የትጋትና የውጤታማት እንዲሆን እንመኛለን፡፡ ለክቡራን ለደንበኞቻችንም ሳምንቱ የስኬትና የፍሬያማነት እንዲሆን ምኞታችን ነው፡፡ አብረን በመሥራት፣ የተሻለ አገልግሎትን በመስጠትና እሴትን በመፍጠር፣ ከባሕር ባሻገር ያለውን ዕድል እንገነባለን! የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ #EthiopianShippingAndLogistics #ESL #BeyondTheSea #መልካም ሳምንት
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
*ኢባትሎ ዓመታዊ የሠራተኞች ጉባዔውን አካሄደ* የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ (ኢባትሎ) የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈጻጸምና የ2019 ዓ.ም ዋና ዋና ዕቅዶች ላይ ያተኮረ ዓመታዊ የሠራተኞች ጉባዔ በአዲስ አበባ እና በተለያዩ ቅርንጫፎች አካሄደ። ዝግጅቱን ከማእከል ሆነው በሁሉም ቅርንጫፎች በብሮድካስት ያስጀመሩት የኢባትሎ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አብዱልበር ሸምሱ (ኢ/ር) ፤ ድርጅቱ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ያስመዘገበው የላቀ ውጤት በመላው አመራርና ሠራተኞች ትጋትና ቁርጠኝነት የተገኘ መሆኑን ገልጸው፣ በመጪው አመት የተሻለ ውጤት ለማምጣት ሁሉም የድርጅት ሰራተኞች ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል። በዚህ አመት በልዩ ሁኔታ፤ በሆርሙዝ ሰርጥ አካባቢ በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት ፈታኝ ሁኔታዎችን ተቋቁመው ተልዕኳቸውን ሲወጡ ለነበሩት የጊቤ መርከብ ባሕረኞች የዕውቅና መርሃ ግብር ተካሂዷል። በአዲስ አበባ፣ ጅቡቲ፣ ሞጆ፣ ድሬዳዋ፣ ባሕርዳር፣ ኮምቦልቻ፣ መቀሌ፣ ሰመራና ወረታ በተካሄደው ጉባዔ ወደ 2,500 የሚጠጉ አመራሮችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል።
без подписи
без подписи
без подписи
ኢባትሎ እና ኢትዮ ኢንጂነሪንግ የረጅም ጊዜ የሥራ ግንኙነታቸውን ወደ ተሻለ ትብብር ለማሸጋገር ተስማሙ የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ እና ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ከዚህ ቀደም በነበራቸው የሥራ ግንኙነት የተነሱ የፋይናንስ ጉዳዮችን በሁለቱም ወገኖች ተቀባይነት ባለው አግባብ ለመፍታት መግባባት ላይ ደርሰዋል። በኢባትሎ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ እና በኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ሸጋው ሙሉጌታ መሪነት በተካሄደው ውይይት፣ ለረጅም ጊዜ ሲካሄድበት የቆየውን ጉዳይ ወደ መፍትሔ ለማምጣት በሚያስችል አሠራር ላይ መግባባት ተችሏል። ኢትዮ ኢንጂነሪንግ የኢባትሎ ቁልፍ አጋር እንደሆነ የገለፁት ኢንጅነር አብዱልበር ፤ ይህንንም በሚያሳይ አግባብ በቀጣይነት በልዩ ሁኔታ አብረው የሚሰሩበት አሰራር በቅርቡ እንደሚመቻች ጠቁመዋል።
የባቦጋያ ማሪታይምና ሎጅስቲክስ አካዳሚ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ እና የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ - ግብር አከናወነ:: በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የባቦጋያ ማሪታይምና ሎጅስቲክስ አካዳሚ የ2018 የክረምት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ የመትከል መርሀ - ግብር እና ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የሚውል የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉን አቶ ሲራጅ አብዱላሂ የባቦጋያ ማሪታይምና ሎጅስቲክስ አካዳሚ ዲን ገለጹ። እንደ አቶ ሲራጅ ገለጻ በዛሬው ዕለት 500 ሀገር በቀል ችግኞች የተተከሉ ሲሆን አካዳሚው ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ በንቃት በመሳተፍ ከችግኝ ተከላ ባለፈ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ፣ የተራቆቱ መሬቶችን በደን በመሸፈን እና የአካባቢ ስነ-ምህዳርን በማጠናከር የሀገሪቱን የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ በተግባር እየደገፈ መሆኑን አስረድተዋል። በዚህ የችግኝ ተከላ መርሀ - ግብር ላይ ከአካዳሚው አመራርና ሠራተኞች በተጨማሪ በወቅቱ ስልጠና ላይ የሚገኙ ሰልጣኞች፣ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር የሆራ አርሰዲ ወረዳ አመራሮች እና በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚሰጡ ወጣቶች ተሳታፊ ሆነዋል:: ከዚህ በተጨማሪም የአካዳሚው ሠራተኞችና አመራሮች በበጎ ፈቃድ በመሳተፍ ከ71 ሽ ብር በላይ ወጪ በማድረግ በአካባቢው ለሚገኙ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የሚውል 100 ደርዘን ደብተር እና 10 ፓኮ እስክርቢቶ ድጋፍ ተደርጓል:: ይህ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በቀጣይም በደም ልገሳ መርሀ-ግብር ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ ተገልጿል::
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи