መሠረተ ግእዝ | Meserete Ge'ez
Статистикаየሀገራችን ቀዳማዊና ጥንታዊ ስለሆነው የግእዝ ቋንቋ መሠረታዊ ትምህርት የሚሰጥበት ቦታ ነው። እርስዎም አባቶቻችን ያቆዩልንን ቋንቋ በመማርና ለትውልድ በማስተላለፍ ኃላፊነትዎን ይወጡ። ለጥያቄና አስተያየት - @geezchanal
- Последний пост
- 10 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 1
- Всего постов
- 23
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Книги (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 1 291
- 1/48двое суток
- 1 479
- 1/72трое суток
- 1 595
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ወርኃ ነሐሴ - የነሐሴ ወር ነሐሴ “አናሕሰየ" ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ አቀለለ ፣ አቃለለ ፣ ተወ ፣ አሳለፈ ፣ ይቅር አለ ማለት ነው ። ነሐሴ በቁሙ “ናሴ"የመጨረሻ ወር ፤ ከአሥራ ሦስቱ ወራት አሥራ ኹለተኛ ወር ነው ። ነሐሴ ፬ ፳፻፲፰ ዓ.ም ዕለተ ሰኑይ @meseretegeez
የግዕዝ ፈደልና ቁጥር መማሪያ
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
https://youtu.be/we9bap92cdM
ወርኃ ሐምሌ - የሐምሌ ወር ሐምሌ “ሐመለ" ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ ለቀመ ማለት ነው ። ሐምሌ ሐመለ ፣ ለመለመ ፣ የልምላሜ ወር ፤ ሐምል ጎመን የሚበላበት ፣ ልምላሜ የሚታይበት ወር ነው ። (ሕያው ልሳን መዝገበ ቃላት) ሐምሌ በቁሙ የወር ስም ከአሥራ ሦስቱ ወራት አሥራ አንደኛው ወር ሲሆን በሠኔ እና ነሐሴ መኃል ይገኛል ። አሕመልመለ - ለመለመ ሐመልማል - ለምለም ሐመልሚል - የለመለመ ሐመልማለ ወርቅ - የወርቅ ሽቦ (ቅጠል) ሐመልማለ ዘርዕ - ቡቃያ ፣ ተዘርቶ የሚበቅል (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ) ሐምሌ ፩ ፳፻፲፰ ዓ.ም ዕለተ ሠሉስ @meseretegeez
መዝሙር ዘሰንበት ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ሶበ ይዘንም ዝናም ይትፌሥሑ ነዳያን ሶበ ይዘንም ዝናም ይጸግቡ ርኁባን ወሠርዐ ሰንበተ ለሰብእ ዕረፍተ ደምፀ እገሪሁ ለዝናም ደምፀ እገሪሁ ለዝናም። ትርጕም፦ የዝናም እግሩ ተሰማ ዝናም በሚዘንም ጊዜ ነዳያን ደስ ይሰኛሉ ዝናም በሚዘንም ጊዜ የተራቡ ይጠግባሉ ለሰው ዕረፍት ሰንበትን ሠራ የዝናም እግሩ ተሰማ። @meseretegeez
без подписи
без подписи
ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያየ የትምህርት መርሐግብራት ያስተማራቸውን 562 ደቀ መዛሙርት በማስመረቅ ላይ ይገኛል ------- በመርሐ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተገኝተው ለተመራቂዎች አባታዊ ቡራኬ በመስጠት ላይ ይገኛሉ። በተጨማሪም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ በርካታ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ እንዲሁም የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች፣ የዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደርና መምህራን፣ የተመራቂ ተማሪዎች ቤተሰቦች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በታዳሚነት ተገኝተዋል። ይህ መርሐ ግብር የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች የነበራቸውን የመማር ማስተማር ሂደት አጠናቀው፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ እና በሀገሪቱ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ነው። በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ የዩኒቨርሲቲው የሥራ ኃላፊዎች፣ ተመራቂዎች ለቤተ ክርስቲያን እና ለሀገር ያላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ መልእክት እያስተላለፉ ይገኛሉ። @MesereteGeez
ክረምት ፦ ማለት ከረመ ካለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም (ክራማት፣አክረመ፣ምክራም) ወርኃ ዝናም፣ ወርኃ ነጎድጓድ፣ ዘመነ ባሕር፣ ዘመነ አፍላግ፣ ዘመነ ጠል፣ ዘመነ ደመና፣ ዘመነ መብረቅ ማለት ነው። የክረምት ወቅት ከሰኔ ፳፮ ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም ፳፭ ቀን ድረስ ነው። ደምፀ እገሪሁ ለዝናም @MesereteGeez
ከ300 ዓመታት በፊት ከዕብራይስጥ ወደ ግእዝ የተተረጎመው የኦሪት ብራና መጽሐፍ ለቅዱስነታቸው ተበረከተ #Ethiopia | በኢትዮጵያ ቤተ እስራኤላውያን ታሪክ ላይ ከ40 ዓመታት በላይ ጥናት ያደረጉት እስራኤላዊው የታሪክ ጸሐፊ ራቢ ማናኼም ዋልድማን፣ ከዕብራይስጥ ቋንቋ በቀጥታ ወደ ግእዝ የተተረጎመና 300 ዓመታት ገደማ ዕድሜ ያለው የኦሪት ብራና መጽሐፍ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ በስጦታ አበርክተዋል። ይህ አዲስ ግኝት ቀደም ሲል ከጎንደር አካባቢ ወደ እስራኤል ከተጓዙት ቤተ እስራኤላዊው አባ ሳሙኤል ንጉሤ የተገኘ ሲሆን፣ አምስቱን ብሔረ ኦሪት ያካተተ ነው። መጽሐፉ ይፋ ከመደረጉ በፊት በዘርፉ ምሁራን ታይቶ ከግሪክ ወደ ግእዝ ከተተረጎመው የኦሪት መጽሐፍ ጋር የተመሰከረ ሲሆን፣ በአማርኛ፣ በዕብራይስጥና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች መግቢያ ተዘጋጅቶለት በዲጂታል መልክም እንዲቀመጥ ተደርጓል። ይህ ታሪካዊ ግኝት የኢትዮጵያን የ3000 ዘመን ታሪክ የሚያረጋግጥና ቤተክርስቲያኗ "ከዕብራይስጥ የተተረጎሙ መጻሕፍት አሉኝ" ለምትለው ትልቅ ሕያው ምስክር መሆኑን የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አሥኪያጅ ንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ ገልጸዋል። ራቢ ዋልድማን የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ በቀጥታ ከዕብራይስጥ ወደ ግእዝ ተተርጉሞ ሲገኝ ይህ የመጀመሪያው መሆኑንና ይህም በኦሪትና በክርስትና እምነት መካከል ያለውን ጥብቅ ግንኙነት እንደሚያሳይ ተናግረዋል። ቅዱስ ፓትርያርኩም የተደረገውን ጥናትና ስጦታ በማድነቅ፣ ግኝቱ የሁለቱን ሕዝቦች የረጅም ዘመን ታሪካዊ ትስስር ይበልጥ እንደሚያጠናክር ገልጸው ለጸሐፊው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት-
በኢ/ኦ/ተ/ቤ ምግባረ ሠናይ ጠቅላላ ሆስፒታል
ለክረምት ሥልጠና ፈላጊዎች በሙሉ በመጪው ክረምት የአብነት ትምህርት ኦንላይን መሠልጠን የምትፈልጉ በሙሉ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ እንገልጻለን ። ፩. የግእዝ ቋንቋ ለጀማሪዎች ፪. የቃል ትምህርት (ውዳሴ ማርያም ፣ መዝሙረ ዳዊት) ለመመዝገብ ፦ @geezchanal
без подписи
без подписи
без подписи