Yeshua Apologetics Ministry
Статистика➟የሹዋ ዐቅበተ እምነት አገልግሎት አላማ ከክርስትና እምነት አንጻር ደርዛቸውን የጠበቁ ስነ መለኮታዊ ፍልስፍና፤ አመክንዮአዊና ታሪካዊ ጽሑፎችን ማቅረብ በክርስትና ላይ የሚነሱ የተቃውሞ ሀሳቦችንና የኑፋቄ ትምህርቶችን መመከት የሌላውን እምነተ መርህ ከሎጂክና ከታሪካዊ ዳራዎች አንጻር መመርመር ▼ @Yeshua_Apologetics_Ministry ▲
- Последний пост
- 11 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 22
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Книги (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 970
- 1/48двое суток
- 1 111
- 1/72трое суток
- 1 198
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
stop asking me what's wrong in DMs lol if u want to know what im going through kafka's already written it 😁 beteley ante sewuye @YApolog
без подписи
« የእግዚአብሔር ፍትሐዊነት እና እከይ» እግዚአብሔር ሁሉን ቻይ፣ ሁሉን አዋቂ እና ፍጹም ቸር ከሆነ፣ ለምን ክፋትና መከራ እንዲኖር ይፈቅዳል? አልቪን ፕላንቲንጋ ቲዎዲሲ[¹] "እግዚአብሔር እከይ እንዲኖር ለምን እንደሚፈቅድ ለሚነሳው ጥያቄ የሚሰጥ ምላሽ ነው" ብሎ ይናገራል።[²] ብዙ አሳቢያን እንዲሁም የቤተክርስቲያን አበው በእግዚአብሔር ፍትሐዊነት እና በእከይ ሕላዌ መካከል ስላለው ግንኙነት ብዙ የፍልስፍና ሞዴሎችን ሲያዋቅሩ ሲጠይቁ እና ሲያንሰላስሉ እንመለከታለን። ጆን ሂክ የተባለ እንግሊዛዊ ፈላስፋ በ1966 ባሳተመው እከይና የፍቅር አምላክ /Evil and the God of Love በተሰኘው መጽሐፉ ለእከይ ጣጣ/PoE በታሪክ መዛግብት መሐል የተሰጡ ክርስቲያናዊ ምላሾችን በመቃኘት ሦስት ዋና ዋና የቴዎዲሲ ሞዴሎችን ያስቀምጥልናል፤ እነርሱም ፕሎቲኒያዊ /Plotinian፣ አውግስጢኖሳዊ /Augustinian እና ሔሬኔዎሳዊ/ Irenaean አቀራረቦችን በንጽረተ ሐቲት ለማቅረብ ይሞክራል።[³] እርሱም መለስ ብሎ soul-making theodicyን ሞዴል ተጠቅሞ የእከይን ሕላዌ ከእግዚአብሔር አምላክ ፍትሐዊነት እና መልካምነት ጋር ለማነጻጸር ይሞክራል። ብቻ ምን አለፋችሁ የሰው ልጅ ካለው ነባራዊ እውነታ በመነሳት እነዚህን ተጻራሪ መሳይ እውነታዎች ለማስታረቅ እና በመሐላቸው የጋራ መስመርን ለማስመር ይታገላሉ። በውኑ እግዚአብሔር ፍትሐዊ አምላክ ነውን? አዎ በእርግጥ እርሱ ፍጹም ጻድቅ ፍትህ ምንነቱ የሆነ አምላክ ነው። ታዳ ክፋት በምድር በፈጠረው ፍጥረት ላይ ሲነግሥ ስለምን ዝም ይላል? በእርግጥ ሁሉን አዋቂ ከሆነስ ምን እንደሚፈጠር እያወቀ ለምን ሥቃይ በፍጥረቱ ላይ እንዲደርስ ፈቀደ? ደግሞስ እርሱ ፍጹም ቸር ከሆነ፣ ምንም ዓይነት ዓላማ በፍጥረታቱ ላይ የሌለው የሚመስል መከራን ለምን እንዲኖር ፈቀደ? ዛሬ እንድንጠይቅ የፈለኩት ዝም ብለን "እከይ ለምን ይኖራል?" የሚል ረቂቅ የፍልስፍና ጥያቄን ብቻ አይደለም፤ ነገር ግን ከዛ በዘለለ ሁኔታ "ለምን እኔ/ ጋር መድረስ አስፈለገው?' የሚልን የእኔነት ጥያቄን ነው። ለምን ንጹሐን ሕፃናት መከራ መቀበል አስፈለጋቸው? ለምን የምንወደው ሰው መሞት ነበረበት? ጸሎቶቻችንስ ለምን የማይሰሙ እስከሚመስለን ድረስ በዝምታ ውስጥ ሊያልፉ አስፈለጋቸው? ምናልባት አሁን እኛ ከምናየው ባሻገር ያሉ ምክንያቶች ይኖሩ ይሆናል፤ ነገር ግን እኛ ካለንበትና ከመከራው ሸክም በታች ሆነን ስንመለከተው የእግዚአብሔር ቸርነት የተሰወረ ይመስለናል፣ ዝምታውም ሊሸከሙት የማይችሉት መሪር ቀንበር ይሆንብኛል። ስለዚህ በተጠቂነት ጥልቅ ጩኸት ውስጥ "ጌታችን ፈጣሪያችን ሆይ እከይ በሕይወታችን ውስጥ እንዴት ሊኖር ቻለ?" የሚል ብቻ ሳይሆን "በጣም በፈለግንህ ጊዜ የት ነበርክ?" የሚለው ይበልጡን በውስጣችን የሚመላለሰው ጥያቄ ይሆናል። ምናልባትም የእከይ ሕላዌ ጥያቄ ከክርክር እና ፍልስፍናዊነት በላይ የሚሆነው እዚህ ጋር ነው፤ ኃያል አምላክ፣ ኩሉን አዋቂ፣ ፍጹም ቸር የሆነው እና አፍቃሬ ኩሉ አምላክ አሁንም በዚህ ጨለማ ዓለም ውስጥ መኖሩን ለማወቅ የሚፈልግ የቆሰለ ሰው ጩኸት ይሆናል። አንዳንድ ጊዜ ጥያቄዎች ከፍልስፍናዊ ሙግት ባለፈ በሰው ልጅ ስሜትና ሥቃይ መነጽር ወይም ደግሞ ሊገልጹት ከሚችሉት በላይ መከራን ካዩ ሰዎች ዝምታ ከነገሠበት ልብ ውስጥ ጥያቄዎች ይፈጠራሉ። እኔ በህይወቴ በብዙ የውስጥና የውጭ ስሜቶች መሐል አጣብቂኝ ውስጥ ገብቼ አውቃለሁ። ካለሁበትም የውስጥ ስሜት የሐሳብ ፍጭት ለመውጣትም ከእኔው ጋር እጅጉን ስሟገት ራሴን አገኘዋለሁ፤ ግን አንዳንዴ ነገሮች ከአቅማችን በላይ ሊሆኑ ይችላሉ። ለዚህም ነው መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊት "እግዚአብሔርን ማመስገን መልካም ነው(92:1)" ብሎ የዘመረው የአንዳንድ ጥያቄዎቻችን መልሶች በእግዚአብሔር ዘንድ ናቸው። እርሱንም ስለሆነውም ስላልሆነውም ማመስገን ከሁሉም በላይ በላጩ ቁም ነገር እርሱ ነው። በዝምታ ውስጥ መልስን የሚሰጥ አምላክ ነውና በሚቀጥለው የቴዎዲሲን ንድፈ ሐሳቦችን ለመቃኘት እንሞክራለን ወስብሃት ለአብ። @Yeshua_Apologetics_Ministry 🔖ማጣቀሻዎች [¹] • ቴዎዲሲ /theodicy የሚለው ቃል የመጣው ቴዎስ /θεός አምላክ እና ዲኬ /δίκη ፍትሕ/ፍርድ ከሚሉ ሁለት የግሪክ ቃላት የተዋቀረ ሲሆን በዓለም ላይ እከይ/ክፋትና መከራ መኖሩ እየታወቀ የእግዚአብሔርን ቸርነት፣ ፍትሐዊነትና መለኮታዊ ጥበቃን ለማረጋገጥ፣ ለመከላከል ወይም ለማሳየት የሚደረግ ፍልስፍናዊ ወይም ሥነ መለኮታዊ ጥረት ነው። [²] • Plantinga, Alvin (1974). God, Freedom, and Evil. pg. 10 [³] • Evil and the God of Love by J. Hick
ከአኳይናስ እግር ስር የተደፋው ኢብን ሩሽድ/አቬሮስ ነው
❝ እስልምናዊ ፍልስፍና እና የምዕራቡ አለም እሳቤ ተጽዕኖ ❞ ሰሞኑን ፊታችንን ወደ እስልምና ፍልስፍና፣ ዲበአካላዊ ትንታኔ እና አመክንዮን በምዕራባውያኑ አሳቢያን መነጸር ለመቃኘት እንሞክራለን በተለይም የእነ አል ኪንዲ፣ አል ፈራቢ፣ ኢብን ሲና (በላቲናውያን ዘንድ አቪሴና ተብሎ ይጠራል)፣ ታላቁ የኢስላም ፈላስፋ አቡ ሐሚድ ሙሐመድ አል ጋዛሊን እና የኢብኑ ሩሽድ(በላቲኑ አቬሮስ)ን ፍልስፍና ከአመክንዮ ጋር እያዋዛን እንቃኛለን። በተለይ ትኩረቴን በሳበው ሙስሊሙ ፈላስፋ የአቬሮስ በ11ኛው መ/ክ/ዘ ለተጻፈው ለአል ጋዛሊ "ታሃፉት አል ፈላሲፋ/the incoherence of the philosophers" ለሚለው መጽሐፍ ምላሽ የሚሆን መጽሐፍን ጽፎ ነበር (the incoherence of incoherence)፤ ይህም መጽሐፍ በአልጋዛሊ ላይ የተሰነዘረ አመክንዮአዊ ፍልስፈና አዘል በጣም ጠንካራ ትችት ነው ብንል ማጋነን አይሆንብንም። አቬሮስ የአሪስጣጣሊስን አመክንዮና ፍልስፍናን ያቀበ፣ ኮሜንታሪዎችን ያዘጋጀ ብቻ ሳይሆን እንደነ አቪሴና(ኢብን ሲና) እና አል ፈራቢ ፍልስፍናን በእስልምናው አስተምህሮ ለማስረጽ የሞከረም ፈላስፋ ነበር። በላቲኑ ትውፊት ላይም በአሪስጣጣሊስ ስራዎች ላይ ባደረጋቸው ሰፊ ትንታኔዎች አማካኝነት ትልቅ ተጽዕኖ መፍጠር ችሎ ነበር። በላቲኑ ንጽሮተ አለም ብዙ ጊዜ አሪስጣጣሊስን ፈላስፋው/philosophus ብለው እንደሚጠሩት ሁሉ አቬሮስን ደሞ ተንታኙ የሚልን ስያሜ ተሰጠው፤ ይህም ደሞ ላቲኖቹ ለትንታኔዎቹ ምን ያህል ቦታ እና ግምት እንደሰጡት አንዱ ማሳያ ነው። ይህንን ተከትሎ ላቲናዊ አቬሮይዝም በመባል የሚታወቀው የእሳቤ ንቅናቄ ማስነሳት ችሎም ነበር። እንደ ሲገር ኦፍ ብራባንት እና የዳሲያው ቦይቲየስ ያሉ አሳቢያን ፍልስፍናዊ ትንታኔዎችን ለመጠየቅና ለማንሳት የአሪስጣጣሊሳዊ እና አቬሮይስታዊ መርሆችን ተጠቅመዋል። የአቬሮይስቶች እሳቤ ከክርስትና መሠረታዊ አስተምህሮዎች ጋር (creation ex nihilo, individual human immortality, divine providence, and God's freedom) ለመስማማት አስቸጋሪ መስለው በመታየታቸው ከፍተኛ ውዝግብን በወቅቱ አስነስተው ነበር። ይህ በላቲናውያን ዘንድ የተፈጠረው ውጥረት መሠረት በማድረግ በ1270 የፓሪሱ ጳጳስ ኤቲየን ቴምፒየር ከቤተክርስቲያኑ አስተምህሮ ጋር ይጋጫሉ ያላቸውን 15 መሠረተ ትምህርቶች (አቬሮይስታዊ የሆኑትን) አወገዘ። በ1277 ደግሞ በሊቀ ጳጳስ ዮሐንስ 21ኛ ጥያቄ፣ ቴምፒየር በዋነኝነት ከአሪስጣጣሊስ እና ከኢብን ሩሽድ ትምህርቶች የተወሰዱ 219 ነጥቦችን በድጋሚ አወገዘ። ምንም እንኳ የተወገዙት ሐሳቦች በሙሉ በቀጥታ የኢብን ሩሽድ ትምህርቶች ባይሆኑም በወቅቱ በፓሪስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ይሰራጩ የነበሩ የአሪስጣጣሊስ እና የኢብን ሩሽድ ፍልስፍናዎችን የሚመለከቱ ነበሩ። በ13ኛው ክፍለ ዘመን ግንባር ቀደም የካቶሊክ አሳቢ የነበረው ቶማስ አኳይናስ አሪስጣጣሊስን ለመረዳት የኢብን ሩሽድ ትርጓሜዎች እና ትንተናዎች ላይ ድጋፉን ቢሰጥም፤ በብዙ ነጥቦች ላይ ግን አልተስማማውም ነበር። ለምሳሌ ያክል the doctrine of a single intellect shared by all human beings, the eternity of the world as a philosophically necessary conclusion, እና የአቬሮናውያንን divine providence ክፉኛ ይቃወም ነበር። ግን ከቶማስ አኳይናስ በጣም የምወድለት ባህሪው አንዱ በመካከለኛው ክፍለ ዘመን ያለውን ስኮላስቲሲዝም ዝምብሎ መቃወም ወይም መቀበል ሳይሆን critical appropriation ተጠቅሞ አጥርቶ እና መርጦ የመውረስ እሳቤውን ነው። ከዚህም በመነሳት አኳይናስ አሪስጣጣሊሳዊ ሜታፊዚክስን በክርስትና መዋቅር ውስጥ በማስገባት፣ እግዚአብሔር ቀዳማዊ ምክንያት/causa prima ሲሆን፣ ፍጥረታት ደግሞ ሁለተኛ ደረጃ ምክንያቶች/ causae secundae መሆናቸውን፣ እና የሰው ነፍስ የእያንዳንዱ ግለሰብ መሠረታዊ ቅርጽ መሆኗን አብራርቶ አቬሮይዝምን እንቅስቃሴ በጥንቃቄ ሲተች እንመለከታለን። በ1270 እና በ1277 በካቶሊክ ቤተክርስቲያን የተሰጡት ውግዘቶች እና በአኳይናስ የቀረበው ፍልስፍናዊና ክርስትናዊ መር ትችቶች አቬሮይዝም በላቲን ክርስትና ውስጥ ያለውን ስርጭት አዳክመውት ነበር። ይሁን እንጂ የአውሮፓ አስተሳሰብ ከአሪስጣጣሊሳዊነት መራቅ እስከጀመረበት እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ተከታዮች ነበሩት። በቀጣዮቹ ክፍለ ዘመናት ከነበሩት ታዋቂ አቬሮይስቶች መካከል 14ኛው ክፍለ ዘመን ጆን ኦፍ ጃንዱን እና ማርሲሊየስ ኦፍ ፓዱዋ፣ 15ኛው ክፍለ ዘመን ደሞ እነ ጋኤታኖ ዳ ቲየን እና ፒዬትሮ ፖምፖናዚ እንዲሁም 16ኛው ክፍለ ዘመን አጎስቲኖ ኒፎ እና ማርካንቶኒዮ ዚማራ ይጠቀሳሉ። 🔖ዋቢ መጽሐፍት፦ [¹] •GREAT ISLAMIC THINKERS፡ Averroes (Ibn Rushd): His Life, Works, and Influence by MAJID FAKHRY [¹] •PHILOSOPHY IN THE ISLAMIC WORLD: A History of Philosophy without any gaps volume 3 by PETER ADAMSON @Yeshua_Apologetics_Ministry
без подписи
pre Islamic period ጊዜ ነገደ ቁረይሽ በመካ ሐራም ውስጥ ካካተቱዋቸው ጣዖታት ውስጥ ታላቁ አምላክ ሁበል፣ ኢሳፍ፣ ናኢላ በbattle of elephant ጊዜ በAbraha ላይ ለቁረይሾች ድልን የሰጣቸው አላህ የሚባለው ጣኦት ከሶስቱ ሴት አማልክት ጋር ይገኛል። መሐመድ አላህ ብሎ የሚጠራው አምላክ እንደነ ስኮት ጆንሰን እና ሌሎች ምሁራን ጥናት መሠረት ከመሐመድ በፊት የሚኖሩ መድብለ አማልክት አምላኪዎች ዘንድ የሚመለክ ጣኦት እንደነበር ታሪካዊና አርኪዮሎጂያዊ ማስረጃዎችን ያቀርባሉ። መሐመድ ወደ መካ ሲገባ ሁሉን ጣኦታት ካስወገደ በኋላ አላህን ሲያስቀረው እንመለከታለን። ለነገሩ ሁበል በጊዜው ሙሉ ለሙሉ ከእስልምና አልወጣም ነበር፤ አንዳንድ ነገሮችን ለምሳሌ ጧዕፍ ማድረግን፣ በመስጂዶች ሚናራና ጉልላቶቻቸው ላይ የሚጠቀሟቸው የኮከብ እና የጨረቃ ምልክት እና ለአምላካቸው የሚሰግዱበት ትውፊት ከሁበል አምላኪዎች የተኮረጀ እንደሆነ እንመለአታለን። ስለሁበል ከዚህ በፊት የጻፍኩትን መጣጥፍ ይሄንን ተጭናችሁ ማግኘት ትችላላችሁ @Yeshua_Apologetics_Ministry
без подписи
« የተዋሕዶ ንድፈ ሐሳብ (theoria unionis)» the metaphysics of the Incarnation በእንተ ስጋዌ ዲበአካላዊ «ሁለት እውነታዎች ያለ ምንም ተጨማሪ "ህልውናዊ ትስስር/ ontological bond" ውህደትን ማስገኘት ይችላሉን? » የሚለው ጥያቄ ተዋህዶን/union ለሚያቀነቅኑን ሊቃውንቶች ማለትም እነ ቦናቬንቸር፣ ስኮተስና ናታሊስን ብንጠይቃቸው መልሳቸው አይችልም ነው። ለምሳሌ በእንተ ስጋዌ ዘተዋህዶ መለኮታዊው አካል(divine person) እና ሰብአዊው ባህሪይ (human nature) ለመዋሐድ የግድ ሶስተኛ መካከለኛ ግንኙነት አስፈላጊ እንደሆነ ያስረዳሉ፦ ቃል ←→ የተዋሕዶ ግንኙነት ←→ ሰብአዊ ባሕርይ ይህ ግንኙነት በሐሳብ ደረጃ (conceptual) ብቻ ያለ አይደለም ይልቁንም እውናዊ/real እና በትክክልም ህልው የሆነ ነው። ሐሳቡን በደንብ ለመረዳት አንድ ምሳሌ እንመልከት ለምሳሌ "ሀ" እና "ለ" ብለን ሁለት የጊዜ ሁኔታዎችን እንውሰድና ሁለት ዐዋጆችን እንመልከት፦ በጊዜ "ሀ" ላይ ሰብአዊው ባሕርይ ከቃል ጋር ተዋሕዷል ብለን እናስብ በጊዜ "ለ" ላይ ደሞ ሰብአዊው ባሕርይ አልተዋሐደም ከሚሉት ዐዋጆች ተነስተን በእነዚህ በሁለቱ ተጻራሪ መሠረታውያን ዘንድ ልዩነቱ ወይም ለውጡ ምንድነው ብለን ብንጠይቅ፣ ቃሉም ሆነ ሰብአዊው ባሕርይ ራሳቸውን ሆነው ሳይለወጡ ከቀጠሉ፣ በሜታፊዚክሱ መሠረት ይህን ተዋሕዶ እንዲኖር ወይም እውን የሚያደርግ ሌላ ሦስተኛ ነገር መኖር አለበት። ካልሆነ ግን ተዋሕዶ በሆነ ጊዜ ኖሮ በሌላ ጊዜ ደሞ የማይኖርበትን ምክንያት ማስረዳት የሚቻል አይደለም። ይህ የእነስኮተስ መሠረታዊ ሜታፊዚክሳዊ የሙግት ሐሳብ ነው።[1] ሌላ ምሳሌ ከዊልያም ኦካም (William of Ockham) ከሃይሎሞርፊካዊ ቅንብር (hylomorphic composition) ንድፈ ሐሳቡ[2] ተውሰን ይህን theory ለማዳበር እንሞክር፦ ለምሳሌ እንዲህ ብለን እናስብ ነፍስ እና ሥጋ አሉ እንበል፤ ያው በተለመደው ሁኔታ የነፍስ እና የሥጋ ጥምረት ሕያው ሰውነት ነው። እግዚአብሔር በታምራት ነፍስን ከሞት በኋላ በነበረችበት ስፍራ በትክክል እንድትቆይ አደረገ እንበል፣ ምንም ዓይነት የቦታ ለውጥ ባልተደረገበት ሁኔታ እግዚአብሔር አምላክ ነፍስ ሥጋን ሕያው ማድረጓን (informing) እንድታቆም ቢያደርጋት፤ በዚህ ሁኔታ ላይ የመደረግና ያለመደረግን ልዩነቱን የሚያስረዳው መሠረታዊ አንድምታ ምንድን ነው? ነፍስም አለች፣ ሥጋም አለ፣ ቦታውም አልተለወጠም። ስለሆነም የሆነ ተጨማሪ ነገር መጥፋት ወይም መለወጥ አለበት። ኦካም ከዚህ በመነሳት እውናዊ ግንኙነት (real relation) መጥፋት ወይም ለውጥን ከእሱ ተነስተን መናገር አለብን የሚልን ድምዳሜ ያስቀምጣል።[3] ስለዚህ ጥምረቱ የቁስ(Matter)፣ ቅርጽ (Form) እና የተዋሕዶ ግንኙነት (Union Relation) ነው እንጂ፤ ዝም ብሎ ቁስ + ቅርጽ ብቻ አይደለም። ከዚህ በመነሳት ወደ ነገረ ክርስቶሳዊው አንድምታ እንመለስና ቃል በሆነ ጊዜ ከስጋ ጋር ያልተዋሐደበትን ኑባሬ እና በሆነ ጊዜ በስጋዌ (incarnation) አማካኝነት በተዋሐደበት በእነዚህ በሁለት ክስተቶች መሐል ያለው የልዩነት ምክንያት ለማስረዳት መሠረት የሚሆነን እውናዊ ግንኙነት (real relation) መኖሩ ላይ ነው። ስለሆነም እነ ስኮተስ ሰብአዊ ባሕርይ + የተዋሕዶ ግንኙነት + መለኮታዊ አካል የተዋሕዶ ጽንሰ ሐሳብ (Union Theory) ቀመር አድርገው ይወስዱታል። ይቀጥላል...... 🔖ማጣቀሻዎች [¹] The Physics of Duns Scotus: The Scientific Context of a Theological Vision (Oxford: Clarendon Press, 1998), 82–9. [²] hylomorphic composition የምንለው ቁስን እና ቅርጽን መሠረት ያደረገ የአካል አወቃቀር ንድፈ ሐሳብ ነው ያው የአርስጣጣሊሳዊ ቶማሳዊ የሐይሎሞርፊዝም እሳቤ ከኦካም እና ስኮተስ የተለየ እሳቤ ነው ያለው አንድ አካል የተገነባው ከሁለት ውስጣዊ መርሆች ብቻ ነው፤ እነርሱም ቁስ/matter እና ቅርጽ/form ናቸው ሌላ ምንም ነገር አያስፈልግም ቅርጹ ቁሱን በቀጥታ እውን ያደርገዋል የሚል እሳቤ ነው ያላቸው በቀጣይ በሰፊው እንመለስበታለን [³] Ockham, Ordinatio, Book I, Distinction 30, Question 4. የመግቢያው ሐቲት ማስፈንጠሪያ በእንተ ስጋዌ ከዲበአካላዊ ትንታኔ አንጻር @Yeshua_Apologetics_Ministry
የLive ቆይታ ርዕስ፦ ጥንታዊው የሥላሴ ትምህርት፡ ሥልታዊ እና ሜታፊዚካዊ ትንተና ሊንክ፦ https://youtube.com/watch?v=Y0o2YHLNfLs&si=jwCzpd8O2P1pAqjS @Yeshua_Apologetics_Ministry
без подписи
ታሪክ ምናምን ለሚመቻችሁ አንድ መጽሐፍ ልጋብዛችሁ 😊 የቦልድዊን 4ኛ ዘእየሩሳሌም ንጉሥ ብዙ ጊዜ ለምጻሙ ንጉስ እየተባለ ይጠራል በተለይ ከመስቀል ጦርነቶች ታሪክ ውስጥ እጅግ ከሚታወቁት ውጊያዎች መሐል አንዱ የሞንትጊዛርድ ጦርነት (Battle of Montgisard) ነበር ቁጥሩ ላይ ውዝግብ ቢኖርም ግን በብዙ እጥፍ የሚበልጠውን የታላቁን የሙስሊሙ ግዛት መሪ የሰላዲንን ጦር አሸንፎ እስከ ግብጽ ድረስ እንዳባረረ በርናንድ ሃሚልተን ይናገራል እንደውም ብዙ የታሪክ አጥኚዎች ሰላዲን ወደ ካይሮ ሲመለስ ከጦርነቱ በኋላ የተረፈው ጦረኛ አንድ አስረኛው ብቻ እንደሆነ ይናገራሉ። ቦልድዊን 4ኛ በሕይወት ዘመኑ በኢየሩሳሌም የክርስትናውን እና የመንግስቱን ግዛት ያስጠበቀ ወጣቱ ለምጻሙ መሪ በመባል ይታወቅ ነበር፤ ብቻ አንብቡት ታሪክን ማወቅ ጥሩ ነው ያው እኔ ቦልድዊን ታሪክ ስሰማ ሳነብ ምናምን ስለምደነቅበት ነው መጽሐፉን ከታች አስቀምጠዋለሁ @Yeshua_Apologetics_Ministry
«የፍቅር ልዕልና በዶስቶየቭስኪ» ዶስቶየቭስኪ ለፍቅር ያለው ግንዛቤ ትኩረቱን ከአፍላጦናዊው ምጡቅነት ወደ ሰው ልጅ ህልውናዊ ክብር/existential dignity በማሸጋገር ይበልጥ ጠሊቅ ያደርገዋል። እውነተኛ ፍቅር ማለት ሌላውን ሰው እግዚአብሔር ሊያየው እንደፈለገው ወይም እንዲሆን እንዳሰበው አድርጎ ማየት ነው የሚለው አባባሉ በሰው ልጆች ግንኙነት ውስጥ መለኮታዊ ገጽታን ሲያስገባ እንመለከታለን። የሰው ልጅ በሚታይ ሁኔታው፣ በሥነ ልቦናዊ ውስንነቱ ወይም በሥነ ምግባር ውድቀቱ ባለው ነገር (ቁሳቁስ ቤት፣ መኪና ገንዘብንም ያካትታል 😁) ብቻ የሚመዘን አይደለም፤ ምክንያቱም ሰው በአምሳለ መለኮት/imago Dei የተፈጠረ እና ይህን ማንነቱ ማናቸውም ሁኔታዎች የማያጠፉበት ልዩ ፍጡር ነው። ስለዚህ እውነተኛ ፍቅር ስሜታዊ ከመሆኑ በፊት የእዚህ መሠረት ክሂል ነው። ይህም ግለሰቡን በታሪክ አጋጣሚዎች፣ በሥነ ልቦናዊ ጠባሳዎች/trauma ወይም በውድቀቱ ብቻ ለመለካት ፈቃደኛ ያልሆነ የማወቂያ መንገድ ነው። ተራ እይታ አሁን ያለውን እውነታ ብቻ ሲያስተውል ፍቅር ግን ሊሆን የሚችለውን ሁናቴ ያስተውላል፤ ተራ ምልከታ አሁን ባለው ሁኔታ ሲፈርድ ፍቅር ግን ግለሰቡ ሊደርስበት የሚገባውን ግብ/telos ይመለከታል። የዶስቶየቭስኪ የፍቅር እይታ ጥልቅ ሥነ መለኮታዊ የሆነው ለዚህ ነው። ይህም ፍጥረታትን ባሉበት ሁኔታ ብቻ ሳይሆን ሊደርሱበት በሚገባቸው የመጨረሻ ጥሪ መሠረት ከሚመለከተው ከመለኮታዊ ዕይታ ጋር በአምሳያነት ስለሚሳተፍ ነው። ስለሆነም ፍቅር ስለ ተወዳጁ ጉድለቶች የሐሰት ቅዠትን አይፈጥርም፤ ይልቁንም እነዚያን ጉድለቶች ሰብሮ በመግባት ከጉድለቶቹ በፊት የነበረውንና ከእነርሱም በላይ የሆነውን ህልውናዊ ክብር/ontological dignity ይረዳል። @Yeshua_Apologetics_Ministry
ሰላም ተወዳጆች በዐቀብተ እምነት አገልግሎት ውስጥ ለረጅም ጊዜ የቆየውና የእውነት ለሁሉ ዌብሳይት መሥራችና አርታዒ ወንድማችን ዳንኤል የዶክትሬት ትምህርቱን ለማጠናቀቅ የእናንተን እርዳታ ያስፈልገዋል። አገልግሎቱን የምትወዱ ሁሉ ከጎኑ እንድትቆሙ በታላቅ ትህትና እንለምናችኋለን። በድርጅት መርዳት የምትችሉና ኦፊሴላዊ ደብዳቤ የምትፈልጉ በውስጥ ብታነጋግሩን ከላኪ ድርጅት ደብዳቤ ማቅረብ እንችላለን። በዚህ የgofundme ገጽ( ይሄንን ሊንክ ይጫኑ ) በመግባት የምትችሉትን እንድታደርጉ መልካም ፈቃዳችሁ ይሁን። ከሀገር ውስጥ መርዳት ለምትፈልጉ በውስጥ ወንድማችን ዳንኤልን በዚህ የቴሌግራም አድራሻ ማነጋገር ትችላላችሁ @danit4all ተባረኩ! @Yeshua_Apologetics_Ministry
без подписи
«ፍቅር ከባድ የአእምሮ በሽታ ነው» ፍቅር ዝም ብሎ በግርድፉ ስነ ልቦናዊ ስሜት ወይም ስሜታዊ ትስስር ብቻ አይደለም፣ ይልቁንም በረቀቀ ደረጃ የሰውን ልጅ የኑሮ ዘይቤ መሠረታዊ በሆነ መልኩ የሚቀይር ህልውናዊ ክስተት ነው። ከአፍላጦን እስከ አውግስጢኖስ፣ ከኪርክጋርድ እስከ ዶስቶየቭስኪ ያሉ ታላላቅ የፍልስፍና ትውፊታዊ ወጎች ፍቅርን የሚያስረዱት «እኔነትን የሚያናጋ ሁናቴ» አድርገው ነው። ምክንያቱም ፍቅር ራሱን የቻለ እኔነት በራሱ ተብቃቂ ነው የሚለውን ቅዠት ገሀድ ያወጣል። አፍላጦን «ፍቅር ከባድ የአእምሮ በሽታ ነው» ማለቱ በዘመናዊው የሥነ አእምሮ ሕክምና ትርጉም እንደ በሽታ ሊወሰድ አይገባም፤ ይልቁንም «መለኮታዊ እብደት /theia mania» ተብሎ ለሚጠራው ሁናቴ የተሰጠ እውቅና ነው። ይህም የዘልማዱ ንቃተ ህሊናችን ከፍ ባለ እውናዊ ዓለም ውስጥ በሚሳተፍበት ጊዜ የሚስተዋል ሁኔታ ነው። በፌድረስ መጽሐፉ አፍላጦን ይህንን መለኮታዊ እብደት ከተራ እብደት ይለየዋል። ተራ እብደት አመክንዮን የሚበታትን ሲሆን መለኮታዊ እብደት ግን አመክንዮን ከውስን አድማሱ በላይ ወደ ውበት (ቶ ካሎን/τὸ καλόν) ራሱ ከፍ ያደርገዋል። ስለዚህ ፍቅር/Eros ዲበ አካላዊ ረብሻ ነው፤ ምክንያቱም የታጠረውን ራስ ተኮር ህልውና ሰብሮ የነፍስን ዘላለማዊ አምሳያዎች የማስታወስ/anamnesis ብቃት ስለሚቀሰቅስ ነው። ተወዳጁ አካል ዝም ብሎ እንደ አንድ ውስን ነገር የሚፈለግ ሳይሆን ነፍስ በዚያ በኩል ምጡቁን የውበት አምሳያ የምታይበት መገለጫ ይሆናል። ስለዚህ እውነተኛ ፍቅር መሠረቱ ሌላውን ሰው የራስ ማድረግ ሳይሆን በስሜት ህዋሳት ከሚታወቅ ውበት ወደ ረቂቁ የውበት ምንጭ የሚደረግ እርገት ወይም ከፍታ ነው ። ይህ የአፍላጦን እይታ ፍቅር ለinstrumental reason ለምን ምክንያታዊ ያልሆነ መስሎ እንደሚታይ ያሳያል። ዘመናዊው አመክንዮአዊነት ቅድመ ግምትን፣ ሚዛናዊነትንና ቁጥጥርን ይፈልጋል። ፍቅር ግን ያልታሰቡ ክስተቶችን፣ ተጋላጭነትንና ሊቆጣጠሩት ለማይችሉት ነገር ክፍት መሆንን ያስከትላል። እኔነት የሚኖረው ድንበሮችን በማበጀት ራስን ከሌላው በመለየትና የገዛ ራሱን ወጥነት በመጠበቅ ነው፤ ፍቅር ግን የእነዚህ ድንበሮች ህልውናዊ ስብራት ነው። ሌላውን መውደድ ማለት የሌላኛውን ሰው ህልውና የራስ ማንነት መሠረታዊ አካል እንዲሆን መፍቀድ ማለት ነው። ከፍልስፍና አንጻር ይህ ከተነጠለ አካልነት ወደ ተያያዥ ህልውና/relational being የሚደረግ ሽግግርን ይወክላል። ግለሰቡ ከዚያ በኋላ ለራሱ ብቻ አይኖርም፤ ይልቁንም ወደ ሌላኛው አቅጣጫ ፊቱን ያዞራል። በዚህ ትርጉም ፍቅር ግለሰቡን ከማዕከልነት የሚያወጣ ዲበአካላዊ ክስተት ነው። የፍቅር እብደት የሚገኘውም ሌላውን ሰው ዝም ብሎ ለመገልገያነት ሳይሆን በባሕርዩ አስፈላጊ እንደሆነ አድርጎ እንዲቆጥር በማስገደዱ ነው። ለዚህም ነው አፍላጦን ፍቅር እኔነት ራሱን ለመጠበቅ ያለውን ተፈጥሮአዊ ስሜት የሚንድ ነው ብሎ የሚፈርጀው። @Yeshua_Apologetics_Ministry
🤔🤔 @Yeshua_Apologetics_Ministry
ሱራ 15:9 እና የቁርኣን አጠባበቅ ጽሑፍ፦ በSamuel Green ትርጉም፦ በDavid Yeshua እውን በሱራ15:9 እንደምንመለከተው አላህ ቁርኣንን ከመረሳት ይጠብቀዋል ማለት ነውን? በፍጹም አይደለም፤ ምክንያቱም.... ሙሉውን ጽሑፍ ያንብቡ፦ ➔ https://yeshuaapologeticsministry.org/surah-15-and-the-preservation-of-the-quran/ መልካም ንባብ። @Yeshua_Apologetics_Ministry
ሳሙኤል ግሪንም በፌስቡክ ገጹ ለቆታል። ጸሐፊው ሙሉ ለሙሉ ሌሎቹንም የእሱን ስራዎችን ጨምሮ ተርጉሜ እንድጠቀማቸው መፍቀዱ ለእኔ ትልቅ ነገር ነው። አሁን ይሄ አንዱ ስራ ነው፣ ሌሎቹን ስራዎቹን እየተረጎምኩኝ እገኛለሁ። በዚህም ጌታ ይርዳኝ! የፌስቡክ ገጹ➔ https://www.facebook.com/share/19NatXuyr6/ ፎሎ አድርጉት፣ በሙስሊሞች ላይ እና በባርት ሄርማን ላይ እየሰሩት ያሉት ስራ በጣም የሚበረታታ ነው። ትጠቀሙበታላችሁ። @Yeshua_Apologetics_Ministry
አርጌንስ እና የአዲስ ኪዳን ጥንታዊ ቅጂዎች ጽሑፍ፦ Samuel Green ትርጉም፦ David Yeshua ------ ይህ መጣጥፍ፣ በሊቁ አርጌንስ ድርሳን ውስጥ ስለ አዲስ ኪዳን የሰፈረውን ንግግር መሠረት በማድረግ የሚያብራራ እና በሙስሊሞች መካከል ለሚደረገው ውይይት እንዴት በጥቅም ላይ መዋል እንዳለበት የሚተነትን ነው።.....ሙሉውን ጽሑፉን ለማንበብ፦ ➔ https://yeshuaapologeticsministry.org/origen-and-the-text-of-the-new-testament/ መልካም ንባብ። @Yeshua_Apologetics_Ministry