tgindex
አስተምረኝ ጌታዬ ሆይ

አስተምረኝ ጌታዬ ሆይ

Статистика

. 🇼 🇪 🇱 🇨 🇴 🇲 🇪 #በዚህ_መንፈሳዊ_ቻናል ☞︎︎︎ የእግዚአብሔር ቃል ዳሰሳ፣ ☞︎︎︎ አስተማሪ ታሪኮች፣ ☞︎︎︎ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ጥያቄዎች፣ ☞︎︎ መንፈሳዊ ግጥሞች ይቀርባሉ። #የእግዚአብሔር_ቃል_በሙላት_ይኑርባችሁ ◈●ቆላስይስ 3፥16●◈ ➥ @astemiren_bot ➥ @from_jesus_to_jesus

Последний пост
23 мая 2025 г.
Последнее чтение
13 авг.
Постов за неделю
0
Всего постов
21
Тип
открытый
Язык
ti
В каталоге с
13 авг.
Подписчики
1 249
−1 за 1 дн.
Сутки
0
0,00%
Неделя
 
Месяц
 
Просмотров на пост
734
21 постов
Вовлечённость
58,8%
к подписчикам
Постов в день
0,0
всего 21
Упоминаний
0
каналов
Охват размещения
оценка
1/24сутки в ленте
1/48двое суток
1/72трое суток

Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.

Посты

  • አጠገቤ ነህ ጌታ አጠገቤ ዘልቀህ ገብተሀል ከውስጥ ከልቤ ውጪውን አይቶ ልቤ እንዳይሰጋ እርፍ አለ በአንተ ተረጋጋ እሩቅ አይደለህም ካለሁበት አለህ እስከምድር ጫፍ ብሄድ ቀድመህ ትገኛለህ ፍጥረት ባንተ አብሮ የለህም ብትባል ምስክር አልሻም ስራህ ይናገራል          ዘማሪ ተከስተ ጌትነት ❇️ ሀይማኖት እግዚአብሔርን በጣም ሩቅ በሰማይ ያለ የሰዎችን ስሜት መረዳት እንደማይችል ቀሳፊ መአተኛ ተቆጪ አድርጎ ነው የሚስልብህ ጌታ ካልበራልህ በስተቀር በዚህ ተውጠህ ነው የምትኖረው ይሄንን መዝሙር ልዩ የሚያደርገው እግዚአብሔር የቅርብ ወዳጅ እንደሆነ እንዲሰማን የሚያደርግ እኔ በበኩሌ ብሰማው የማልጠግበው ድንቅ መዝሙር ነው! መንፈስ ቅዱስ በመካከላችን መኖሩ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንደሆነ እና የዘላለም ሕይወታችን አስተማማኝ እንደሆነ የሚያረጋግጥ ጥኡም ሁሌም አብሮን ያለ አባታችን ነው እግዚአብሔርመንፈስ ቅዱስ ክብር ይገባሀል!! ሀሌሉያያያ

  • 17 мая 2025 г.920из christology_GC

    без подписи

  • 17 мая 2025 г.80882из christology_GC

    ገላትያ ም.1 ክፍል 5 የጳውሎስ የሕይወት ታሪክ የገላትያ ደብዳቤ፦ የአዲስ ኪዳን ዘጠነኛ የመልእክ ታት አራተኛ ነው። የጳውሎስ 6ቱ ምእራፎች * ምእራፍ 1እና 2 የጳውሎስን የሕይወት ታሪክ የያዙ ናቸው። 2ቱ ደግሞ ስነ መለኮትን ቀጣዮቹ ደግሞ ስነምግባርን *ጳውሎስ እስከ3 ፒኤችዲ እንዳለው ይገመት ነበረ። ማለትም ምንም እንኳን በዛን ዘመን የፒኤችዲ ት/ት ባይኖርም የዘንድሮውን ፒኤችዲ ሊያሟላ የሚችል የት/ት ደረጃ እንደነበረው ይነገራል። * ጳውሎስ ቤ/ንን ሙሉ በሙሉ ለመጥረግ የሚ ያስብና የሚሰራ ሠው ነበረ። *ከመለወጡ በፊት ተሳዳቢ፣ምሕረት የሌለው ጨካኝ ከሀጢአተኞች ዋና እንደነበረ በጢሞ1፥15 ላይ ራሱ ተናግሯል። * ጳውሎስ 613ቱንም ሕግ በቃሉ የሚያውቅና የሚጠብቅ ሰው ነበረ። በአመት 3ጊዜ አስራት ለመስጠት ለመስጠት ቤተመቅደስ የሚመጣ ሰው ነበረ። በቀን 3ቴ የሚጸልይ ነበረ። በጣም የሚጾም ሠው ነበረ። * ኤር49፥2፦ ኤር1፥5፦በማህጸን ሳልሰራህ አወቅሁህ ይላል ስለዚህም ጳውሎስ አይሁዳዊ እንደሆነ ብሉይን ያነብ እንደነበረ በዚህ ሌሎች ማረጋገጥ ይችላሉ። ከጳውሎስ ሕይወት የምንማራቸው ነገሮች፦ *የእግዚአብሔር ጥሪ በሰው ማንነትና በውለታ ላይ የተመሰረተ አይደለም። *ታማኝ የሆኑ ሰዎች እያሉ እግዚአብሔር አመጸኞችን መጠቀሙ የእግዚአብሔር ሉአላዊነት መገለጫ ነው። ጳውሎስ ከተለወጠ በሁዋላ፦ * አንድም ከራሱ ጋር ማውራት ማለትም ጌታ በዛ መንገድ በጠራራ ጸሀይ በብርሀን ተገናኝቶት ስለ ነበረ ጊዜ ወስዶ ማሰብ የሚጠይቅበት ሁኔታ ላይ ስለነበረ ነው። *ጳውሎስ ከሰዎች ጋር ከመነጋገሩ በፊት ከእግዚአብ ሔር ጋር መነጋገር ስለነበረበት ነው ኢየሩሳሌም ከመሄዱ በፊት ወደ አረብ ሀገር የሄደው። *ሶስት አመት ጸለየ፣አሰላሰለ ከዛም ወደ ኢየሩሳሌም 5 ጊዜ ሄዷል። * ጳውሎስ መጀመሪያ ወደ አረብ ሀገር ቀጥሎወደ ደማስቆ በመቀጠል ወደ ኢየሩሴሌም በመጨረሻም ወደ ሶሪያና ኪልቂያ ሄዷል። @christology_GC @christology_GC

  • без подписи

  • 14 мая 2025 г.67144из christology_GC

    ገላትያ ም.1 ክፍል 4 ገላ 1፥11-16 አሸባሪው ሳኦል ወደ ወንጌላዊው ሳኦል! * ከሐዋርያቱ የተለየ ወንጌል ነው የሚሰብከው በሚል የአይሁድ መምህራን የጳውሎስን ትምሕርት እንዳይቀበሉ ሰዎችን ያነሳሱና አገልግሎቱን ጥያቄ ምልክት ውስጥ ያስገቡ ስለነበረ እንዲሁም ከአይሁድ ጋር ጥላቻ ስላለበት ነው ይሄንን ትምሕ ርት የሚያስተምረው ይሉት ስለነበረ ያንን ለመከ ላከል ከሰው ሳይሆን በቀጥታ ከእግዚአብሄር ነው የተቀበልኩት ብሎ ራሱንና ትምሕርቱን በቁ.11 ለመከላከል ይሞክራል። በመገለጥ ከራሱ ከኢየሱስ እንደተቀበለው ይናገራል። * ጳውሎስ በመልእክቱ 2ጊዜ በሐዋርያት ስራ 3ጊዜ ስለ ራሱ የሕይወት ለውጥ ይናገር ነበር። ከጳውሎስ መለወጥ 4 የምንማራቸው ነገሮች * በምንም ዓይነት የሀጢአት ጥልቀት በየትኛውም አይነት ሁኔታ ውስጥ መሆንህ እግዚአብሄርን ከምሕረት የሚከለክለው አንዳች ነገር የለም። * በሕልውናው ፊት ማንም ሊቆም እንደማይችል እንገነዘባለን። * ለክብሩ ይጠቀምባችሁዋል!! * ጳውሎስ በተለወጠ በአንድ ሣምንት ውስጥ ሀናኒያ ወንድም ሲለው ከ1ሳምንት በፊት ወንድማ ቸው እስጢፋኖስን በአሰቃቂ ሁኔታ እንደገደለው በክርስቶስ ፍቅር ረስቶ ወንድም ሲለው እንመለ ከታለን። *ሙሴ የግብጽ ሰዎችን ነጻ እንዲያወጣ እንደተላከ ሁሉ በአዲስ ኪዳን እግዚአብሄር ከሀጢአት በጸጋው ነጻ ለማውጣት የተጠቀመበት የአዲስ ኪዳኑ ሙሴ ነው ይላሉ አንዳንዶች። ጌታ ለምን ደማስቆ ላይ ሊጠብቀው ፈለገ?? *ከኢየሩሳሌም ደማስቆ እስኪደርስ ድረስ 340ኪ.ሜ በዛን ጊዜ 1ሣምንት ይፈጅ ነበረ። ከምቾቱ እንደፈ ለገ ከሚያደርግበት ከኢየሩሳሌም ከለመደው Atmosphere እንዲወጣ አድርጎ በመገናኘት ሊለውጠው ፈልጎ ይሆናል ተብሎ ስለሚታሰብ። * ምናልባት በኢየሩሳሌም የመከራው እሳት ይነድ ስለነበረ በእምነት የሚፈለገውን ያህል የሚያጸናው ሰው በኢየሩሳሌም ሊገኝ ስለማይችል ወደ ደማስቆ እንዲመጣ አደረገው ልንል እንችላለን። @christology_GC @christology_GC

  • 13 мая 2025 г.5503из christology_GC

    የጸሎት ጊዜ 🗣የኢየሱስ ስም 🗣 በልሳን ውስጥ የሚያልፍ መንፈስ፣ሀይል፣ክብር @christology_GC @christology_GC

  • 10 мая 2025 г.6421из christology_GC

    "ሙሴና እስራኤል" 📌 ሙሴ ያለፈበት መንገድ ጠመ ዝማዛ ነበረ!! 📌ከሙሴ ግለ ታሪክ እግ/ር የተና ገራቸው ሰዎች ምን ይማራሉ?? @christology_GC @christology_GC

  • ለአንዲት እህት የተሠጠ ምላሽ 🎚24.2 MB🎚 📌 ንሠሀ ሣልገባ ብሞትስ?እድናለሁ? 📌 እንዴ የዳነ አማኝ ይጠፋል? ✍ 1ኛቆሮ3*10, ዕብራ10*14✍ ጥያቄዎቻችሁን በ@wbinu ላይ ማሥቀመጥ ትችላላችሁ @christology_GC @christology_GC

  • @christology_GC @christology_GC

  • 24 апр. 2025 г.80811из DessieChurchUnionYouth

    без подписи

  • 21 апр. 2025 г.7474из christology_GC

    без подписи

  • 19 апр. 2025 г.7374из christology_GC

    # የሀጢአት ዋጋ! * የሀጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤የእግዚአብሄር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየ ሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው።          (ሮሜ6፥23) * ኢየሱስ የከፈለውን ዋጋ የታመመውን ሕመም የተ ሰቃየውን ስቃይ ሳስብ አንድ ነገር ማስተዋል እጀምራለሁ ለሀጢአት የተከፈለውን ዋጋ! ሀጢአት ኢየሱስን ከሰማይ አወረደው ከክብሩ አወረደው! መዘባበቻና መቀለጃ አደረገው በሰዎች በፈጠራቸው ሰዎች ፊት እንዲዋረድ አደረገው የደም ላብ እንዲያልብ እንዲ ጨነቅ አደረገው! ሀጢአትትት! * በኢየሱስ ዋጋ የምሕረት በር ለዘላለም ተከፈተ! በኢየሱስ ዋጋ የሀጢአት ሒሳብ ተወራረደ! አንድ ሰው መቼም ወንጀል ሲሰራ መከሰሱ አይቀርም አንድ ሠው ወሩን ሙሉ ሰጥ ለጥ ብሎ ሰርቶ ደመወዝ የለህም ሊባል አይችልም! ልክ እንደዛው ሁሉ ሀጢአ ትም ዋጋ አለው ዋጋው ሞት ነው!(1ኛቆሮ15፥56) የሞት መውጊያ ሀጢአት ነው! የሀጢአትም ሀይል ሕግ ነው እንደተባለው ነው። *በሀጢአት መጫወት በመስ ቀሉ ስራ በተከፈተው ትልቅ የምሕረት ደጅ ማፌዝ እንደ ሆነ ይሰማኛል። ይሄን ያክል ዋጋ በተከፈለበት ሀጢአት መጫወት በእሳት መጫወት መስሎ ይሰማኛል። ምሕረቱን ሳስብ ለሀጢአቴ ዋስትና ለመ ስጠት መጠቀም አልፈልግም ይልቁንም ምሕረቱን ሳስብ ዋጋውን ዋጋውን ሳስብ ለሀጢአት የተከፈለውን ዋጋ ያንን ደግሞ ሳስብ የይቅርታና የምሕረቱን ጥልቀት የተሰጠኝን ሰፊ የምሕረት በር የምሕረት እድል የምጠቀመው ጸጋውን የተከፈለልኝን ዋጋ ለሀጢአቴ ዋስትና አድርጎ በማቅረብ ነጻ ፈቃድ እንዳለኝ በማሰብ ሳይ ሆን ለክርስቶስ ይበልጥ ለመ ኖር እንዳስብ ያሳስበኛል። @christology_GC @christology_GC

  • 19 апр. 2025 г.56667из christology_GC

    ገላትያ ጥናት መግቢያ የገላትያ መግቢያ ጽድቅ በእምነት ድነት በጸጋ ገላትያ የነጻነታችን አርማ!! ብዙ በመነበብ የሚታወቅ መጽሀፍ ነው። ሉተርን ለReformation እንቅስቃሴ የተጠቀመበት መጽሀፍ ነው። የፕሮቴስታንት እንቅስቃሴ የተወለደው በገላትያ መልእክት ነው። 9ነኛው የአዲስ ኪዳን መጽሀፍ ነው። 4ተኛው የመልእክት መጽሀፍ ነው። 1ኛው የጳውሎስ ደብዳቤ/መልእክት ነው። ከጳውሎስ ደብዳቤዎች መካከል የመጀመሪያ እንደ ሆነ የሚታመን መጽሀፍ ነው። መቼ ተጻፈ? በ50አ.ም ተጻፈ። በሀዋ.ስራ 14እና 15 መካከል እንደተጻፈ ከኢየሩሳ ሌም ጉባኤ በፊት ተጽፏል ተብሎ ይታመናል። ምክንያቱም ከጉባኤው በሁዋላ ቢጻፍ ኖሮ በመልእክ ቱ ላይ የጉባኤው ጭብጥ ይካተት ነበረ። ከ1ኛው የወንግል ጉዞ በሁዋላ ነው የተጻፈው። መጽሀፉ ለገላትያ አቢያተክርስትያናት የተጻፈ ነው። *ልስጥራን ሁለቱ ቦታዎች ጳውሎስ ጢሞቲዎስን ያገኘባቸው ቦታዎች ናቸው። *ደርቤን ገላ6፥11 ፦ እንዴት ባሉ ታላላቅ እጆቼ እንደጻፍ ሁላችሁ ተመልከቱ ሲል ራሱ እንደጻፈው ያረጋግ ጣል። ገላትያ የነጻነት አርማ ነው። ጳውሎስ በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ ሆኖ የጻፈው መጽሀፍ ነው?? ገላ1:6፦ ወደ ተለየ ወንጌል ፈጥናችሁ መዞራችሁ ድንቆኛል ሲል በመደነቅ ውስጥ ሆኖ እንደጻፈው ማየት ይቻላል። በጭንቀት ውስጥ ሆኖ የጻፈው ነው፦ ገላ4፥19-20 ምጥ ይዞኛል በማለት ያረጋግጠዋል። ገላ4፥11፦በከንቱ ስለእናንተ የደከምኩ እየመሰለኝ እፈራለሁ ሲል ፍርሀት ውስጥ ሆኖ እንደጻፈው ማረጋገጥ ይቻላል። መደነቅ ጭንቀት ፍርሀት ውስጥ ሆኖ የጻፈው ነው። የገላትያ መልእክት አላማ * የወንጌሉን እውነት ለመከላለከል ታስቦ የተጻፈ ነው። *የገላትያ ሰዎችን ወደ ኢየሱስ ለመመለስ ነው። *በሕግና በእምነት በነጻነትና በቅድስና መካከል ያለውን ግንኙነትና ልዩነት ለማሳየት ነው። *ቅድስና የመዳን ምክንያት ሳይሆን የመዳን ግብ እንደሆነ ለማሳየት የተጻፈ ነው። *መቀደስ በሙሴ ሕግ ሳይሆን በኢየሱስ ነው። ገላትያ 31 ጊዜ ሕግን 21 ጊዜ እምነትን 18 ጊዜ ስጋን 15 መንፈስን 11 ጊዜ ባርነትን 10 ጊዜ ተስፋን 6ጊዜ መስቀልን ጽፎልናል።

  • 17 апр. 2025 г.557из christology_GC

    የባርኮት እና የጸሎት ጊዜ 🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐🖐 ሊያመልጥዎት አይገባም! @christology_GC @christology_GC

  • ከሕግ አስተማሪዎች መጠበቅ! 🗣 ክፍል 2 ❇️ 48MB❇️ ሁሉም ሊያደምጠው የሚገባ! 📌 የሚቆረጡት ቅርንጯፎች እነማን ናቸው??? 📌የሕግ አስተማሪዎች ደሕንነታችንን እንድንጠራጠር ያደርጉናል...! ይቀጥላል... @christology_GC @christology_GC

  • ከሕግ አስተማሪዎች ተጠበቁ! 18MB ድንቅ አስተማሪ መልእክት ❇️ ቲቶ 2፥11❇️ Share 💯 share 💯 share💯 @christology_GC @christology_GC

  • 9 апр. 2025 г.81421из christology_GC

    ሞቴን በሕይወት ቀይሮ ነገሬን ሊገለብጥ በጭንቀቴ ሊያሰፋ ከፍታን ለኔ ሊሰጥ አዎ ዘመን መጣ ከፊቴ ፋሬስ ብዬ ምጥስበት የያዘኝ ዳግም ላይዘኝ ሰብሬ የምወጣበት @christology_GC @christology_GC

  • 8 апр. 2025 г.67210из EWNETINBEFKERYEWNGALAGELGELOT

    без подписи

  • ❇️ጽድቃችን❇️ PART 1 ሁሉም ሊያደምጠው የሚገባ ድንቅ ትምህርት 📌 ጽድቃችን ፍጹምና ዘላለማዊ ነው! 📌በሀሰት ትምሕርት እንዳትታለሉ ጽድቃችን የተረጋገጠ ዋስትና ያለው ን መዳን ሰጥቶናል! @christology_GC @christology'_GC

  • 7 апр. 2025 г.631из christology_GC

    # አስጠኚ ይፈልጋሉ?? ✍ ልጆችዎን መቆጣጠር ከስራዎ ጋር ተደራርቦ አልመች ብልዎታል ✍ የሚያሳርፍ የላቀ ብቃት ያለው አስጠኚ ደርሶሎታል ✍ ማጋነን አይደለም ተጠቅመው ያዩታል ማየት ማመን ነውና በተመጣጣኝ ዋጋ የልጆችዎን የነገ እጣ ፋንታ ይወስኑ!! GRADE ከ 1ኛ እስከ 4ተኛ ክፍል ደውለው ይመዝገቡ 🗣ስራችን ምስክር ነው! በ0994839910 ላይ ይደውሉ ያገኙናል @christology_GC @christology_GC