Bilalul Habeshi Community ቢላሉል ሐበሺ - ኑ ወደ ደግነት
Статистика''እኛ ከገንዘባችሁ በፊት ቀልባችሁን እና ማንነታችሁን እንፈልጋለን! ገንዘባችሁ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ላይኖር ስለሚችል ስለ ቀልባችሁ እንጨነቃለን። ምስኪኖች ግን በቅደሚያ ገንዘባችሁን ይፈልጋሉና አስታውሱዋቸው። አሏህ ﷻ እናንተን ያስታውሳችኃል ።'' (ኡስታዝ ሙሐመድ ጀማል ጎናፍር የቢላሉል ሐበሺ ዋና መስራችና የበላይ ጠባቂ )
- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 20
- Всего постов
- 29
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 129
- 1/48двое суток
- 147
- 1/72трое суток
- 159
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
የእዝነቱ ነቢይ! **** በዚህ ታላቅ የረቢዕ ወር፣ ለአለማት እዝነት ሆነው የተላኩትን የነቢዩ ሙሐመድን (ﷺ) ውልደት እናስታውሳለን። የእሳቸው መምጣት የጨለማው ዘመን ማብቂያ እና የብርሃን፣ የፍቅር እንዲሁም የርህራሄ ጅማሮ ነበር። የህይወት ዘመናቸው ሙሉ የሰው ልጅን ወደ በጎነት የመምራት ጥረት ሆኖ አልፏል። ኑ ወደ ደግነት! የነቢዩን (ﷺ) የራህመት መንገድ በተግባር በመከተል፣ እጃችንን ወደ ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል እንዘርጋ። ማዕከሉን በመርዳት የእዝነት እና የደግነት ተቋዳሽ እንሁን!
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
ልዩ የጉብኝት መርሐ-ግብር በቢላሉል ሐበሺ ማዕከል! ** በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያን የተለያዩ ከተሞች እና ቦታዎች እየጎበኙ የሚገኙ ከሳውዲ አረቢያ የመጡ ታላላቅ ኡስታዞች፣ ዳዒዎች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች (ታዋቂ ቲክቶከሮች) በቢላሉል ሐበሺ ማዕከል በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል። የተቋማችንን መስራችና የበላይ ጠባቂ ኡስታዝ ሙሐመድ ጀማል ጎናፍርን አግኝተው አነጋግረዋል። በነበራቸው ቆይታም ማዕከላችን እያከናወናቸው ባሉ ሰፊ የማህበራዊ ስራዎች እና እንቅስቃሴዎች ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን፣ ወደፊት በሁለቱ ወገኖች መካከል ሊጠናከሩ በሚችሉ የትብብር መስኮች ላይም ፍሬያማ ምክክር አድርገዋል። ይህ ጉብኝት ለቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ልዩ ትርጉም ያለው አጋጣሚ ነው። ክቡራን እንግዶቻችን በማዕከላችን ተዘዋውረው በተመለከቷቸው እና በሰሟቸው ተስፋ ሰጪ ተግባራት ላይ ያላቸውን ልባዊ አድናቆት እና መልካም አስተያየት አስፍረዋል። ጊዜያችሁን ሰውታችሁ ተቋማችንን ስለጎበኛችሁ ከልብ እናመሰግናለን! #BilalulHabeshi #BHTC #Ethiopia #SaudiArabia #IslamicScholars
ሉህ (ለውሕ) ጥንታዊው በእንጨት ላይ የተከተበ ቁርአን! #ኢስላማዊ_ትምህርት #ቢላሉል_ሐበሺ #BilalAlHabashiMuseum
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
без подписи
በአፋር ክልል ለሚገኙ ኡለማዎቻችን እና ተማሪዎች የድጋፍ መርሐግብር ተካሄደ! * ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል በአፋር ክልላዊ ቅርንጫፉ አማካኝነት ለተከበሩ ኡለማዎች የገንዘብ እና የአልባሳት፣ እንዲሁም ለተማሪዎች የሚሆን ልዩ ድጋፍ አድርጓል። ይህ አሁን የተደረገው የቢላሉል ሐበሺ ድጋፍ ጅማሮ ሲሆን፤ በቀጣይም ይህንኑ በጎ ተግባር አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል። በዕለቱ በርካታ ኡለማዎች፣ ሸይኾች እና ወጣቶች የተገኙ ሲሆን፤ ለተደረገላቸው ድጋፍ እና ማስታወስ ከልብ የመነጨ ምስጋናቸውን ገልፀው ዱዓ አድርገዋል። ተጨማሪ ከክልሉ የመንግስት አመራሮች ጋር በመነጋገር ለቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ግንባታ የሚውል የቦታ (መሬት) ጥያቄ ሂደት እንደሚካሄድ አሳውቀውናል። ኡለማዎቻችን የዲን አውራዎች ናቸው። ሁላችንም ከጎናቸው በመቆም፣ በማገዝና በማስታወስ የበኩላችንን ኃላፊነት እንድንወጣ ጥሪያችንን እናቀርባለን። #ቢላሉል_ሐበሺ #አፋር #ኡለማዎች #ድጋፍ #ኢስላማዊ_ትምህርት #BilalulHabeshi #Afar