Ethio Stock info
Статистикаየባንክ የኢንሹራንስና የሌሎች ንግድ ድርጅቶች የድርሻ/አክሲዮን/ መረጃ ! ሥልክ ፡ 0911248597/0940599595 Banks, Insurances and other corporations share information! Phone No.: 0911248597/0940599595
- Последний пост
- 31 янв.
- Последнее чтение
- 14:28
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 135
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- Категория
- Новости и СМИ (по похожим)
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- —
- 1/48двое суток
- —
- 1/72трое суток
- —
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
Special FX Auction Notice!
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
የዳሽን ባንክ አክስዮን ማህበር የምዝገባ ማስታወቂያ ********* በሰነደ ሙአለ ንዋይን ለህዝብ የማቅረብ እና ግብይት መመሪያ ቁጥር 1031/2016 አንቀጽ 4 እና 29 ላይ በመመሪያው ወይም በካፒታል ገበያ አዋጅ ቁጥር 1248/2013 ከምዝገባ ነጻ ከተደረጉ ውጪ ያሉ ለህዝብ የሚቀርቡ ወይም የሚሸጡ ሰነደ ሙአለ ንዋዮች በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን መመዝገብ ያለባቸው በመሆኑ እና መመሪያው ከመውጣቱ በፊት በህዝብ የተያዙ ሰነደ ሙአለ ንዋዮችም ባለስልጣኑ መመዝገብ ያለባቸው መሆኑ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በዚህም መሰረት ባለስልጣኑ በታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. የዳሽን ባንክ አክስዮን ማህበርን የምዝገባ መግለጫ ያጸደቀ ሲሆን በዚህም መሰረት፡ ➡️ በነባር ባለአክስዮኖች ተይዘው ያሉ አስራ አራት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሰላሳ ሰባት ሺህ (14,337,000) አክስዮኖችን፤ እንዲሁም ➡️ በያዙት አክስዮን ድርሻ ልክ ለነባር ባለአክስዮኖች እና/ወይም ነባር ባለአክስዮኖች ሳይገዙ ከቀሩ ለብቁ ኢንቨስተሮች/ ለህዝብ የሚቀርቡ ሁለት ሚሊየን ሁለት መቶ ስድስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ስድስት (2,206,906) አክስዮኖችን የመዘገበ መሆኑን ለህብረተሰቡ ለማሳወቅ ይወዳል፡፡ ማሣሠቢያ: ማስታወቂያው ሰነደ ሙአለ ንዋይ ለመሸጥ ወይም እንዲሸጡ ለማድረግ የቀረበ ጥሪ አለመሆኑ፤ ይህ ማስታወቂያ የወጣው ሰነደ ሙአለ ንዋዮች በባለስልጣኑ መመዝገባቸውን ለሕዝብ ለማሳወቅ ብቻ ሲሆን፤ ማንኛውንም ሰነደ ሙአለ ንዋዮች ለመሸጥ የቀረበ ጥያቄ ወይም እንዲሸጡ ለማድረግ የቀረበ ጥሪ ወይም ማስታወቂያ አይደለም። #Dashenbank
የሕብረት ኢንሹራንስ የ 2017 በጀት ዓመት ትርፍ 1 ቢሊዮን ብርን ተሻገረ! ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ 1.08 ቢሊዮን ብር አትርፏል። ባንኩ በአንድ አክሲዮን 68.56% ትርፍ አስመዝግቧል።
አማራ ባንክ ከታክስ በፊት 654 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር አተረፈ! ******* Via FBC አዲስ አበባ፣ ሕዳር 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አማራ ባንክ በ2017 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት 654 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር ትርፍ አስመዘገበ። የባንኩ አራተኛ ጠቅላላ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል። የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) በዚህ ወቅት÷ ባንኩ በበጀት ዓመቱ ከታክስ በፊት 654 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር ትርፍ ማስመዝገቡንና ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ85 በመቶ ዕድገት እንዳለው ተናግረዋል። በተጨማሪም የባንኩ አጠቃላይ ሀብት 43 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር መድረሱንና ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀርም የ23 ነጥብ 2 በመቶ ዓመታዊ ዕድገት እንዳሳየ አመላክተዋል። የባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ በ26 በመቶ በማደግ ወደ 31 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ከፍ ብሏል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው÷ በበጀት ዓመቱ 70 ነጥብ 8 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማግኘቱን ጠቁመዋል። አጠቃላይ የባንኩ ካፒታል በ21 በመቶ በማደግ 8 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር እንዲሁም የተከፈለ ካፒታሉ በ14 በመቶ በማደግ 7 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ደርሷልም ነው ያሉት። በበጀት ዓመቱ አጠቃላይ የባንኩ ገቢ 5 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር እንደደረሰና ከዚህም 80 በመቶው የሚሆነው ወለድ ነክ ከሆኑ የብድር ሥራዎች የተገኘ መሆኑን አስረድተዋል። ይህም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ29 በመቶ ዕድገት ማሳየቱ ተገልጿል። #AmharaBank #አማራባንክ
ጋዜጣዊ መግለጫ | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሩብ ዓመት የውጭ ምንዛሪ ጨረታ መርሐ ግብር! #NBE
Bunna Bank የቡና ባንክ አክሲዮን ማህበር የዳይሬክተሮች ቦርድ የባንኩን የተከፈለ ካፒታል በ2022 ዓ.ም. መጨረሻ (እ.ኤ.አ 2030) ወደ 20 ቢሊዮን ብር ለማሳደግ የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ዕቅድ አዘጋጅቶ ለባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ የውሳኔ ሃሳብ ሊያቀርብ መሆኑ ተገልጿል። ይህ ዕቅድ ባንኩን በቀጣይ 5 ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ሦስት ቀዳሚ የፋይናንስ ተቋማት ተርታ ለማሰለፍ የሚያስችል ነው። የቦርዱ የተከፈለ ካፒታል የማሳደጊያ ዕቅድ በመጪው ቅዳሜ ህዳር 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚያደርገዉ 16ኛዉ የባለአክስዮኖች መደበኛና 7ኛዉ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ቀርቦ ይፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል። ባንኩ ካፒታልን ማሳደግ ያስፈለገበት ዋነኛው ምክንያት፣ ዛሬ ካፒታልን ማሳደግ የሕግ ግዴታን የመወጣት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ የህልውና እና የላቀ ተወዳዳሪነት ጉዳይ መሆኑን መገንዘብ ነዉ ሲል ቦርዱ አስታውቋል። በስትራቴጂክ እቅዱ ላይ ካፒታል ጋዜጣ ለመመልከት እንደቻለው ፤ ብሔራዊ ባንክ ከዚህ የሒሳብ ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ያጸደቀውና ባንኮች ለሌሎች ስጋቶችም በቂ መተማመኛ የሚሆን ጠቅላላ ካፒታል እንዲይዙ የሚያስገድድ አዲስና ጥብቅ መመሪያ ባንኩ ካፒታሉን እንዲያሳድግ ያስፈለገበት ቀዳሚዉ ምክንያት እንደሆነ በዝርዝር አስቀምጧል። በተጨማሪም መንግሥት የባንክ ዘርፉን ለውጭ ባንኮች ክፍት ማድረጉን ተከትሎ የሚመጣውን ከፍተኛ ውድድር መቋቋም ለመቻይ ይህ ዉሳኔ በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን አፅንኦት በመስጠት አብራርቷል። ቦርዱ ፤ ባንኩ የረጅም ጊዜ ስትራቴጂካዊ ዕቅዱን ለማሳካት እና በተለይ የብድር አቅርቦት አቅሙን በዘላቂነት ለማስፋት የሚያስችል ጠንካራና አስተማማኝ የካፒታል መሰረት መገንባት ወሳኝ እንደሆነ ገልጿል። Via #capital #Bunnabank
ለዘመን ባንክ ባለአክሲዮኖች የተላለፈ መልዕክት፡ "ዉድ የዘመን ባንክ ባለአክሲዮኖች የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የሰነደ ሙዓለ ንዋይን ለህዝብ የማቅረብ እና የግብይት መመሪያዉ በሚደነግገዉ መሰረት አክሲዮኖችን ለሽያጭ ያወጡ ድርጅቶች መመሪያዉ ከመዉጣቱ በፊት የሸጧቸዉን አክሲዮኖች ባለሰልጣን መ/ቤቱ እስከ ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ.ም የማስመዝገብ ግዴታ እንዳለባቸዉ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ በዚህም መሰረት ጥቅምት 01 ቀን 2018 ዓ.ም. በተደረገው የባለአክሲዮኖች 12ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በተሰጠዉ ማሳሰብያ መሰረት ቀነገደቡ ከመጠናቀቁ በፊት ተፈርመዉ ክፍያ ያልተከፈለባቸዉን አክሲዮኖች እስከ ህዳር 11 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ቀሪ ክፍያ በመክፈል አክሲዮኖቹ መመዝገብ እንዲችሉ እንዲያደርጉ እናሳስባለን፡፡ ዘመን ባንክ አ.ማ" ያልተከፈሉ የዘመን ባንክ አክሲዮኖችን እንገዛለን። ይደውሉልን: +251911248597 +251940599595 Greetings, We buy Subscribed Zemen bank shares, call us: +251911248597 +251940599595
የብርሃን ባንክ የ 2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም **** Gross Profit: 2.5 Billion EPS: 54.7% Total Asset: 58.9 Billion * ምንጭ፡'Berhan Bank S.C. 2024-25 Annual Report'
видео или голосовое, без подписи
"የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ምዝገባ ሊጠናቀቅ 30 ቀን ቀረው *************** ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች (አክሲዮኖች) በሙሉ በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን መመዝገብ እንዳለባቸው በካፒታል ገበያ አዋጅ እና የሰነደ ሙዓለ ንዋይ ለህዝብ የማቅረብ እና ግብይት መመሪያ ተደንግጓል። የምዝገባ ህጉ ተፈጻሚነት የሚኖረው፤ 1ኛ. ከዚህ ቀደም አክሲዮኖቻቸሁን ለህዝብ የሸጣችሁ፣ 2ኛ. መመሪያው ከመውጣቱ በፊት የአክሲዮን ሽያጭ ጀምራችሁ ሽያጩ አሁንም በሂደት ላይ የሆነ ወይም፣ 3ኛ. አዲስ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች የሚያወጡ የአክሲዮን ማህበራት ላይ ተፈጻሚነት ያለው በመሆኑ በሚቀጥሉት ሰላሳ ቀናት መመዝገብ እንዳለባችሁ በድጋሚ ለማስታወስ እንወዳለን፡፡" የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን
የጠቅላላ ጉባዔ ጥሪ📣📣📣 *** መክሊት ማይክሮፋይናንስ ኢንስቲትዩሽን አ.ማ. የባለአክሲዮኖች 17ኛ መደበኛ እና 12ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን ጥቅምት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ አዲስ አበባ በሚገኘው ግዮን ሆቴል ሳባ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ያካሂዳል። በመሆኑም የተከበራችሁ የአክሲዮን ማህበሩ ባለአክሲዮኖች በዕለቱ በጉባኤው ላይ እንድትገኙልን የማህበሩ ዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪውን ያስተላልፋል። በጉባኤው ላይ በአካል መገኘት የማትችሉ ባለአክሲዮኖች በተቋሙ ዋና መ/ቤት ወይም በሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ፅ/ቤት በመገኘት ውክልና መስጠት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ተጨማሪ መረጃ እና ማብራሪያዎችን ረቡዕ ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ/ም በወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ መመልከት የምትችሉ መሆኑንም በአክብሮት ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ *** መክሊት ማይክሮፋይናንስ ኢንስቲትዩሽን አ.ማ የዳይሬክተሮች ቦርድ! *** #MeklitMFI #GeneralAssembly2025 #GhionHotel #UnlockingYourPotential
видео или голосовое, без подписи
የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ ለህብረት ኢንሹራንስ ባለ አክሲዮኖች ⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳ ሐሙስ ህዳር 4 2018 ፒያሳ አደዋ ድል መታሰቢያ
የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ ለ Coop ባንክ ባለአክሲዮኖች *************** ቀን ____ለ ጥቅምት 22 2018 ቦታ____በአዳማ ከተማ አባ ገዳ አዳራሽ
የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ ለአሐዱ ባንክ ባለአክሲዮኖች *************** ቀን ____ህዳር 13 2018 ቦታ____ሚኒሊየም አዳራሽ
የዘመን ባንክ የ 2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ******** Gross Profit: 8.9 Billion EPS: 68.3% Total Asset: 88.6 Billion ***** ምንጭ፡'Zemen Bank S.C. 2024-25 Annual Report'
የወጋገን ባንክ 2017 ዓ/ም አፈፃፀም