- Последний пост
- 12 авг.
- Последнее чтение
- 14 авг.
- Постов за неделю
- 2
- Всего постов
- 20
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 38
- 1/48двое суток
- 43
- 1/72трое суток
- 46
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
የሀዘን ግጣም ናት ፣ ትለኛለህ አሉ ገል ነው ሰውነቷ ፣ ወዲያው ይጠፋል ውሉ ሊቅ ደቂቅ አታውቅም ፣ የማይንጣት የለም ትለኛለህ አሉ ፣ ልምዷ ነው መቆዘም ። ወለምታ ነው የሚቀናት ትንሹ ነው የሚያበግናት ሀሳበ ውስን ነች አታይም አርቃ ሀዘን ይቀናታል ኢምንቷንም እከል ታያለች አትልቃ ። ትለኛለህ አሉ አልከኝ አሉ ጠና ያለ ወግ አያምርባት ቆፍጠን ማለት አይሄድባት አታውቅበት መከራከር ምከንያት ሰበብ በረድፍ አርጎ ከፍ ማለት በስሜት ላይ ፣ ፊትን ከልብ ዘወር አርጎ ። ባይሳንም ይከብደኛል ፣ እውነት አለው ንግግርህ ማይወርፍህ ይጥለኛል ፣ ጣም የሌለው ይመረኛል ባየሆን ይሄን አትዘንጋ በሚታየው ስለምወድቅ ፣ ልብህ መራቅ ስላልቻለ እንዳይመስልህ ደንዳናነት ፣ ስርቴ ላይ ያልታከለ ። ምሕረት ዘነበ
ሰምተን እስክንመልስ ፥ አይተን እስክንሰይም ተራምደን እስክንደርስ ፥ ጨርሰን እስክንደግም ስንት ከስተቶች አሉ የህይወት አካል ማይመስሉ ። ምን ያህል ዛሬዎቻችን ተሰው ለመዳረሻ ላይመጡ አሳለፍናቸው እያወዳደርን ጣልናቸው ምንም እንደሌላቸው በእኛነታችን ድርሻ ። እየኖሩ መሄድ ነው ፥አዳንዴም ቀረት እያሉ ለሁሉ ምላሽ ባይሰጡም ፥ ከሁሉ እያስተዋሉ መዳረስ ይበል ቢያስብልም ፥ መሰየም ከትልቅ መድረክ መኖር ይካከስ ይሁን ዛሬ ትላንት ሲሆን ይኖረዋልስ ደህና መልክ ? ምሕረት ዘነበ
ሆይሆይታ ነው ጊዜው ፥ ወረት ነው አለሙ እንኳን የሌላ አካል ፥ የገዛ ልባችን አይገባን ቀለሙ አለመኖር ማለት ፥ አለመመሳሰል ከአንድ አለመሰየም አለ' መሞት ማለት፥አብረው እየተጓዙ አለመሽቀዳደም ። ጫፉ ጠፍቷል በዘመኔ "መሆን " የለው መዳረሻ ቤትም ይምሩን ተጓዦች ነን ፡ ብቻ አንቁም ፣ ብቻ አንባል መጨረሻ ። ምሕረት ዘነበ
ሀሳቤ መች አስቦልኝ ፣ እዚህ አድርሶኝ ማወቄ መች ቁጥር ይገባና ፣ ድል ያረኩት ተጠንቅቄ ከንቱ መሆኑ ጭንቀቴ ፣ ማወቁ መቼ ተሳነኝ ሰውነት ቢይዘኝ እንጂ ከእምነቴ ሀይል በላይ ፣ ገሀድ ህይወቴ ቢጫነኝ ። "ያልፋል" አትብለኝ አልፋለሁ ልክ ነው ይረሳል ረግፋለሁ እውቀቴ አድማስ ፣ቢሻገር ብሰማም ሲባል ብዙ ሰማይ ከመሬት ሲላቀቅ ፣ ይጀምረኛል መቅበዝበዙ። "ያልፋል "ማለት አያለፋም ትናንትና ምን ቢዘምም ፣ ከዛሬ ጽልመት አይከፋም ልክነትህን ልቀበል ፣ ካለመቻሌ ተስማማ ድንግዝግዝታዬ ይዋጥልህ ፣ ዳግም ተስፋን እንድጫማ ። ሀሳብን ሽቼ አይደለም ፣ ምክርን ውስጤ ናፍቆ የሚናገርን አንደበት ፣ ምክንያት ከውጤት አራቆ "ከብደኝ ፣ደከመኝ" ስልህ ፣" ለምን ?" እንዳይሆን መልስህ ይልቅ ዝም በልና ፣ አጥር ሁንልኝ በክንድህ። ሳትደርስብኝ ልትደርስልኝ አትታገል መች ተችሎት ፣ ተግሳጽ ሁሉን መገላገል ። " ከበደኝ ፣ ደከመኝ " ስልህ ፣ "እንዴት?" እንዳይሆን ምላሽህ ትከሻዬ እና ቀንበሬን ፣ አታወዳድረው ከራስህ ባለፋከው ነገር ሚዛን ፣ አይነውረብህ ሽንፈቴ የእኔ አቅም እዚህ ድረስ ነው ፣ "ልክ ነሽ " በለኝ በሞቴ ። ምሕረት ዘነበ
የተወዳጁ አዳም ረታ አዲሱ መጽሐፍ ነገ ቅዳሜ በሁሉም የጃዕፈር መጻሕፍት መደብሮቻችን ለሽያጭ ይቀርባል :: በቅርብ ቀናት ደግሞ ከደራሲ አዳም ረታ ጋር በመነጋገር የፊርማ ስነስርአት ዝግጅት ይኖረናል :: በድጋሚ ለማሳወቅ ያክል በአዲስ አበባ ኤግዝቢሽንና ባዛር ላይ አልተሳተፍንም :: ምክንያቱንም ሌሎች ተሳታፊዎች ከከፈሉት እጥፍ ክፈሉ ስለተባልን ነው :: ይህንንም በተደጋጋሚ የምናሳውቀው ጃዕፈር መጻሕፍትን ብላችሁ ሄዳችሁ ውድ ጊዜያችሁንና ገንዘባችሁን እንዳታባክኑ በማሰብ ነው :: ከመደበኛው ሽያጭ ባለፈ ባሉን ሁሉም ቅርንጫፎቻችን እስከ እሁድ ድረስ ልዩ ቅናሽ አድርገናል ይህን አጋጣሚ ተጠቅማችሁ ከ 30% እስከ 50 % ቅናሽ መጻሕፍትን መሸመት ትችላላችሁ :: እናመሰግናለን !
"My mission in life is not merely to survive, but to thrive." Maya Angelou
እስቲ ዛሬ ደግሞ ለለውጥ ያክል አለቃ ክንፌ የላኩልኝን ግጥም መሳይ ምክር ልጋብዛችሁ! ©️(በዕውቀቱ ስዩም) (ለለጅ ምክር የአባት መታዘቢያ) ልዠ ሆይ! ሙቫይልህን አስቀምጥ ምክሬን አድምጥ ! ጦርነትን የሚጠምቀው እድሜውን ብትጠይቀው የማቱሳላ ገራዥ የአብርሀም ዣንጥላ ያዥ በጎሽ ያረሰ አዳምና ሄዋን ገምጠው የተፉትን በለስ አንስቶ የጎረሰ የሎጥን ሚስት ሀውልት የላሰ ሆኖ ታገኘዋለህ ፤ ልዠ ሆይ! ጦርነትን የሚያውጀው ያረጀው ነው የጃጀው ግና ጦርሜዳ ላይ የሚዋጋው ያንተ ብጤ ነው ለጋው፤ ሜሲ አንደመታት ኩዋስ ወደ መቃብር የሚልለጋው፤ ልዠዋ! በጀግኖች ዘመን እንኩዋ-“ከመሞት መሰነበት” ይባላል የሰማእት ሀውልት ሆኖ ተመቆም ህያው ሆኖ መተኛት ይሻላል ልዠ ሆይ! በሀያላን እንዳትታፈስ ሁንባቸው መንፈስ መንፈስ መሆን ቢሳንህ ; ሁንባቸው የጎመን ፈስ ቀን እስኪያልፍ ድረስ ወደ ጎረቤት አገር ንፈስ፤ ልዠ ሆይ ! ጦርነት ማለት አንድ ሀሙስ የቀራቸው ሸባዎች፣ አንድ ሀሙስ ብቻ የኖሩትን አበባዎች የሚያስቀጥፉበት አዝመራ ነውና በሰማእትነት ስም ምትክ አልባ ሕይወትህ ሳይከስም እሸት አካልህን ሳይለውጡት ወደ ፍግ ተግተህ አፈግፍግ፤ ልጄ ሆይ! ለማንም ኩስለመናም ነፍስ ይማር ለማለት አንኩዋ ጊዜ ለሌለው የሙቫይልህን ካሜራ አንጂ ጠመንጃህን አትወልውለው፤ አለቃ ክነፌ በተሳትፎዎ ይቀጥሉበት!
" When you learn teach , when you get give . Maya Angelou
ነግረሀኝ ነበር ስሜ በአንተ አፍ ሆኖ እንደማያውቅ መጠሪያ ብቻ ከሚያውቀኝ ሁሉ ቃሉም ትረጉም እንዳይደል አቻ የሚተነተን መልክት እንዳለው ከልብህ ሰፈር እንደሰየምከኝ አንድ ቃል አርገህ ልክ እንደ ሀገር ። ነግረሀኝ ነበር እኔም አምኜ በአጠራርህ ከብዙ ድኜ ። ቆም እስኪያረገኝ አንድ አጋጣሚ እየጠራሀኝ አቤት ሚል ሳስ ልክ እንደ ሰሚ አፍታ እስኪበቃህ ሌላ ለመጫር በእንቅፋቴ ሹመቴ እስኪሻር። ያቺው ብሆንም ቀጥ ያለ አይደለም ዛሬ አቋቋሜ ለካ ወትሮውም ተግባሬ ነበር የእኔ ስያሜ ። ምሕረት ዘነበ
ንግግር ነው የሰው ቋንቋ የእውነቱ ልክ ሚያየውን ነው " ሆነ "ብሎ የሚተርክ አለ ተብሎ ካልተነካ ፥ ያውቃል ተብሎ ካላብራራ የልብ እልፍኝ ፥ አይታይም በሰው ተራ ሸርተት ስትል ፥ እንደምትቆም ሚያስታውስ ሳይከፋ ማንም የለም ፥ በስህተትህ አንተነትህን ማያጣፋ ። ምሕረት ዘነበ
"Living is easy with eyes closed, misunderstanding all you see…." John Lennon
"You may not control all the events that happen to you, but you can decide not to be reduced by them." — Maya Angelou
ላረፈበት ሀሳብ ፥ ልቡን ለተጠጋ ቀድሞ ያለመውን ፥ በቃሉ ላረጋ ከመጥላት መውደዱ ፥ ወዲያው ለሚዛመድ ፈጥኖ ለሚያገኘው ፥ ብዙ ሳይራመድ ይሆናል ጠበቃ ፥ በሁሉ ደጋፊ ወለምታውን የሚያሽ ፥ ግድፈቱን አላፊ ከየትም ይምጣ ወዴት ፥ ሰው ያው ሰው ነው ዞሮ ለርሱ ፣ ከርሱ ሲሆን ፥ ሚዛኑ ሳት ይላል የማንም ከወትሮ ። ምሕረት ዘነበ
" Sometimes , being nice is not being kind. " Kim scott
" Find what you love and let it kill you " Charles Bukowski
ትዝታችንን ቀርቶ ፣ ውልብታችንን ላልኖረ ስናልፍ ስናገድም ብንውል ፣ በአንገቱ አንዴ ላልዞረ እያየ ለማያጤነን ፣ አልፎም ምንጨነቀው የትኛው ሀሳብ ሞልቶልን ፣ የትኛው ጊዜ ተርፎን ነው ? ምሕረት ዘነበ
ድሮሮሮ.. ሆነህ ዩኒቨርስቲ ከገባህ ያመልኩሃል። ያጨበጭቡልሃል። ያደንቁሃል። ጀለስካዎች ይቀኑብሃል። ጸዴ፥ የተማረች፥ ገርል ትጠብሳለህ። ላይፍ ይገባሃል። ራስህን ትችላለህ። ሰው አያነብልህም። በአውራ ጣትህ አትፈርምም! ፈረንጅ ማውራት ትችላለህ። ፖለቲካ ታውቃለህ። የመንግስት ስራ ትይዛለህ። ኮት ትገዛለህ። ቤተሰቦችህ ደረታቸውን ይነፋሉ። እህቶችህ የመጠበሻ ክላሳቸው ከፍ ይላል። ወመኔው ወንድምህ በስምህ ተበድሮ ያጨሳል። የሰፈሩ ቅያስ በስምህ ይጠራል "ያ ዩኒቨርስቲ የገባው ጨዋ ልጅ ቤት ጋ" ምናምን ነገር፥ የሰፈሩ ሼባዎች ያከብሩሃል፥ ወመኔ ጀለሶችህ በሹክሹክታ ያሙሃል፥ የተለየ ወጥ ይሰራልሃል፥ ትኩስ እንጀራ ይቀርብልሃል። ትከበራለህ። የዋለልኝን አርቲክል ታነባለህ። ጥላሁን ግዛው ይናፍቅሃል። መንግስትን ትጠላለህ። ቦርጫም ቢሮክራት ይደብርሃል። ፀጉርህን ታጎፍራለህ። ጺም ይኖርሃል። ፍልስፍና ታሪክ ፖለቲካ ትንሽ ሳይንስ ትለበልባለህ። ትከራከራለህ። በካሴት ሙዚቃ ትሰማለህ። ሲጋራ ታጨሳለህ። ወሬህ ፀዴ ይሆናል። አይዲያሊስት ሆነህ ቁጭ ትላለህ። ምድር ላይ ገነት ትፈልጋለህ። የኢትዮጵያ ህዝብ ባንተ ትግል ነፃ እንደሚወጣ ታምናለህ። ትመረቃለህ። በት'በት ብለህ የመንግስት ስራ ትይዛለህ። ቤት ትከራያለህ። መፃህፍት ይኖሩሃል። መንግስትን በጎሪጥ ታያለህ። እሱም ይገላምጥሃል። ሲመሽ ቢራ ትጠጣለህ። መንግስትን በሹክሹኩታ ታማለህ። መኖር ትጀምራለህ። ለናትህ ሻሽ ትገዛለህ። ለአባትህ የጠጅ መጠጫ ትሸጉጣለህ። ጨረቃን በገመድ ለማውረድ እንደሞከርክ ይገባሃል። ኒያላ ለኩሰህ ከት ብለህ ትስቃለህ። ታገባለህ። እናትህን አያት ታደርጋለህ። ሰፈሩ ለሚያሰራው መንገድ ሊቀመንበር ትሆናለህ።
በእርግጥ ፤ አለፍ አለፍ ብሎ ፥ ስም ለግብር ያዋጣል ያመኑትም ሀሳብ ፥ ሥጋ ለብሶ ይመጣል ቅድመ ክንውኖች ፥ መንገድ ይጠርጋሉ ግን ሁሌ ዋስ ሆነው መች ያስፈጽመሉ ? ብዙ እየታዘቡ ፥ ለሀሳብ ለፍላጎት ምክንያት ሰቶ መላፍ ማታ ህርሜን ብሎ ፥ ቀን አብሮ መሰለፍ የዛሬ ሰቀቀን ፥ የነገ ኪሳራ የፈረሰ ሁሉ ፥ ዳግም ላይሰራ አንዳንዱ አይለወጥ ፥ ይቅር እንደ ከፋ ላልሆነልን ሁሉ ፥ አይገባም ጸጸት አይገባም ተስፋ ። ምሕረት ዘነበ
Happy to see this 🥺🥰 The King is Back !! መዝሙረ ሄላም አዳም ረታ ብዙነህ
ላባቴ ሰው ብቻ አይደለህም ካፈር ወጥተህ ላፈር መላክ ነሕ ሉሲፈር ክብርሕ ማንነትሕ ባመፅ የሚታፈር የማትንበረከክ የማትርመጠመጥ ከባለጌ ዙፋን በርጩማ የምትመርጥ ያለባሕር ሰርጓጅ ያለሙሴ በትር በመታገስ ብቻ ባሕር የምትመትር ካዘልከኝ ጀምሮ እንኮኮ ጫንቃሕ ላይ ከፍታውን እንጂ ዝቅታውን ሳላይ እንደንስር መጠቅሁ እንደምስራቅ በራሁ የገዛ ክንፎቼን እንደ ዳንቴል ሠራሁ በርግጥ ደሃ ነበርክ ከሰላምታ በቀር የማታበረክት ነጠላሕ መናኛ ሰውነትሕ የክት በርግጥ ደሐ ነበርክ የነጣህ የጠራህ ከጦር ሜዳ ይልቅ ገበያሚያስፈራህ ቤሳ ባታወርሰኝ አወርሰክኝ ትግል የትም እንዳይጥለኝ ህይወት እንደፈንግል፡፡ አባየ ብርሐን አባ የእውቀት በር ገመና ሸሻጊ እንደ ካባ ገበር አባቴ ባትሆን ምን ይውጠኝ ነበር? (በእውቀቱ ስዩም)