የኔ' ማስታወሻ ..🧚
Статистикаበዚህ ቻናል የማይዳሰስ ጉዳይ የለም የተለያዩ አስገራሚ ታሪኮችን፣ ግጥሞችን፣ መጣጥፎችን፣ ወጎችን እንዲሁም በጥበባዊ እይታ የተቃኙ ሁሉ አይነት ጉዳዮችን እናይበታለን ሼር በማድረግ ቤተሰብ እናብዛ... እወዳችኋለሁ❤️ for any comment :- 👉 @Hamy_Hamy Subscribe 👇👇👇 https://www.youtube.com/@Yenemastawosha
- Последний пост
- 14 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 1
- Всего постов
- 22
- Тип
- открытый
- Язык
- ti
- Категория
- Видео
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 133
- 1/48двое суток
- 152
- 1/72трое суток
- 164
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
እምነት በመሀላ አይረጋገጥም😉 @poethaymi
ሰዎች አብዛኛውን ጊዜ መተው ባለመቻላቸው ምክንያት ምንም ጥቅም የሌላቸውን አሉታዊ ስሜቶች በመያዝ ጊዜያቸውን ያባክናሉ። #Master_Your_Emotions @poethaymi
ጅል ሰው ትኩሳት ነው ..🙅 @poethaymu
T.me/Poethaymi
አንዴ ብቻ ይድላኝ ፣ አንዴ ብቻ ልረፍ፣ አንዴ ብቻ ልኑር ፣ አንዴ ብቻ ልትረፍ ፣ ፋታ ብቻ ላግኝ እንደምፈልገዉ፣ እንዴት እንደማለቅስ እኔ ነኝ የማዉቀዉ ። Habtamu Hadra ✍️ @poethaymi @poethaymi
#መሳቅ_ግን_እንዴት_ነው? በጊዜ ቅብብል መሆን አለመሆን በሚታገሉበት መምሰል ከመሆን ጋር በሚወዳጅበት በዚህ በክረምቱ፦ በዝናብ ጠብታ አካሌ እየራሰ ልቤ እየተናጠ ይህን አስባለሁ... በታጠፈ አንጀቴ ብርድ በጀቦነው ልክ እንደጐርፍ እድሜ ታይቶ በሚጠፋው በዚ አቅም ሰባሪ በበረዶ ዘመን ማመን ተሸርሽሮ ቃል የትም ተጥሎ ሲመሽ እየነጋ ሲነጋ ቢመሽም ሳቅ ከተባለ የማያልፉት የለም... #መሳቅ_ግን_እንዴት_ነው? እንባ ከአይን ዘልቆ... ልብ ከሀሴት ርቆ ዝም ብሎ ብቻውን ተጉዞ.... ተጉዞ.. ያሰቡት ሲጐድል ስህተት ልክ ሲሆን ትክክል ሲሳሳት ጐደሎ ተሟጦ የሞላ ሲጐድል... ሁሉም መሆን ትቶ መምሰልን ሲመስል.. በዳይ እየሳቀ ተበዳይ ሲያነባ.... #መሳቅ_ግን_እንዴት_ነው? በተወዛገበ በጭንቅንቅ ስሜት የማይቻል ችሎ ከራስ ጋር መታገል.. ፈገግ ለማለት ልብ ውስጥ ሀዘን መቅበር.... በዝምታ ብሩሽ በፀጥታ ቀለም በራስ ልክ ሰው መሳል ሁልጊዜ መኮለም.....? #መሳቅ_ግን_እንዴት_ነው? ተፃፈ ፦ በሀይሚ ሀምሌ 19/2012..ሲዘንብ የተፃፈ @poethaymi @poethaymi @poethaymi
. . . በእርግማኖች መሐል " የአባቴ አምላክ ካለ ..." ሲሉ ሰማሁ ልበል? ታድያ ምነው ... " ካለ " ብለውታል መኖሩን ማወቅ ነው .. ፀሎቱ ይቀድማል? 🤔🤔🤔🤔🤔 👇👇👇 @poethaymi @poethaymi @poethaymi
ሰዉ በረደኝ😔 @poethaymi
፪ ✅ታውቃለህ ? ሕይወት ለሴት ሌላ ናት… ጨካኝ ናት። ስነቃ ዙሪያዬ በእርጉዝ፣ ዙሪያዬ በሰርግ፣ ዙሪያዬ በ“ቆመሽ ቀረሽ” ምክር ታጅቦአል። አንተ እንደ መጀመሪያው አፍላ ፍቅር፣ አፍላ ጭቅጭቅ፣ አፍላ መውደድ ላይ ነህ። ✅ኩርፌያዬ፣ ስጋቴ፣ ጭቅጭቄ ውስጥህ አልዘልቅም አለ። ቁም ነገር የሌለው ፍቅር፣ ያልበሰለ ፍቅር፣ ነገ የሌለው ፍቅር፤ 'አቤት እዚ ጋ ነኝ' የማይሉት ፍቅር ከወንድ በላይ ለሴት ምቾት አይሰጥም። የማይታገል ወንድ፣ ሃላፊነት የማይሸከም ወንድ፣ “እከለልበታለሁ” የማይሉትን ወንድ፣ “አለልኝ” የማይባል ወንድን ባል ማድረግ ያስፈራል። አስቴር አወቀ “ጠይም ዘለግ ያለ፣ የሰፋው ደረቱ ፍቅር ሃላፊ ነው ባረገኝ እህቱ…” እንዳለችው ነው። ፍቅር ሃላፊ እንደሆነ አስተዳደጌ ነግሮኛል ... አያያዛችን ... ✅ፍቅሩ ሲያልፍ፣ የኑሮን ቀንበር ስንሸከም፣ ሲያንገዳግደን፣ ሃላፊነት ሲወጥረን፣ ልጆች ሲመጡ ....... ጫንቃችን “አልተዘጋጀም” አልኩኝ። እንዳላጠናክርህ የምለው አይገባህም፤ እንዳታጠናክረኝ አልጠነከርክም። ልቤ እየወደደህ አልረጋ አለ… “የት ነሽ?” ስባል “እዚ ጋ” ማለት ተሳነኝ፤ ልቤ ሸሸክ… ሄድኩኝ። የተለየውህ እንደ ዋዛ አልነበረም፤ ሌት ቀን አስቤ "ያልበሰለ ሰው ፍቅር አያሻግረም ብዬ እያዘንኩኝ ነው " © Adhanom @poethaymi @poethaymi
፩ ✅ታውቂለሽ ..... ? ተኩሰሽ ብትገይኝ ይታረድ ስለተባለ ስቃይ እንዳይበዛብኝ ነው የተኮሰችብኝ ነው የምለው.... አንቺ ለኔ እንደህልሜ ከልቤ ጠፍተሽ አታቂም ። ሌላ ቦታ ያለዉ ቸልታዬ አንቺ ጋ ሲደርስ አቅም አንሶት ይተጋል ተጎድቼ እምጨነቀው ጉዳቴን የምነገርሽ መንገድ ነው.... ድንገት ተለያየን እንደዋዛ ታውቂኝ የለ ስቃይን መሸከም ፣ የተሰማኝን አምእሮዬ ውስጥ ማስቀመጥ እችላለሁ .... እንዳልናፈቀ፣ እንዳልተጎዳ መሆን መንገዴ አስተምሮኝ የለ? ብንለያይም ልቤ አልተለየሽም ነበር . .... ልቤ ያላዜመሽ ያላወሳሽ ያልተረከሽ ቀን የለም ..... ✅ሲሳካልኝ ፣ስወድቅ ፣ ሲደብረኝ ፣ የልቤን ሳወራ ከትውስታ ከትዝታዬ መሀል እየወጣሁ የማወሳሽ ሚስጥሬ ነሽ ታሪኬ ነሽ .....ትዝታዬም አንቺ ግን ሶስት ወር የምታቂውን ሰው ልታገቢ ነው??! ታድለሻል .....! እኔ የዘገየሁት እራሴን እየጠረብኩ፣ እየቀረፅኩ ፣ እያበጃጀሁት ነበር፣ ...... ✅ያልመጣሁት መቀየሬን ላሳይሽ ፣ ማደጌን ላስዳስስሽ ነበር... ስደርስ ግን በሌላ መንገድ እየሄድሽ ነው.... የውነት ግን ደስተኛ ነሽ ?? ይሁን..... የኔን ግን እንዳልኩሽ ነው ✍️Adhanom Mitiku @poethaymi @poethaymi @poethaymi
አንድ ልጅ እናቱን በጣም ይጠላት ነበር። ለምን ቢባል እናቱ አንድ አይኗ የለም ነበር። "የአንድ አይን ባለቤት ልጅ" እየተባለ በትምህርት ቤት ስለሚሳለቁበት፣ እናቱ ወደ ትምህርት ቤት ስትመጣበት ይሸማቀቅና ይቆጣ ነበር። "ለምንድነው እንዲህ ሆነሽ የምታሳፍሪኝ? ብትሞቺ ይሻል ነበር!" ብሎ ይጮህባት ነበር። ልጁ አድጎ፣ ተምሮና ሀብታም ሆኖ ትልቅ ከተማ ውስጥ መኖር ጀመረ። ትዳር ይዞ ልጆች ወለደ። አንድ ቀን እናቱ ልጇን ናፍቃ ልትጠይቀው ቤቱ መጣች። ልጆቹ ግን አያታቸውን አይተው ደነገጡ፤ እርሱም "ለምን መጥተሽ ልጆቼን ታስፈራሪያለሽ? ውጪልኝ!" ብሎ አባረራት። ከወራት በኋላ እናቱ መሞቷን ሰማ። ወደ ቤቷ ሲሄድ እናቱ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ትታለት ነበር፦ "ልጄ ሆይ፣ ሁልጊዜ ስላሳፈርኩህ ይቅርታ። ግን አንድ ሚስጥር ልንገርህ... ትንሽ ህፃን ሳለህ አደጋ ደርሶብህ አንድ አይንህን አጥተህ ነበር። እኔ ግን ልጄ በአንድ አይን እንዲያድግ ስላልፈለኩ፣ የራሴን አንድ አይን አውጥቼ ሰጠሁህ። ዛሬ አንተ በአይኔ እያየህ ስላለህ እኔ በጣም ደስተኛ ነኝ።" በአለም ላይ ትልቁ ስቃይ ለአንድ ሰው ሙሉ ህይወትህን ሰጥተህ፣ ያ ሰው ግን እንደ ውርደት ሲቆጥርህ ነው። እናትና አባት የሰጡንን ብርሃን ረስተን፣ በራሳችን ብርሃን የፈጠርን ይመስለንና ስንኮራ ነፍሳችን በቁም ትሞታለች። 📕 ርዕስ፦የተሰበሩ ክንፎች ✍🏻 ደራሲ፦ካህሊል ጂብራን 📚 @poethaymi
«በእኔ እይታ ለራሴ ታላቅ ነኝ፤ ምክንያቱም ትግሎቼን፣ መከራዬን እና መሰቃየቴን የማውቀው እኔ ብቻ ነኝ። እንዲሁም ሊያሸንፉኝ ቀርበው ያልተሸነፍኩላቸውን እያንዳንዱን ቅጽበት የማውቅ ብቸኛ ምስክር እኔ ነኝ!።» ፦The Gambler-ዶስቶይቭስኪ Imagination_officially @poethaymi
ሁለት ነገሮች በምድር ላይ እጅግ በጣም ያስፈሩኛል :- ታዋቂነትና አላዋቂነት። በተለይ ታዋቂ ስትሆን (በሰዎች ፊት ከፍ እያልክ ስትሄድ) ልክ እንደ ዝንጀሮ ከስር ያለው መላጣህ ይገለጣል። በዚህ ጊዜ ሁለቱም ያላቸው ሰዎች እየበዙ ነው። እና አንድ ያላዋቂ ታዋቂ ሰው ከሰፈር ሽማግሌዎች ጋር ባልና ሚስት ለማስታረቅ ይቀመጣል። አንቺም ተይ አንተም ተው እያሉ በብዙ ልፋት ወደ ገደለው ጉዳይ ሳይገቡ ሽማግሌዎቹ እንደምንም ከአንገት በላይ ያስታርቋቸዋል። (ይሄ ከENT ሰርጀሪ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም) በመጨረሻ ያ ያላዋቂ ታዋቂ ሰው የመዝጊያ ንግግር እንዲያደርግ ይጋበዛል። እሱም ተነስቶ በመታረቃቸው የተሰማውን ደስታ ገልፆ "በሉ ይሄን የመሰለ ደስታ ብቻችንን መካፈል የለብንም፤ አንቺም ውሽማሽን አንተም ጎረቤት ያለውን ልጅህን ይዛችሁ መደሰት አለብን" በሚል ንግግሩን ይዘጋል። 🙄 እናላችሁ አላዋቂ ታዋቂዎችን እናክማለን ገባ ገባ በሉ🤗🥰 👇👇👇 @poethaymi @poethaymi
የህይወት ወርቃማ ህግ:- መቀየር ባልቻልከው ነገር አትበሳጭ ነገሩን እንዳለ ተቀበለው። የአየሩን ሁኔታ ለመቀየር አንሞክርም ነገርግን በቀላሉ እንዳየሩ ሁኔታ እንለብሳለን። ምርጡ ወንድ 🕴 ➱ ዘወትር ሌሊት 11:30 ይነሳል ➱ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ያደርጋል ➱ አልጋውን ያነጥፋል ➱ ቤቱን ያፀዳል ➱ በትጋት ይሰራል ➱ አልኮል ንክች አያደርግም ➱ ከኩሽና አይጠፋም ➱ በየቀኑ ይጸልያል ➱ ያነባል ➱ ምሽት 9:00 አልጋው ላይ ያርፋል ጥያቄ:- እንደዚህ ያለ ምርጥ ወንድ የት ነው የሚገኘው? መልስ:- ማረሚያ ቤት @poethaymi
✔️የሆነ ሰው ያለ አግባብ የወሰደብህን ገንዘብ አንድ ቀን ሊመልስልህ ይችላል፤ የወሰደብህን ጊዜ ግን መቼም አይመልስልህም። +++ ✔️እድሜ ጊዜ ነው። ሰው ሞተ የሚባለውኮ ጊዜው ሲያልቅ ነው። ጊዜ ሲረዝም እድሜ ሲያልቅ ደግሞ ሞት ነው። ሞት መራራ ከሆነ ምነው የጊዜ መባከን ቢያንስ ሕመም አይሆንብንም? ሰው ቀጥሮህ ሲቀር ከእድሜህ እየቀነሰብህ ነው። የሆነ ሰው ያለ አግባብ የወሰደብህን ገንዘብ አንድ ቀን ሊመልስልህ ይችላል፤ የወሰደብህን ጊዜ ግን መቼም አይመልስልህም። አንድ ሊቅ እንዳለው "ለሰው የምትሰጠው ትልቁ ስጦታህ ጊዜ ነው።" እንዴት? የሰጠኸው ጊዜ ከእድሜህ ላይ የተቀንሰ ነውና። #ሰበዝ -ገፅ 156 በዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ** @poethaymi
መጨረሻውን አውቃለሁ .. ግን መንገዱን ወደድኩት...😊 T.me/poethaymi
ያስታመመ ሲቀብር ብዙ አያለቅስም @poethaymi
✅‹‹እናም በድንገት ከረጅም ጊዜ በኋላ በዚህ ሕይወት "የተሻለ ሰው" ብለን የምናስበው ነገር በጠቅላላ ጠቃሚ ነገር አለመሆኑን እንረዳለን። ያምራሉ የተባሉትን ነገሮች በሙላ ከፍ ከፍ ማድረግ እናቆማለን። በዛ ፈንታ በጸጥታ ውስጥ ተቀምጠን መንፈሳዊ እንሆናለን። ምንም ነገር ባለመፈለጋችን በሁሉም ነገር እረካለን።›› ―ዶ/ር አሕመድ ካሊድ ታውፊቅ @poethaymi
ሰው በውስጡ ይዞት የሚኖረው ቁስል የእድሜ ልክ ህመም ነው:: @poethaymi
ልማድን መስበር ትችላለህ ፤ የመርሳት እድልህ ግን ዝቅተኛ ነው ። 😉 @poethaymi