- Последний пост
- 4 авг.
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 0
- Всего постов
- 20
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- В каталоге с
- 15 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 71
- 1/48двое суток
- 81
- 1/72трое суток
- 87
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
ገንዘባችን ለምን አይባረክም https://youtu.be/BI7Cx7pw8kA?si=yz_59m1CZiy7YZO1
ከየትኛውም ሱስ መላቀቅ የሚፈልግ ሊመለከተው የሚገባ ቪዲዮ 👇👇👇👇 https://youtu.be/qLC3dcyt5vo?si=Et72VYKcOcrfJsZY
📚ርዕስ:- ሕማማት 📝ደራሲ:- ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ 📜ዘውግ፦ ሃይማኖታዊ 📖የገፅ ብዛት:- 460 📅ዓ.ም:- 2010 ጌታችን አጎንብሶ የደቀ መዛሙርቱን እግር ሲያጥብ ይሁዳም ሊታጠብ ተራውን ይጠብቅ ነበር፡፡ ጌታውን ሊሸጥ በተስማማበት ማግሥት ጌታችን አጎንብሶ እግሩን አጠበው፡፡ 'ወኀፀበ እግረ ይሁዳ አስቆሮታዊ ዘያገብኦ' ‹የሚያስይዘውን የአስቆሮቱ የይሁዳንም እግር አጠበ› እንዲል (ግብረ ሕማማት ዘሐሙስ) ከአንድ ቀን በፊት ክፋትን ለማሴር ወደ አይሁድ ካህናት ግቢ የሮጡትን የይሁዳን እግሮች ጌታችን አጎንብሶ አጠባቸው፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ሊያስይዘው ወደ አይሁድ የሚሮጥባቸውን እግሮች ፣ የሚይዙትን ወታደሮች እየመራ ወደ እርሱ የሚመለስባቸውን እግሮች አጠበለት፡፡ ምንም እንኳን በነገው ዕለት እግሮቹን እንዲቸነከር አሳልፎ የሰጠው መሆኑን ቢያውቅም ሰውን ወዳጁ ክርስቶስ ግን የአስቆሮቱ ይሁዳን ለመጨረሻ ጊዜ እግሩን አጥቦ ተሰናበተው፡፡ እንደ ነቢዩ ዳዊት ‹አቤቱ፥ ምሕረትህን እንዴት አበዛህ!› ከማለት በቀር በምን አንደበት ልንናገር እንችላለን? (መዝ. ፴፮፥፯) ‹ጠላቶቻችሁን ውደዱ› ያለን ጌታ አሳልፎ የሚሰጠውን የይሁዳን እግር ሲያጥብ ከማየትስ በላይ በቂም በቀል ለሚቆስለው ልባችን ምን መድኃኒት ይኖር ይሆን?... 📌አሁኑኑ ይ🀄ላ🀄ሉን ቆየት ላሉ መፅሐፍቶች↘️ @ETHIO_PDF_BOOKS1 ለተለያዩ ትረካዎች↘️ @BHERE_TREKA ለትምህርት መፅሐፍቶች⤵️ @YETMHRTPDF
በሰሙነ ህማማት ወቅት የምንሰማቸው እንግዳ ቃላትና ትርጉማቸው በግብረ ሕማማት ውስጥ በግዕዝም ሆነ በኋላ በአማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የእብራይስጥ፣ የቅብጥና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ። የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፦ #ኪራላይሶን፦ ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ < ኪርዬ ኤሌይሶን> ነው። #ኪሪያ ማለት እግዝእትነ / እመቤታችን" ማለት ሲሆን "ኪርዬ" ማለት ደግሞ "እግዚኦ / ጌታ ሆይ / አቤቱ" ማለት ነዉ፡፡ "ኤሌይሶን" ማለት ደግሞ "ማረን / ይቅር በለን" ማለት ነዉ ፡፡ ትርጉሙም "አቤቱ ማረን" ማለት ነዉ፡፡ "ኪራላይሶን" የምንለዉ በተለምዶ ነዉ፡፡ ይኸዉም "ኪርዬ" ከሚለዉ "ዬ" ኤሌይሶን" ከሚለዉ ደግሞ "ኤ" በመሳሳባቸዉ በአማርኛ "ያ"ን ፈጥረዉ ነዉ፡፡ #ናይናን፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "መሐረነ፤ማረን" ማለት ነው። #እብኖዲ ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "አምላክ" ማለት ነው። "እብኖዲ ናይናን" ሲልም " አምላክ ሆይ ማረን" ማለቱ ነው። #ታኦስ ፦ የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "ጌታ፣አምላክ" ማለት ነው። #ማስያስ ፦ የእብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "መሲህ" ማለት ነው። #ትስቡጣ ፦ "ዴስፓታ" ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም "ደግ ገዥ" ማለት ነው። #አምነስቲቲ_ሙኪርያቱ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ "ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ መንግስትከ- አቤቱ በመንግስትህ አስበኝ" ማለት ነው። #አምነስቲቲ_ሙዓግያ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ " ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግስትከ -ቅዱስ ሆይ በመንግስትህ አስበን" ማለት ነው። #አምነስቲቲ_ሙዳሱጣ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ " ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ በውስተ መንግስትከ -የሁሉ በላይ የሆንክ ሆይ በመንግስትህ አስበን " ማለት ነው።
የዓለም ትክክለኛ መልክዋ ይኼ ነው። <ሆሳዕና> ተብሎ ሲዘመር ሁሉም መዝሙሩን ተቀብሎ ይዘምራል፤ አላፊ አግዳሚው ይጋፍል፣ መሬት መርገጥ አይገባህም ብሎ ልብሱን እስከ ማንጠፍ ይደርሳል። በተሰደብክበትና በተዋረድክበት ጊዜ ደግሞ ሁሉም ሊሰድብህ ይሻማል ፤ልትረግጠው አይገባህም ብሎ ባነጠፈልህ መሬት ላይ አንተን አንጥፎ ይረግጥሃል፣ ክሱን እንኳን ሳያጣራ <ይሰቀል ይሰቀል> ብሎ ይጮኸል፤ መንገድ አላፊው ሳይቀር በመሳደብ ይተባበራል ዓለም ንፅህናንና እውነተኝነትን ብትወድ ኖሮ? ከመድኀኒ ዓለም በላይ ንፅሕና እውነተኛ የለም። 📕ህመማት
ጽድቅንና ምሕረትን የሚከተል ሕይወትና ጽድቅን ክብርንም ያገኛል። ምሳሌ 21:21 Share♻️ @yetesfa_qal
እኔ ክርስቲያን ነኝ!! Share ♻️ @yetesfa_qal
ንጉሡ ዳዊትም ገባ በእግዚአብሔርም ፊት ተቀምጦ እንዲህ አለ፦ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ እስከዚህ ያደረስኸኝ እኔ ማን ነኝ 2 ሳሙኤል 7:18 Share♻️ @yetesfa_qal
ብፁዓንስ የእግዚአብሔርን ቃል ሰምተው የሚጠብቁት ናቸው። ሉቃስ 11:28 Share♻️ @yetesfa_qal
እግዚአብሔር ፀሎታችንን መቼ ይመልሳል? /መምህር እዮብ ይመኑ👇👇👇👇 https://youtu.be/mqUIlIRGcM0?si=pFEFVoBJEyadKwwg
እግዚአብሔር የኃይል እና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሀት መንፈስ አልሰጠንምና 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1:7 Share♻️ @yetesfa_qal
ከእናንተ ኀጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት አላቸው። ዮሐንስ 8:7 የራስን ድካማ ማወቅ መላዕክትን ከማየት የበለጠ ጸጋ አለው። ሶርያዊው ቅዱስ ይስሐቅ Share♻️ @Yetesfa_qal
ጸሎታችን ያልተመለሰበት ምክንያት ይህ ነው! ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ #ጸሎት👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://youtu.be/qDXBj93RUjo?si=hqV84RSHWe-V2Ngb
ጌታ ቅርብ ነው።በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋራ በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ። ፊልጵስዩስ 4:6 Share♻️ @yetesfa_qal
እናንተ ደካማዎች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ ማቴዎስ 11:28 Share♻️ @yetesfa_qal
እግዚአብሔር እረኛዬ ነው የሚያሳጣኝም የለም መዝ 23 sahre♻️ @Yetesafa_Qal
አቤቱ ንጹህ ልብን ፍጠርልኝ የቀናውን መንፈስ በውስጤ አድስ መዝሙር 50፥10 Share♻️ @Yetsidq_Qal
በተስፋ ደስ ይበላችሁ በመከራ ታገሱ በጸሎት ጽኑ ሮሜ 12:12 Share♻️ @yetesfa_qal
➲ ➳ አንድ ምድራዊ ንጉሥ "ጠላቱን ያልወደደ ሰው በሞት ይቀጣል" ብሎ አዋጅ ቢያውጅ ሁሉም ሰው በአካለ ሥጋ ላለመሞት ሲል ሕጉን ለመጠበቅ የሚፋጠን አይደለምን? ወዮ! ምድራውያን ነገሥታት በሥጋዊ ሞት እንዳይቀጡን ብለን ፈርተን የሚያወጡትን ሕግ ለመፈፀም የምንፋጠን ሆነን ሳለ፥ ለነገሥታት ንጉሥ ለእግዚአብሔር ሕግ አለመታዘዛችን እንደ ምን ያለ ወቀሳ ያመጣብን ይሆን? ( #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ ) @yetesfaqal
ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየኀቱ፣ ዘተጽሕፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፣ አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ፣ አንቲ ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፤ ወለኪኒ ይሰግድ ውእቱ፡፡ (ማኅሌተ ጽጌ)