Feta Daily News
Статистика- Последний пост
- 14:44
- Последнее чтение
- 15 авг.
- Постов за неделю
- 21
- Всего постов
- 28
- Тип
- открытый
- Язык
- und
- Категория
- Новости и СМИ
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 1 390
- 1/48двое суток
- 1 592
- 1/72трое суток
- 1 717
Медиана по постам, которые мы застали свежими и померили через сутки.
Посты
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
ከኢራን ጋር ያለው ጦርነት የአሜሪካን የጦር መሣሪያ ክምችት እያመነመነ መሆኑና 25 በመቶ ያህሉን የሪፐር ድሮኖች ማሳጣቱ ተገለጠ አሜሪካ ከኢራን ጋር በገባችበት ወታደራዊ ግጭት ሳቢያ እስካሁን ድረስ 25 በመቶ የሚሆነውን የሪፐር ሰው አልባ ድሮን ክምችቷን ማጣቷን ዎሽንግተን ፖስት ባወጣው የምርመራ ዘገባ ይፋ አድርጓል። እያንዳንዳቸው እስከ 50 ሚሊዮን ዶላር የሚገመቱት እነዚህ ውድ ድሮኖች በሆርሙዝ ወሽመጥ ዙሪያ በከፍተኛ ሁኔታ ጥቅም ላይ የዋሉ ቢሆንም፥ ለኢራን እና በኢራን ለሚደገፉ ታጣቂዎች (ፕሮክሲዎች) ግን በቀላሉ ሊመቱ የሚችሉ ኢላማዎች መሆናቸውን ዘገባው አመልክቷል።
https://youtu.be/HfqHiUniHjg?si=dNAjIKz4mJyuTYgE
አር.ኤስ.ኤፍ. ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የምትገኘውን ኩርሙክ ከተማን መቆጣጠሩን ገለጸ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ድጋፍ ሰጪ ኃይል (አርኤስኤፎ) በብሉ ናይል ክልል የምትገኘውንና ከኢትዮጵያ ጋር የምታገናኘውን ስልታዊ የድንበር ከተማ ኩርሙክን በትናንትናው ዕለት ሙሉ በሙሉ በቁጥጥሩ ሥር እንዳዋለ ማስታወቁን አልጀዚራ ዘግቧል። የቡድኑ ቃል አቀባይ ባወጣው መግለጫ መሠረት፥ ታጣቂዎቻቸው ከሱዳን መከላከያ ሠራዊት (ሳፍ) ጋር ለቀናት ያደረጉትን ከባድ ውጊያ ተከትሎ ከተማዋን መያዝ የቻሉ ሲሆን በርካታ የጦር መሣሪያዎችንና ጥይቶችንም መማረካቸውን ገልጸዋል።
ኢራን ያለ ፈቃዷ ማንኛውም መርከብ በሆርሙዝ ወሽመጥ ማለፍ እንደማይችል አስጠነቀቀች የኢራን መንግሥት ከቅድመ ፈቃድ ውጭ ማንኛውም ዓይነት የንግድም ሆነ የጭነት መርከብ ስልታዊ በሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ መጓዝ እንደማይችል ማሳሰቡን አል አረቢያ ዘግቧል። ይህ የቴህራን ጠንካራ መግለጫ በዓለም አቀፉ የባሕር ላይ ንግድ እና በነዳጅ ማጓጓዣ መስመሮች ላይ ከፍተኛ ስጋትን የፈጠረ ሲሆን በቀጣናው ከአሜሪካ እና ከሌሎች የምዕራባውያን ኃይሎች ጋር ያለውን ወታደራዊ ፍጥጫ ይበልጥ ሊያባብሰው እንደሚችል ተስግቷል።
አሜሪካ እና ቻይና በቢሾፍቱው ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ ፉክክር ውስጥ መግባታቸው ተገለጸ የኢትዮጵያ አዲሱ የ12.5 ቢሊዮን ዶላር ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ሀገሪቱን በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ባለው የጂኦፖለቲካዊ ፍጥጫ እምብርት ውስጥ ከቷታል። በቻይና ሞርኒንግ ፖስት በወጣው መረጃ መሠረት፥ በመንግሥት የተያዙ የቻይና ኩባንያዎች የጨረታ ፉክክሩን እየመሩት ቢሆንም፤ ዋሽንግተን እንደ ቦይንግ እና ጄነራል ኤሌክትሪክ ያሉ የአሜሪካ ኩባንያዎች ኮንትራቱን እንዲያገኙ ከፍተኛ ግፊት እያደረገች ነው። የአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ በስተደቡብ ምስራቅ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘውን ይህንን ግዙፍ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እየገነባ ሲሆን፥ ተቋሙ ለአፍሪካ ንግድ እና ጉዞ ዋና ማዕከል ሆኖ እንዲያገለግል ታስቦ የተወጠነ ነው።
በናይሮቢ የሚገኘው የደቡብ ሱዳን ኤምባሲ በቤት ኪራይ ዕዳ ምክንያት መዘጋቱ ተገለጠ በኬንያ ናይሮቢ የሚገኘው የደቡብ ሱዳን ኤምባሲ መንግሥት የናይሮቢውን ቢሮ የነሐሴ ወርን ጨምሮ የአራት ወራት የቤት ኪራይ ክፍያ ባለመክፈሉ ምክንያት መዘጋቱን የኬንያው ኬንያንስ እና ራዲዮ ታማዙጅ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። በናይሮቢ ኪሊማኒ ሰፈር የሚገኘው ይህ ኤምባሲ የተዘጋው ባለፈው ማክሰኞ ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲሆን ይህም በኬንያ ውስጥ ለሚኖሩ የደቡብ ሱዳን ዜጎች የሚሰጠውን የቆንስላ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ አስተጓጉሏል። የኤምባሲው የሥራ ባልደረቦች እንደገለጹት የደቡብ ሱዳን መንግሥት ጣልቃ ገብቶ ያለበትን ውዝፍ ዕዳ እስካልከፈለ ድረስ መሥሪያ ቤቱ ዝግ ሆኖ ይቆያል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የሥራ ዘመን መራዘሙ ተገለጸ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በቀጣይነት እስከ ነሐሴ 2019 ዓ.ም. በኃላፊነታቸው ላይ እንዲቆዩ መወሰኑን ብርሜትሪክስ የቢዝነስ መረጃ ገጽ ዘግቧል። ይህ የሥራ ዘመን ማራዘሚያ ውሳኔ የተላለፈው አቶ መስፍን ወደ ጡረታ ሊወጡ ይችላሉ በሚል ለወራት የዘለቀ መላምት በኢንዱስትሪው ውስጥ ሲንጸባረቅ ከቆየ በኋላ ነው። አዲሱ ውሳኔ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ከተመደበላቸው የመጀመሪያ የሥራ ዘመን በላይ እንዲያገለግሉ እና የአየር መንገዱን ቀጣይ ስልታዊ ዕድገቶች እንዲመሩ ዕድል የሚሰጥ ነው።
ኢልሃን ዑመር በሚኒሶታ የዲሞክራቲክ ፓርቲ የመጀመሪያ ደረጃ ምርጫን በከፍተኛ ድምፅ አሸነፉ የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ኢልሃን ዑመር በሚኒሶታ 5ኛ ኮንግረሽናል ዲስትሪክት በተካሄደው የዲሞክራቲክ ፓርቲ የመጀመሪያ ደረጃ ምርጫ ከ80 በመቶ በላይ ድምፅ በማግኘት ማሸነፋቸውን አልጀዚራ ዘግቧል። ኢልሃን ዑመር ይህንን ድል የተቀዳጁት ለአይሁድ መብት ተሟጋች ከሆነውና ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆነው የአሜሪካ እስራኤል የሕዝብ ጉዳዮች ኮሚቴ ምንም ዓይነት የገንዘብም ሆነ የፖለቲካ ድጋፍ ሳይኖራቸው መሆኑ ስኬታቸውን የላቀ እንዳደረገው ተገልጿል።
https://youtu.be/YL1UyA9I92o?si=2DOBJl65ie4ih_Xi
ደቡብ አፍሪካ ለስደተኞች ማጓጓዣ ያወጣችውን ወጪ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ማላዊ እንዲከፍሉ መጠየቋ ተገለጸ ደቡብ አፍሪካ በሕገ-ወጥ መንገድ የገቡ ስደተኞችን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ያወጣችውን የትራንስፖርት እና የማጓጓዣ ወጪ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ማላዊ እንዲተኩላት መጠየቋን የደቡብ አፍሪካው ዘ ሲቲዝን ባወጣው ዘገባ አመልክቷል። በጊዜያዊ ማዕከል በኩል ወደ ሀገራቸው የተሸኙት ስደተኞች የቪየትናም፣ አልጄሪያ፣ ቦሊቪያ፣ ብራዚል እና የእንግሊዝ ዜጎችንም የሚያካትቱ ቢሆንም ደቡብ አፍሪካ ግን በዋናነት ኢትዮጵያን ጨምሮ ሦስት የአፍሪካ ሀገራት መንግሥታት ወጪውን እንዲሸፍኑላት በይፋ ጠይቃለች።
የዱባይ ገዥ በሱዳን ጦርነት ምክንያት በለንደን ጎዳናዎች ላይ ተቃውሞ ገጠማቸው የዱባይ መሪ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ጠቅላይ ሚኒስትር መሐመድ ቢን ራሺድ አልማክቱም በለንደን ማዕከላዊ ጎዳናዎች ላይ እየተጓዙ ሳሉ ሀገራቸው በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ስላላት ተሳትፎ በአንድ የሱዳን ዜጋ ድንገተኛ ተቃውሞና ወቀሳ እንደገጠማቸው ሚዲያ አይ እና የተለያዩ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ባለፈው እሑድ ይፋ የተደረገው የቪዲዮ ምስል እንደሚያሳየው ግለሰቡ በለንደን ናይትስብሪጅ በተባለው ባለጸጎች በሚኖሩበት አካባቢ ከሌሎች ሰዎች ጋር በእግር እየተጓዙ በነበሩት የዱባይ ገዥ ላይ ከፍተኛ ድምፅ በማሰማት ተቃውሞውን ሰንዝሯል። ተቃዋሚው ግለሰብ ከመንገዱ ማዶ ሆኖ ኤምሬትስ እና ዩኤኢ የሱዳን ሕዝብን እየገደሉ ነው፤ በሀገሬ ላይ ሰዎችን መግደላችሁን አቁሙ፤ ወገኖቼን መግደል አቁሙ ሲል በከፍተኛ ቁጣ መጮኹ በቪዲዮው ላይ ተሰምቷል። በተጨማሪም ግለሰቡ መሐመድ ቢን ዛይድ በሀገሬ ውስጥ ሰዎችን እየገደሉ ነው በማለት የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ፕሬዚዳንትን ስም በመጥቀስ ጭምር ወቀሳውን አቅርቧል።
ትራምፕ በኢራን ላይ በያዙት አዲስ አቋም ምክንያት የዋጋ ግሽበት ስጋት መፈጠሩ ተገለጠ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ የያዙት አዲስ ጠንካራ አቋም፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በነዳጅ እና በኃይል (ኢነርጂ) አቅርቦት ላይ እጥረት በመፍጠር የዋጋ ግሽበትን ሊያባብስ ይችላል የሚል ስጋትን በድጋሚ መቀስቀሱን ብሉምበርግ የዜና ወኪል ዛሬ ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው የትንተና ዘገባ ገልጿል። በዋሽንግተንና በቴህራን መካከል ያለው ፖለቲካዊ ውጥረት ማየሉ የዓለምን የነዳጅ ገበያ መረጋጋት የነሳው ሲሆን ይህም በቀጣይነት ለሚኖረው የዋጋ ንረት መናር እንደ ዋነኛ ምክንያት እየተጠቀሰ ይገኛል።
https://youtu.be/hFQZxoFEHfM?si=Bb-bJBrJv8w9A986
ኢትዮ ቴሌኮም ግዙፍ የተባለ ኔትወርክ የማመዘመን ሥራ መጀሩ ተገለጸ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በምክትል ፕሬዝዳንት እና ዋና ስራ ማስፈጸሚያ ኦፊሰር ሴ ጁንሺ የተመራውን የዜድቲኢ ከፍተኛ ልዑክ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል። በውይይቱም በ2026 በባርሴሎናው የዓለም የሞባይል ኮንግረስ ላይ የተፈረመውን የኔትወርክ ማስፋፊያ እና ማዘመን ስምምነት አፈጻጸም የገመገሙ ሲሆን፤ ይህም የኢትዮ ቴሌኮምን ቀጣዩ አድማስ ዲጂታል እና ከዚያ በላይ 2028 ስትራቴጂ ለማሳካት ያለውን የጋራ ራዕይ የሚያጠነክር መሆኑም ነው የተገለጸው። በዚህም መሰረት 879 ሳይቶችን በሚያካትተው የዜድቲኢ ቀጠና ውስጥ 462 የራዲዮ ተደራሽነት ኔትወርክ ማዘመኛዎች፣ 237 የማይክሮዌቭ ሊንክ ማሻሻያዎች እና 103 የኢንተርኔት ፕሮቶኮል ራዲዮ ተደራሽነት ኔትወርክ ሳይት ማስፋፊያ ስራዎች መጠናቀቃቸው ተመልክቷል።
የሱዳን ጦር መሪ ጀነራል አልቡርሃን በውጭ ሀገር ባሉ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች ላይ የተመሰረቱ የሕዝብ ክሶችን ለማንሳት ተስማሙ የሱዳን ሉዓላዊ ምክር ቤት ሊቀ መንበር ጀነራል አብደል ፈታህ አልቡርሃን በውጭ ሀገር በሚገኙ በርካታ የሱዳን ተቃዋሚ የፖለቲካ አመራሮች ላይ የተመሰረቱ የሕዝብ መብት (የመንግሥት) ክሶች እንዲነሱ መስማማታቸውን የአገሪቱ ብሔራዊ ኃይሎች አስተባባሪ መሪ መሐመድ ሰይድ አሕመድ (አል-ጃኩሚ) ይፋ ማድረጋቸውን አል ሙሐቂቅ ዘግቧል። ይህ ውሳኔ የተላለፈው ሁሉን አቀፍ የውስጥ የሰላም ውይይት ለመጀመር ምቹ ሁኔታን ለመፍጠርና በስደት ያሉ ፖለቲከኞች ወደ ሀገር ቤት እንዲመለሱ ለማስቻል ሲሆን፥ ጀነራል አል ቡርሃን የግል መብት ክሶችም የሰላም ውይይቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ እንዲዘገዩ ለማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። እንደ አል ጃኩሚ ማብራሪያ፥ ጀነራል አል-ቡርሃን ከታሲስ ጥምረት በስተቀር በውጭ ያሉ ሁሉንም የሱዳን የፖለቲካ ኃይሎች በውይይቱ ላይ ለማሳተፍ ፈቃደኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም የቀድሞው ገዥ ፓርቲ (ብሔራዊ ኮንግረስ) ደጋፊዎች በጦርነቱ መሃል ከ10 ጊዜ በላይ መፈንቅለ መንግሥት መጠንሰሳቸውን አስታውሰው ወደፊት መሰል ሙከራ እንዳያደርጉ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን የጦር መሪው ይፋ አድርገዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬት ለስሪላንካ ብሔራዊ አየር መንገድ ትልቅ ማስተማሪያ መሆኑ ተገለጠ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመንግሥት የተያዘ ተቋም ሆኖ ሳለ በዓመት 9.1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ የሚያስገኝ ግዙፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ መሆን መቻሉን የስሪላንካው ዴይሊ ሚረር የዜና ወኪል ዛሬ ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው የትንተና ዘገባ አመልክቷል። ዘገባው እንደሚያሳየው፤ የስሪላንካ ብሔራዊ አየር መንገድ በመንግሥት የተያዘና አሁንም ሙሉ በሙሉ በሀገሪቱ የገንዘብ ሚኒስቴር ድጋፍ ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ በሁለቱ አየር መንገዶች መካከል ያለው መሠረታዊ ልዩነት የባለቤትነት ሳይሆን የሥራ አመራርና የውሳኔ አፈጻጸም ብቃት መሆኑን አስገንዝቧል። ስሪላንካ አየር መንገዷን ለመታደግ በየዓመቱ የሕዝብ ገንዘብ ከመደጎም ይልቅ፥ እንደ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ተቋሙን ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነፃ አድርጎ የሚመራ፣ ግልጽ የንግድ ውሳኔዎችን የሚያሳልፍና የተረጋገጠ ብቃት ያለው ዋና ሥራ አስፈጻሚ መቅጠር እንደሚገባት ዘገባው አሳስቧል።
https://youtu.be/kPrnQLvurGY?si=UtSC8I3BxQRuwtqd