University of Gondar (UoG)
СтатистикаUniversity of Gondar is one of a pioneer public higher education institution with commendable achievements in teaching, research and community services.
- Последний пост
- 11 авг.
- Последнее чтение
- 14:46
- Постов за неделю
- 2
- Всего постов
- 67
- Тип
- открытый
- Язык
- английский
- Категория
- Образование
- В каталоге с
- 13 авг.
- 1/24сутки в ленте
- 2 653
- 1/48двое суток
- 3 040
- 1/72трое суток
- 3 279
Оценка по просмотрам недавних постов: пост набирает почти всё за первые сутки.
Посты
አዲሱ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ከፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ዳይሬክተሮችና ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር የትውውቅ መርሃ ግብር አካሄዱ:: ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ በቅርቡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሆነው የተሾሙት ዶ/ር የቻለ ከበደ በፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት ሥር ከሚገኙ ዳይሬክተሮችና የሥራ አስፈጻሚዎች ጋር የመግቢያ ውይይትና የትውውቅ መርሃ ግብር አካሂደዋል። በፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደው በዚህ መርሃ ግብር፣ በዋናነት በፕሬዚዳንቱና በመካከለኛ አመራሮች መካከል ግልጽና ውጤታማ የግንኙነት መስመር በመዘርጋት፣ የጋራ መግባባትን ማጎልበትና ቅንጅታዊ የአሠራር ባህልን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ዶክተር የቻለ ከበደ፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተጣለበትን ሀገራዊና ተቋማዊ ተልዕኮ ለማሳካት የውስጥ አሠራርን ማጠናከርና በቡድን የመሥራት ባህልን ማሳደግ ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል። አዲሱ ፕሬዚዳንት አክለውም፣ “ተቋማዊ ስኬት ሊመጣ የሚችለው እያንዳንዱ አመራርና ባለሙያ የተጣለበትን ኃላፊነት በከፍተኛ የባለቤትነት ስሜት፣ በቅንጅትና በጋራ ጥረት ሲወጣ ነው” ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል። በውይይቱ ወቅት የተቋሙን የአፈጻጸም ብቃት ማሳደግ፣ የአገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ በውጤት ተኮር አሠራር ላይ ትኩረት ማድረግ እና ያሉትን ሀብቶች በቁጠባና በውጤታማነት ጥቅም ላይ ማዋል የሚያስችሉ ሀሳቦች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። በመድረኩ የተሳተፉት አመራሮች በአዲሱ ፕሬዚዳንት የቀረበውን አቅጣጫ በ ኃላፊነት በተሻለ ብቃት ለመወጣት፣ የተጀመሩ ስራዎችን ለማስቀጠልና አዳዲስ አሠራሮችን ለመተግበር ከአዲሱ አመራር ጋር በሙሉ ትጋት ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። በመጨረሻም ፕሬዚዳንቱ ለተሳታፊዎቹ የቀጣይ የሥራ መመሪያና አቅጣጫ የሰጡ ሲሆን፣ በቀጣይም ከተለያዩ የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ተመሳሳይ ውይይቶችን እንደሚያደርጉ ከፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ለልህቀት እንተጋለን! የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ነሐሴ 4/2018 ዓ.ም
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዲስ ፕሬዚዳንት ተሾመ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በአመራር ደረጃ የተደረገውን ለውጥ ተከትሎ ከሰባት ዓመታት በላይ ዩኒቨርሲቲውን በፕሬዚዳንትነት ሲመሩ የቆዩት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሆነው በመዛወራቸው፣ በምትካቸው አዲስ ፕሬዚዳንት መመደባቸው ታውቋል። አዲሱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ዩኒቨርሲቲው በትምህርት፣ በምርምር፣ በማኅበረሰብ አገልግሎትና በተቋማዊ አስተዳደር ያስመዘገበውን ውጤት በማስቀጠል የተሻለ አፈጻጸም ለማረጋገጥ ከዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብና ከሁሉም አጋር አካላት ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባቸው ተገልጿል። የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማ/ሰብ ፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደርየመንግስት ከፋተኛ ኃላዎችና የሀይማኖት አባቶች ፣ ለቀድሞው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን በተቋሙ እድገት ላይ ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርበው፣ ለአዲሱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር የቻለ ከበደ ቀጣዩ ጊዜ የተሳካ የሥራ ዘመን እዲሆን ተመኝተዋል። ትምህርት ሚኒስተር እያደረገ ባለው አዲስ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፕሬዚዳንቶች ድልድል መሰረት የትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሰረተ-ልማት ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ በተገኙበት በዛሬው ዕለት በሁለቱም ፕሬዚዳንቶች መካከል የስራ ርክክብ ተካሂዷል። ለዶ/ር አስራት እና ለዶ/ር የቻለ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እንመኛለን! ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ለልህቀት እንተጋለን! የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ሀምሌ 21/218 ዓ.ም
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи
видео или голосовое, без подписи